የቤተ ክርስትያን መረጃዎች

የቤተ ክርስትያን መረጃዎች Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የቤተ ክርስትያን መረጃዎች, Religious organisation, Addis Ababa.

09/01/2026

"አዕላፋት ዝማሬ ትርክቱን ሰባበረው" ኤርሚያስ ለገሰ

ኤርምያስ እያለን ያለው የአእላፋት ዝማሬ ለዘመናት ኦርቶዶክስ ሴራ ተሰራባት ተገፋች የሚለውን ትርክት ውሸት መሆኑን ሰብሮ አሳይቶናል እያለን ነው::
ይህ የኤርምያስና የአንዳንድ ፖለቲከኞችን በአእላፋት ዝማሬ ላይ የሰጧቸውነ አስተያየቶች ስመለከት በእጅጉ ስበሳጭና ከራሴ ጋር ስሟገት ነበር :: በእኛም ቤተክርስቲያን ያሉ መምህራን ጎራ ከፍለው ሲወቃቀሱና ሲሰነዛዘሩ ስመለከት የሆነ በፅሞና መታየት ያለበት ነገር እንዳለ ታዝቢያለሁ :: ውስጤ መመለስ አለበት ብዬ የማስባቸው ጥያቄዎች አሉኝ
1.ዲያቆን ሄኖክ ኀይሌም ሆነ የጃንደረባው ማህበር ከመንግስትም ሆነ ከሌላ አካል ጋር ምን አይነት የጋራ ነገር እና የውስጥ ተልእኮ እንደሌላቸው ራሳቸውን በይፋ አያጠሩም?

2.የፖለቲካ የአካላት የከተማዋ ማዳመቂያ ሆነልን ሲሉ ለምን ማስተካከያ አይሰጡም?

3.መንግስት ነፃነቱን የሰጣቸው ምን ጥቅም ስለተገኘ ነው ለምን ሌላው የእንጀራ ልጅ ሆነ
4.ማህበሩ በእርሱ ምክንያቱም ቤተክርስቲያን ስትታመስ ራሱን በግልፅ ጥርት አርጎ መግለፅ ለምን አልፈለገም
5.ትናንት እነ ምህረታብን ጧፍ ይዞ መዘመር ብቻ እያሉ ሲተቹ የነበሩ ዝነኛ መምሀራን ለምን አሁን ዝም አሉ? እንዳውም የምህረታብ ትምህርት ስለነበር አይሻልም?
6.በጃንደረባው ሕግ ሰ/ት ቤት አባል ከሆንክ የግድ ውጣ ትባላለህ ማህበረ ቅዱሳንም አይፈቀድልልም ይህ ለምን ሆነ?
7.ማህበሩ የሄኖክ ነው ወይስ የቤተክርስቲያን? ያለ ሄኖክ መቀጠል ይችላል ?
8.ኦርቶዶክሳውያን አልተገደሉም ያለ ቀሪስ ታጋይ በመርሐ ግብሩ ላይ ለምን በvIP ተስተናገደ? ማህበሩ ከታጋይ ጋር ያለው ህብረት ምንድነው
9.በክርስትናVIP የሚባል ነገር አለ ወይ? ለቆራቢ የተባለውስ ለአርቲስቶች ነበር??
10.የአርቲስቱ ጋጋታ ምንድነው ቤተክርስቲያን አምባሳደር አርጋ መቼ ነው የወከለቻቸው .... የሚሉ መአት ጥያቄዎች አሉኝ:: እናም ጃንደረባው ቀጣይ የቤተክርስቲያን ፈተናዋ ነው አካሄዱ ከፍተኛ የፖለቲካ ክንፍ ነው አሁንምምም ሄኖክና አባላቱ በግልፅ ራሳችሁን አጥሩ

23/12/2025

"ኦሮሞ ስለሆንኩ ነው እየተጠቃሁ ያለሁት" ???
እንደዚህ ያሉት ናቸው ሌብነታቸው ሲነቃባቸው ከጉዳዩ ከማይገናኝ የብሔር ጉዳይ ጋር አገናኝተው ማምለጫ ያደርጉታል
የተጠየከው ስለበላከው ብርና ነውር ነው መመለስ ካለብህ እሱን አብራርተህ መመለስ ነው:: ነገር ግን ጭራጭ እስካሁን ትዝ ያላለህ ማህበረሰብን የሌብነትህ መሸሸጊያ አታድርገው ! ራስህን ችለህ ስለራስህ ተሟገት
ከትናንቱ ጥፋትህ ደግሞ ያሁኑ እጅግ ባሰ

21/12/2025

ጉዳችሁን ስሙሙሙ 😭😭
በቤ/ክ ስም ዝርፊያ?? የስልክ ልውውጥ እስቲ ስሙ
በልደተ ቃል የሚመራው ቡድን
የተመስገን የጌታ ሰው ምስክርነት

ዝርፊያው እዚህ ላይ ደርሷል 😭በቲክቶክ ስሙ ፈለገ አትናቴዎስ የሚባለው ግለሰብ በወላይታ ሀገረ ስብከት የተላለፈበት እገዳ!      በግል አካውንት ብር በማሰባሰብና ለምእመናን ገዳሙ እርዳታ ...
21/12/2025

ዝርፊያው እዚህ ላይ ደርሷል 😭
በቲክቶክ ስሙ ፈለገ አትናቴዎስ የሚባለው ግለሰብ በወላይታ ሀገረ ስብከት የተላለፈበት እገዳ!
በግል አካውንት ብር በማሰባሰብና ለምእመናን ገዳሙ እርዳታ ያስፈልገዋል በማለት በግል አካውንቱ ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ በመቀበል የውንብድና ተግባር ሲሰራ ሀገረ ስብከቱ ከእዚህ ግለሰብ ምእመኑ እነዲጠነቀቅ አሳስቧል
ቀጣይ ደግሞ በስልክ እየደወለ በሐሰት ብር የሰበሰበበትን ስልክ Record ተለቆ ትሰሙታላችሁ

12/11/2025

"በሥልጣናችሁ ስላልመጡ ጥቁር አታስለብሱም እኔ ግን እለብሳለሁ" ልደተ ቃል

ከዚህ በላይ መሟት ይብቃ የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ወንድሞቻችነ ጎን እንቁም! ብሔርና ዘር ቀለም ሳትለይ ሁሉን አንድ አድርጋ ለኖረች ቤተክርስቲያን አንድ ሆነን ሞት ለታወጀባቸው ኦርቶዶክሳውያን...
02/11/2025

ከዚህ በላይ መሟት ይብቃ
የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ወንድሞቻችነ ጎን እንቁም! ብሔርና ዘር ቀለም ሳትለይ ሁሉን አንድ አድርጋ ለኖረች ቤተክርስቲያን አንድ ሆነን ሞት ለታወጀባቸው ኦርቶዶክሳውያን ከጎናቸው እነቁም !!! ቤተክርስቲያን ስደት ላይ ናት ልጆቿ እንደ በግ እየታረዱ ነው ወንድሞቻችንን አለሁ እንበላቸው

15/10/2025
ሰሞኑን በዚህ ልጅ ጉዳይ የደረሱኝ መረጃዎች በጣም ነው ልቤን የሰበሩት! ከባህር ዳር ወደ አዲሳባ ለሥራ ጥቂት ቀናት ቆይቼ እመለሳለሁ በመጣሁባትም አጋጣሚ ቤተክርስቲያን ያሉ መምህራንና ቤተክ...
02/10/2025

ሰሞኑን በዚህ ልጅ ጉዳይ የደረሱኝ መረጃዎች በጣም ነው ልቤን የሰበሩት!
ከባህር ዳር ወደ አዲሳባ ለሥራ ጥቂት ቀናት ቆይቼ እመለሳለሁ በመጣሁባትም አጋጣሚ ቤተክርስቲያን ያሉ መምህራንና ቤተክርስቲያን ላይ የሚሳተፋ ወንድሞችን ማግኘት ደስ ይለኛል :: እናም ፈለገ አትናቴዎስንም በፊት ሲከራከር ሲሟገት ሳየው ደስ ይለኝ ስለነበረ አዲሳባ የመጣሁ ቀን አግኝቼው እንዲበረታም ደስታየን ገልጬለት ነበር :: ከእሱ በላይ ደግሞ አከሊልን በጣም ነው ምወደው እናም ባለበት አግኝቼ አመሰግኜምገነበር
ፈለገ አትናቴዎስ ጉዳይ ላይ ግን የዛሬ 2 ወር ግን አብሮኝ የሚሠራ ጓደኛዬ እህቱ ላይ ስለፈፀመባት ነገር ፎቶና ቪዲዮዎች አውጥቶ አሳየኝ የምር በጣም ነበር ሽምቅቅ ያልኩት በዚህም ሳያንስ ልጅቷን ተጫውቶባት ከክብር አሳንሷት ብዙ ነውር ፈፅሞባታል::እናም ቢያነስ ለቤተክርስቲያን ሲል የተላላካቸው ፎቶና የድምፅ ሪከርዶች እንዳያወጣቸው በብዙ ልመና አስቆምኩት ::
በዚህ ተገርመና ተበሳጭቼ በቅርቡ አንዲት እህት 5 ፎቶችና ረዘም ያለ ፅሑፍ አያይዛ ፃፈችልኝ ::እሷም በልጁ በደል ተፈፀመብኝ በሚል ነበር :: በመምሀርነት እንደቀረበችውና በኋላም ፍቅረኛ እንሁን ብሏት አንድ ቀን ቤቱ ጋብዟት ያለ ፈቃዷ ሊደፍራት እንደሞከረ ነገረችኝ:: ጉዳዩን ለመረዳት ስልክ ሰጥቻት በቴሌግራም ረጅም ሰአት የገጠማትን እያለቀሰች አወራችኝ እንደምትከስና ፍርድ በፍርድ ቤት ልጠይቀው እንደምትፈልግ ነገረችኝ ያለ አንዳች መከላከል እንድትከስ አበረታታኋት::
ከልጁ ጋር በቅርብ ለማቃቸው አንድ ካህንና መምህር በአስቸኳይ በአደባባይ ይቅርታ እንዲልና ይህን ካላረገ ግን መረጃውን እንደማወጣው ለማሳሰብ ሞከርኩ ! እናም እንደዚህ ያለ ነውረኛና በትውልድ የምትቀልዱ ነውረኞች ታሳፍራላቹ ::
እነ አክሊልን አነ ጋዲሳን እነ እፎይን ባየንበት እንደዚህ ያለ ነውረኛ ምእመኑ መቀለጃ መሆን የለበትም
(የቤተክርስቲያን መረጃዎች)

20/09/2025

ጼዴንያ ማርያም

መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም

እመቤታችን ድንግል ማርያምን የምትወድና በሚቻላትም ሁሉ የምታገለግላት፣ ቤቷንም ለእንግዳ ማደሪያ ያደረገች አንዲት ማርታ የምትባል ሴት ነበረች፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አባ ቴዎድሮስ የሚባሉ ኢትዮጵያዊ መነኮስ ከእርሷ ዘንድ በእንግድነት አድረው በማግሥቱ ከቤቷ ሲወጡ ማርታ የሚሔዱበትን አገር በጠየቀቻቸው ጊዜ እርሳቸውም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው ቅዱሳት መካናትን እንደሚሳለሙ ነገሯት፡፡ ማርታም ከእርሷ ገንዘብ ወስደው የእመቤታችንን ሥዕል ገዝተው ይዘውላት እንዲመጡ ለመነቻቸው፡፡ መነኵሴውም በራሳቸው ገንዘብ ሥዕሉን ገዝተው እንደሚያመጡላት ቃል ገቡላት፡፡

አባ ቴዎድሮስ ኢየሩሳሌም ደርሰው ቅዱሳት መካናትን ከተሳለሙ በኋላ ሥዕሏን ሳይገዙ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ሥዕል መግዛትን ለምን ረሳህ?›› የሚል የሚያስደነግጥ ቃልን ሰምተው ተመልሰው መልኳ ያማረና የተወደደ የእመቤታችን ማርያምን ሥዕል ገዝተው በሐርና በንጹሕ ልብስ ጠቅልለው ይዘው እየተጓዙ ሳሉ ከሚያስፈራ ዱር ውስጥ ሲደርሱ ወንበዴዎች ተነሱባቸው፡፡ ሊሸሹ ሲሉም ‹‹መንገድህን ሒድ›› የሚል ቃል ከሥዕሏ ወጣ መነኵሴውም መንገዳቸውን በሰላም ተጓዙ፡፡ ሁለተኛም አንበሳ ሊበላቸው በተነሣባቸው ጊዜ ከዚያች ሥዕል የሚያሥፈራ ድምፅ ወጥቶ አንበሳውን አባረረላቸው፡፡

አባ ቴዎድሮስ ይህን ኹሉ ድንቅ ተአምር ባዩ ጊዜም ያቺን ሥዕል ለማርታ ከመስጠት ይልቅ ወደ አገራቸው ሊወስዷት ወደዱ፡፡ በመርከብ ተሳፍረው በሌላ አቅጣጫ ሲሔዱም ታላቅ ነፋስ ተነሥቶ ወደ ማርታ አገር ወደ ጼዴንያ ወሰዳቸው፡፡ ከመርከብም ወርደው ከብዙ እንግዶች ጋር ወደዚያች መበለት ቤት ደረሱ፡፡ ነገር ግን ማንነታቸውን ለማርታ አልገለጡላትም፤ እርሷም አላወቀቻቸውም ነበር፡፡

በማግሥቱም ተሠውረው ወደ አገራቸው ሊሔዱ ሲሉ የቅፅሩ ደጃፍ ጠፍቶባቸው ሲፈልጉ ዋሉ፤ በመሸባቸው ጊዜም ወደ ማደሪያቸው ተመለሱ፡፡ ማታ ማታ በሩን ያዩታል፤ ነግቶ መሔድን ሲሹ ግን የበሩ መንገድ ይሠወርባቸዋል፡፡ እንዲህም ኾነው እስከ ሦስት ቀን ድረስ ቆዩ፡፡ ማርታም ‹‹አባቴ ሆይ አእምሮህ ተነክቷልን? ስትቅበዘበዝ አይሃለሁና ምን ኾነህ ነው?›› ሰትል ጠየቀቻችው፡፡ እርሳቸውም ከእመቤታችን ሥዕል የተደረገውን ተአምር ሁሉ ነገሯት፤ ራሳቸውንም ገለጡላትና ሥዕሏን ሰጧት፡፡ እርሷም የእመቤታችንን ሥዕል ተቀብላ የተጠቀለለችበትን ልብስ በፈታችው ጊዜ ወዝ ከሥዕሊቱ ሲንጠፈጠፍ አገኘች፡፡ ከደስታዋ ብዛት የተነሣም የአባ ቴዎድሮስን እጃቸውንና እግራቸውን ሳመች፡፡ ሥዕሏም ቅዱስ ሉቃስ የሣላት ነበረች፡፡

ከዚህም በኋላ ያቺን ሥዕል ወደ ጸሎት ቤቷ ወስዳ በታላቅ ክብር አኖረቻት፡፡ ማንም እንዳይዳስሳትም የነሐስ መስኮትን ሠራችላት፡፡ በቀንና በሌሊትም የሚያበሩ መቅረዞችን በፊቷ ሰቀለች፤ ከመቅረዞች ውጭም የሐር መጋረጃን ጋረደች፡፡ ከሥዕሊቱ በታችም እየተንጠፈጠፈ የሚወርደው የወዝ ቅባት የሚጠራቀምበት ከዕብነ በረድ የተሠራ ወጭት አኖረች፡፡ እኒያ መነኰስም እስከሚሞቱበት ቀን ድረስ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገሉ ኖሩ፡፡

የሀገሩ ሊቀ ጳጳስም የእመቤታችን ሥዕል ሥጋ የለበሰች ሆና ባገኙና ተአምሯንም በተመለከቱ ጊዜ ከዚህ አምላካዊ ግብር የተነሣ አደነቁ፡፡ ከሥዕሏ ከሚንጠባጠበው ቅባት ቀድተው ለበረከት ሲካፈሉም ወዲያውኑ በወጭቱ ውስጥ መላ፡፡ ሥዕሊቱን ወደ ሌላ ቦታም ሊወስዷት በፈለጉ ጊዜም ንውጽውጽታ ሆኖ ብዙዎች በድንጋጤ ወደቁ፡፡ ሥዕሊቱም እስከ ዛሬ ድረስ በዚያች አገር በጼዴንያ ትገኛለች፡፡

የሁሉ አምላክን በማኅፀኗ የተሸከመችው ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያምም በሥዕሏ ወዝ ብዙ ሕሙማንን ትፈውሳለች፡፡ ከቅዱሳን ልብስና ጥላ የእርሷ ሥዕል ይከብራልና በየዓመቱም መስከረም ፲ ቀን ቤተ ክርስቲያናችን ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት ውስጥ አንዱ አድርጋ በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፤ የልጇ፣ የወዳጇ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነት አይለየን፡፡

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤተ ክርስትያን መረጃዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share