የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት እና ሥርዓት
The Ethiopian Orthodox Tewahido Church Faith and Order

ይህ የፌስቡክ ገጽ በእግዚያብሄር እርዳታና በድንግል ማርያም አማላጅነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና ክርስቲያኖችን አንድነት ለመጠበቅ ይሰራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የቤተክርስቲያኒቱ ዶግማና ቀኖና እንዲጠበቅም የራሱን አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ገጽ ላይ የሚወጡ ጽሁፎች፤ ፎቶዎች፤ ቪዲዮዎች እና ማንኛውም ዶክመንት የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት፤ ዶግማ፤ ቀኖናና ትውፊት የሚጠብቅ መሆን ይኖርበታል፡፡ ከዚህ በመለስ በተለያዩ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሃሳቦች በጨዋነት መንፈስ ሊንሸራሸሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ገጽ ክርስቲያናዊ በመሆኑ የሚወጡት አስተያየቶችም ሆኑ ጽሁፎች በክርስቲያናዊ ስነምግባር ላይ የተመሰረቱ እ

ንዲሆኑ ይጠበቃል፡፡ በመሆኑም የሚወጡት ጽሁፎችና አስተያየቶች ማንንም ሰው የማይሳደቡ፤ የማይዘልፉ፤ የማያንቋሸሹ መሆኑ ብቻ ሳይሆን በአክብሮትና መግባባት እንዲሁም ሌላውን የሚያንጹ መሆን ይገባቸዋል፡፡
ክርስቶስ በደሙ የመሠረታት ሐዋርያት ሰማዕታትና ቅዱሳን አበው በብዙ ተጋድሎና ድካም እስካሁን ያቆይዋትን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነትና ሥርዓት ቀጣይነት የሚያረጋግጠው በየዘመኑ የሚነሳው ትውልድ እምነቱንና ሥርዓቱን ተረካቢ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው:: ቤተ ክርስቲያን ስንል ክርስትያኖች ከእግዚአብሄር ጋር የሚገናኙበት የተመረጡት ክርስትያኖች ቤታቸውን ለጾሎት ቤት አድርገው የሚጠቀሙበት ቤት አንደሆነ በሐዋርያት ሥራ ም.፭፮ ቁ.፯ የተገለጸ አና በሐዋርይት ሥራ ም.፳ ቁ.፪፰ መሰርረት ክርስቶስ በደሙ የገዛቸው የክርስቶስ አካሉ የሆነች ቤተክርስቲያን መስራት አና መገልገል አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን የተገነዘበችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ አሀጉራት አብያተ ቤተ ክርስቲያን እያነፀች ተከታዮቿን ስትጥብቅ የቆየችዉ።

በመሆኑም የእኛ በሆነው ገጽ ኦርቶዶክሳዊ በሆነ ጠባይ እንሳተፍ፤ እንማማር፤ እንወያይ፤ የቤተክርስቲያናችንን አንድነት፤ ዶግማ፤ ቀኖናና ትውፊት እንጠብቅ! አንድነታችንን እናጠናክር!
ይትባረክ እግዚያብሄር አምላከ አበዊነ!

ወበዛቲ ዕለት ቦኡ ሥሉስ ቅዱስ ውስተ ቤተ አብርሃም ወተሴሰዩ ዘአቅረቦ ሎሙ፡፡ በከመ መጽሐፍ ውስተ ኦሪት ወአብሠርዎ ልደቶ ለይስሐቅ ወባረክዎ፡፡ በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስ...
02/10/2025

ወበዛቲ ዕለት ቦኡ ሥሉስ ቅዱስ ውስተ ቤተ አብርሃም ወተሴሰዩ ዘአቅረቦ ሎሙ፡፡ በከመ መጽሐፍ ውስተ ኦሪት ወአብሠርዎ ልደቶ ለይስሐቅ ወባረክዎ፡፡ በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስት ሥላሴ/ በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ፡፡ የይስሐቅንም ልደት አበሠሩት ባረኩት አከበሩትም፡፡

መጽሐፈ ስንክሳር ዘሐምሌ ሰባት

ሥላሴ ማለት በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት አንድ አምላክ በሦስት አካላት እንዳለ ለአበው ለነቢያትና ለሐዋርያት መገለጡን አምነን የምንማረው ትምህርት ነው፡፡ሥላሴ ማለት የግእዝ ቃል ሲሆን ሦስት፤ ሦስትነት ማለት ነው፡፡

የአንድ አምላክ በሦስትነት መገለጥን ለመረዳት በኦሪት ዘፍጥረት 1፡26 ላይ በተገለጠው መሠረት “እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌችን እንፍጠር” ይላል ይህ አገላለጽ “እግዚአብሔርም አለ” ሲል አንድነትን (አንድነታቸውን) “እንፍጠር” ሲል ከአንድ በላይ (ሦስትነትን) መሆንን ያስረዳል፡፡

በኦሪት ዘፍጥረት 3፡22 ላይ “አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” የሚለው አገላለጽ ከአንድ በላይ መሆንን የሚያስረዳ ነው፡፡በኦሪት ዘፍጥረት 11፡5-7 የተጠቀሰው “ኑ እንውረድ ቋንቋቸውን እንደባልቅ”በማለት ሥላሴ የተናገሩት ከአንድ በላይ (ሦስትነት) መሆንን የሚያመለክት ነው፡፡

በኦሪት ዘፍጥረት18 ላይ ሥላሴ ለአብርሃም እንደተገጹለት የሚያስረዳ ሀሳብ የያዘ አገላለጽ ሲሆን ሥላሴ ለአብርሃም በመገለጻቸው አብርሃም ሥላሴን በእንግድነት አሰተናግዷል፡፡የሥላሴ ባለሟል መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ በእርግናው ጊዜ ልጅ እንደሚያገን ተበስሮለታል፡፡ ዘሩ እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ እንደሚበዛ በሥላሴ ቃል ተገብቶለታል፡፡

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚጠመቅበት ጊዜም የሥላሴ ምስጢር ተገልጧል፡፡ “እግዚአብሔር አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው” ሲል እግዚአብሔር ወልድ ሲመጠቅ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ተገልጧል፡፡ ማቴ.3፡13 አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን ሂዱና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀመዛሙርቴ አድርጉ” ማቴ. 14፡28 ሲል ሦስትነት የሚገልጽ መልእክት አስተላልፏል፡፡ እንግዲህ ሥላሴ ስንል በስም በአካል፣ በግብር የተለዩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ይኸውም፡-

የአካል ሦስትነት፡-

አብ የራሱ መልክ፣ ገጽ፣ አካል አለው፡፡

ወልድ የራሱ መልክ፣ ገጽ፣ አካል አለው፡፡

መንፈስ ቅዱስ፡- የራሱ መልክ፣ ገጽ አካል አለው፡፡

የስም ሦስትነት ስንል፡- የአንዱ ስም ለአንዱ የማይሆን አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ በመባል ይጠራሉ፡፡

የግብር ሦስትነት ስንል፡- አብ ወላዲ፣ አስራጺ ሲሆን ወልድ ተወላዲ ነው የተወለደውም ከአብ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ ነው፡፡ የሰረጸውም ከአብ ነው፡፡

የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ለመረዳት በሥላሴ ፈቃድ መጻሕፍት እንዳስተማሩ ሊቃውንት እንደተረጉሙልን እንጂ ማንም በገዛ ፈቃዱ ተመራምሮ አይደርስበትም፡፡

በዓለ ሥላሴ

በዓላት የሰው ልጅ በእግዚአብሔር የተደረገለትን የቸርነት ሥራ በማሰብ ቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ያደረጉትን ተጋድሎና ተአምራት በመስማትና በማሰማት የተደረገውን ድንቅ ነገር በመዘከር በደስታ የሚከበሩ ዕለታት ናቸው፡፡ “በቃለ አሜን ወበትፍስሕት ድምፁ እለ ይገብሩ በዓለ፡- በዓለ የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና የምስጋና ቃል አለው” እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ.41፡5 የበዓል መከበርን ያሳወቁት ሥላሴ ሲሆኑ፤ ሥላሴ ፍጥረታትን ስድስት ቀናት ፈጥረው ሰባተኛውን ቀን ቀዳሚትን አርፈውበታል፡፡ “በሰባተኛውም ቀን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ፡፡ እግዚአብሔር ሰባተኛውን ቀን ባርከውም ቀድሰውም እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፏልና” ዘፍ.1፡1-3 እንዲል

በዚህ መሠረትነት በዓል እንዲከበር የመደቡት ሥላሴ ሲሆኑ የመጀመሪያው የሥላሴ መታሰቢያና የበዓል አከባበር መጀመሪያ የሆነችው ቀዳሚት ናት፡፡

የዛሬው ሐምሌ 7 ቀንም ሥላሴ በአብርሃም ቤት ገብተው ቸርነታቸውና ፍቅራቸውን የገለጹበት፣ አብርሃምን የባረኩትና ልጅ እንደሚወልድ፣ መጻዒው ሕይወቱን የነገሩት ዕለት ስለሆነ በዓሉን ስናዘክር ሥላሴን እናመሰግናለን፡፡ ቸርነታቸው፣ ፍቅራቸው፣ ትድግናቸው እንዳይለየን እንማጸናለን፡፡ የቅድስት ሥላሴ ቸርነት አይለየን፡፡

30/06/2023

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት እና ሥርዓት
The Ethiopian Orthodox Tewahido Church Faith and Order

03/08/2017

ስምንትና መጽሐፍ ቅዱስ (8 8 8)
8/ 8/ 08 ዓ.ም. ተጻፈ
በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
አበው በብኂላቸው ሰኔና ሰኞ እንዲሉ ብዙዎች ዛሬ ቀኑ 8
ወሩ 8 ዓመቱ 2008 ነውና ሲወያዩበት ሐሳባቸውን
ሲሰጡበት ሳይ እስቲ እኔም ስለ ስምንት ቊጥር በጥቂቱ
ልጻፍ አልኍ፤ በቅዱስ መጽሐፍ ላይ ቊጥሮች በምሳሌነት
በብዙ ስፍራ ላይ ተጠቅሰው እናነብባለን፤ ሰባት እንደ
ፍጹም ቊጥር ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ ሌሎችም
ቊጥሮች ብዙ ነገራትን ለምሳሌ ሱባኤያትን፣ የአንድን
ምስጢር በማጉላት የሚያመላክቱ ሲኾኑ ለምሳሌ ያኽል
እንኳ 666 የሚለውን ቊጥር ዮሐንስ በራእዩ በምዕ 13፡
16-18 የአውሬውም ስም ወይም የስሙ ቍጥር አድርጎ
ሲገልጽ ይልቁኑ አእምሮ (ዕውቀት) ያለው የአውሬውን
ቍጥር ቈጥሮ እንዲረዳው ይጽፋል፡፡
መጻሕፍተ ብሉያት የተጻፈበት የዕብራይስጥ ቋንቋ፣
መጻሕፍተ ሐዲሳት የተጻፈበት የግሪክ፣ ቋንቋና ጥንታዊዉ
የኢትዮጵያ የግእዝ ቋንቋ (አ. በ፣ ገ፣ ደ …) ወደ (ሀ፣ ለ፣
ሐ፣ መ…) ሳይቀየር ፊደላቱ እያንዳንዳቸው ፊደላት
ቊጥርም ጭምር ናቸውና በውስጣቸው ብዙ ረቂቅ የኾኑ
ምስጢራትን እንዳመቁ ዛሬ ድረስ እነዚኽ ጥንታውያን
ቋንቋዎች የአጥኚ ያለኽ እያሉ ዮሐንስ እንዳለው አእምሮ
(ዕውቀት) ያላቸው ልባሞችን ይጣራሉ፡፡
1ኛ) መነሻዬ 8 ቊጥር ነውና ይኽ ቊጥር በመጽሐፍ
ቅዱስ ላይ የተጠቀሰ ሲኾን፡- ከዚኽ መኻከል የጥፋት
ውሃ በምድር ላይ በወረደ ጊዜ ከመጣው መቅሠፍት
በመርከብ ውስጥ ኾነው የተረፉት የሰዎች ብዛት 8 ብቻ
ነበር፤ ይኸውም ኖኅ ከነሚስቱ፤ ሦስቱ ልጆቹ ሴም፣ ካም፣
ያፌት ከነሚስቶቻቸው በአጠቃላይ ስምንት ነፍሳት ነበሩ፤
ከመርከብም ከወጡ በኋላ እግዚአብሔር “ብዙ ተባዙ
ምድርንም ምሏት” ብሎ ስምንቱንም ባርኳቸዋል (ዘፍ 8፡
18፤ 9፡1)፤ ቅዱስ ጴጥሮስም በመልእክቱ “ጥቂቶች
ማለት ስምንት ነፍስ በውሃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፥
የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቈየ ጊዜ ቀድሞ
አልታዘዙም” በማለት ስምንቱንም ያነሣቸዋል (1ኛ ጴጥ
3፡20)፡፡ ስምንቱ ሰዎች የዳኑባት መርከብ በወንጌል፣
በጥምቀት፣ በእመቤታችን፣ በመስቀል፣ በትንሣኤ
ስትመሰል ስምንቱ ደግሞ ባመኑ በምእመናን ተመስለው
ይተነተናሉ፡፡
2ኛ) ቀደምት ሊቃውንትም የእያንዳንዱን ሰዓት ምሳሌነት
በተነተኑበት ድንቅ የብራና መጽሐፍ ላይ፤ ስምንትን
በስምንቱ ሰዎች፣ በስምንቱ የምድር መኣዝናት ሲመስሉ፡-
“፰ ሰዓተ መዓልት ይተረጐም በ፰ ነፍሳት እለ ድኅና
እምአስራበ እይኅ ወበ፰ አጽናፈ ዓለም ዘውእቶሙ ጽባሕ፤
ወዓረብ፤ ሰሜን ወደቡብ፤ መስዕ ወአዜብ ባሕር
ወሊባ” (ስምንተኛው የቀን ሰዓት ከጥፋት ውሃ በዳኑ
በስምንቱ ነፍሳት (ሰዎች) ይተረጐማል፤ ዳግመኛም
በስምንቱ የዓለም ዳርቾች እኒኽም ምሥራቅና ምዕራብ፣
ሰሜንና ደቡብ፣ መስዕ (ሰሜን ምሥራቅና)፣ አዜብ
(ደቡብ ምዕራብ)፤ ባሕር (ሰሜን ምዕራብና) ሊባ (ደቡብ
ምሥራቅ) ይተረጐማል) ብለው ተንትነውታል፡፡ በመኾኑም
ቊጥር 8ን ስናስብ አራቱን ዐበይት መኣዝናት አራቱን
ንዑሳን መኣዝናትን የፈጠረውን አምላክ እናመሰግናለን፡፡
3ኛ) ሌላው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ
እንደምንገነዘበው ልዑል እግዚአብሔር አብርሃምን
ከወገኖቹ ለይቶ ከመረጠውና ቃል ኪዳኑን በርሱና በዘሩ
እንደሚያደርግ ከነገረው በኋላ የዚኽ ምልክት እንዲኾን
ወንዶች ኹሉ በስምንተኛው ቀን እንዲገዘሩ ትእዛዝን
ሰጥቶታል፡፡ ይኸውም በዘፍ 17፡12 ላይ “የስምንት ቀን
ልጅ ይገረዝ በቤት የተወለደ ወይም ከዘራችሁ ያይደለ
በብርም ከእንግዳ ሰው የተገዛ፥ ወንድ ሁሉ በትውልዳችሁ
ይገረዝ” ብሎ፡፡ በስምንተኛው ቀን ግዝረት እንዲፈጸም
የታዘዘው የብሔረ ኦሪት ትእዛዝ ሥጋዊና መንፈሳዊ
ጥቅሞችን ይዟል፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ምስጢር
የተራቀቁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መተርጒማን ሊቃውንት ከፍ ብሎ በዘጠኝ በዐሥር ዝቅ
ብሎ በስድስት በሰባት ሳይል ስለምን ሰው በተወለደ
በስምንት ቀን ይገዘር ብሎ ያዘዘበትን ምክንያት ሲተነትኑ
“ከፍ ብሎ በዘጠኝ በዐሥር ቀን ቢኾን አካሉ
ይጠነክራልና ጸንቶ ባመመው ነበርና ቊስል እንዳይኾንበት
ነው፤ ዝቅ ብሎ በስድስት በሰባት ቀን ቢኾን አካሉ
ልሕሉሕ (ስስ) ነውና ደም አፍትቶበት ይሞታል ብሎ ስለ
ርኅራኄ ሲኾን ምስጢሩ ግን የስምንቱ ብሔረ ኦሪት ሕገ
ምግብና ሲፈጸም ግዝረተ ነፍስ ለሰው እንዲሰጥ
ለማጠየቅ” በማለት ያመሰጥሩታል፡፡
በ፲፱፻፴፭ (1935) እ.ኤ.አ ፕሮፌሰር ኤች ሀም ስለ
ቫይታሚን ኤ ባጠናው ጥናት ላይ እንደገለጸው ቫይታሚን
ኤ ጉበታችን ፕሮትሮምቢን የሚባል ንጥረ ነገር
እንዲያመርት የመደገፍ ሐላፊነት አለበት፤ የቫይታሚን ኤ
ዕጥረት ካለብን የፕሮትሮምቢን ዕጥረት ይከሠትና ደም
መፍሰስ ሊከሠት ይችላል፡፡ እንደ ጥናቱ ገለጻ ዐዲስ
በተወለደ ወንድ ልጅ ሕይወት ውስጥ ከዐምስተኛው ቀን
እስከ ሰባተኛው ብቻ ቫይታሚን ኬ (በአንዠታችን ውስጥ
በሚገኝ ባክቴሪያ የሚመረተው) በበቂ መጠኖች ብቻ
ሲኾን የሚገኘው ይኽ ቫይታሚን ኬ ከፕሮትሮምቢን ጋር
በመቀናጀት የደም መርጋትን ይረዳል፤ ይኽም
በማንኛውም የቀዶ ጥገና ሥነ ሥርዐት ውስጥ በጣም
አስፈላጊ ነው፤ ሆልት እና ሚክንቶሽ ሆልት “ፔዲያትሪክስ”
በሚለው ሥራቸው ውስጥ እንደተነተኑት ዐዲስ የተወለደ
ሕፃን በሕይወቱ ኹለተኛውና ዐምስተኛው ቀናት ውስጥ
በልዩ ኹኔታ ለደም መፍሰስ የመጠቃት ዕድል አለው…
በዚኽ ጊዜ የሚከሠት የደም መፍሰስ ምንም እንኳን
ተጽዕኖ ባይኖረውም አንዳንድ ጊዜ በጣም ሰፊ ሲኾን
በውስጥ የሰውነት አካላት በተለይም በአንጐላችን ላይ
ከባድ ጒዳት የማድረስና እስከ ሞትም ሊዳርግ ይችላል
ብለዋል፡፡ በሚያስደንቅ መልኩ በስምንተኛው ቀን በትክክል
የሚገኘው የፕሮትሮምቢን መጠን ከመደበኛው መቶ በመቶ
100% ከፍ ይላል፤ ይኽም ቀዶ ሕክምና ማድረግ ካለበት
ስምንተኛው ቀን ትክክለኛው ጊዜ ነው፤ የቫይታሚን ኬ እና
የፕሮትሮምቢን ደረጃቸውን የሜዲካል ዶክተር የኾኑት
ኤስ. አይ. ማክሚለን “None of These Diseases”
በሚለው መጽሐፋቸው ላይ በትክክል ገልጸዋል፡፡
4ኛ) በተጨማሪ ስምንት ስናስብ የሚገርመው መጻሕፍተ
ሐዲሳትን የጻፉት ስምንቱ ማለት (ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣
ሉቃስ፣ ዮሐንስ፣ ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ይሁዳ)
ናቸውና ይኽነን እናስባለን፡፡
5ኛ) ስምንት ስናነሣ ሌላው የምናስበው ድንቅ ነገር
ጌታችን በተወለደ በስምንተኛው ቀን ስሙ አስቀድሞ
በመልአኩ ለእመቤታችን እንደተነገረ ኢየሱስ ተብሎ
መጠራቱን ወንጌላዊዉ ሉቃስ ገልጦልናልና ስምንትን
ስናስብ ይኽነንም እናስበዋለን (ሉቃ 2፡21)
በአቡሻሕር የቊጥር ትምህርት የተራቀቁት ቀደምት
የኢትዮጵያ መተርጒማን ሊቃውንት 666 የሚለው
የአውሬው (የሐሳዌ መሲሕ) ቊጥርና ስሙ
“መርምያዋዖስ” መኾኑን የዕብራይስጡን አልፋ ቤት
ቀመረ ምስጢር ቀድመው አውቀው (ሜም 40፤ ሬስ
200፤ ሜም 40፤ ዮድ 10፤ ዋው 6፤ ዔ 70፤ ሳን 350)
ቊጥር ናቸውና በድምሩ 666 እንደኾነ እንደደረሱበት
በራእይ ትርጓሜ ተጽፎልናል፡፡
የዚኽ ቊጥር ተቃናኒ ደግሞ 888 ነው ይላሉ ፤ በእጅጉ
የሚያስደንቀው በጥንት ጊዜ የነበሩት የግሪክ የነገረ
መለኮት ቀደምት 888 ቊጥርን የጌታችን ስሙ አድርገው
ይተረጒሙታልና፤ ይኸውም አስቀድመን እንዳየነው
በዕብራይስጥ፣ በግሪክ፣ የግእዝ (አ. በ፣ ገ፣ ደ …) ወደ
(ሀ፣ ለ፣ ሐ፣ መ…) ሳይቀየር ፊደላቱ እያንዳንዳቸው
ቊጥርም ጭምር ናቸው፤ በግሪክ ቋንቋ የፊደላት የቊጥር
ልኬት “ኢየሱስ” የሚለው በፊደል ሲጻፍ፡-
I H S O U S ተብሎ ነው (I H S O U S (iota, eta,
sigma, omicron, upsilon, sigma)) የፊደላቱም ሥያሜ
(አዮታ፣ ኢታ፣ ሲግማ፣ ኦሚክሮን፣ ኡፕሲሎንና ሲግማ)
ናቸው፤ እነዚኽ የጽርዕ ቋንቋ ፊደላት የያዟቸው ቊጥር
ሲደመሩ 888 ይሰጣሉ፤ ይኸውም አዮታ- 10፤ ኢታ- 8፤
ሲግማ- 200፤ ኦሚክሮን- 70፤ ኡፕሲሎን- 400፤
ሲግማ-200 አጠቃላይ ድምር 10+8+200+70+400
+200= 888 ይሰጣልና፤ በጽርዕ ሊቃውንት 888 ቊጥር
ኢየሱስ የሚለው የፊደሉ ቊጥር ነውና፤ ለ888 ቊጥር
የተለየ ክብር ይሰጣሉ፡፡
በዕብራይስጥ ቋንቋ በነቢዩ በሚልክያስ በምዕ 3፡6 ላይ
“እስመ አነ አምላክ ዘኢይትዌለጥ” (እኔ እግዚአብሔር
አልለወጥም) የሚለው በዕብራይስጥ (Ani YHVH, Lo
shaniti) ሲኾን በዕብራይስጥ ቃላቱ ሲደመሩ 888ን
ይሰጣሉ፤ ይኸውም በቅዱስ ጳውሎስ ቃል “ኢየሱስ
ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው” ተብሎ
ተነግሮለታልና (ዕብ 13፡8) የጌታችንን ስም ያጠይቃል
ብለው ያመሰጥራሉ፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በመዝ 97፡3
ላይ በዕብራይስጡ (Yeshoth Elohenu) “የአምላካችንን
ማዳን አዩ” የሚለውም እንደዚኹ ይኽነን ቊጥር (888)
እንደሚሰጥ ይኽነን በጥልቀት ያጠኑ ይተነትኑታል፡፡
የትዕግሥት አባት ኢዮብ በምዕ 14፡5 ላይ “የሰው ዕድሜ
የተወሰነ ነው፥ የወሩም ቍጥር በአንተ ዘንድ ነው፥ ርሱም
ሊተላለፈው የማይችለውን ዳርቻ አደረግህለት” እንዳለ
በመቀጠልም ጠቢቡ ሲራክም “እግዚአብሔር ወሀቦሙ
ለሰብእ ዓመታተ ወመዋዕለ በኊልቊ” (እግዚአብሔር
ለሰዎች ዓመታትና ዘመናትን በቊጥር ሰጣቸው) እንዳለን
ምእመናን ሆይ በተሰጠን የዕድሜ ቊጥር ዕለት ዕለት
መልካም ሥራ እየሠራን ሥጋ ወደሙ እየተቀበልን መርዐዊ
ሰማያዊ ኢየሱስ ክርስቶስን መብራታችንን አብርተን
እንድንጠብቀው ያስፈልጋል፡፡
ይልቁኑ ሐሳዌ መሲሕን ድል የነሡ፣ ለምስሉ ያልሰገዱ፣
ዘመር ዘመስ የሚለውን የ666ን ምልክት በእጃቸው
ያልተከተቡ በግንባራቸው ያልጻፉ ኹሉ በእግዚአብሔር
መንግሥት ከብረው እንደሚኖሩ ዮሐንስ በራእዩ 15፡2 ላይ
“ወእምዝ ርኢኩ ባሕረ እንተ ትመስል ከመ
ማኅው…” (በእሳትም የተቀላቀለውን የብርጭቆ ባሕር
የሚመስለውን አየሁ፥ በአውሬውና በምስሉም በስሙም
ቍጥር ላይ ድል ነሥተው የነበሩት የእግዚአብሔርን በገና
ይዘው በብርጭቆ ባሕር ላይ ሲቆሙ አየሁ) እንዳለን ዛሬ
በዓለም የሐሳዌ መሲሕ መንገድ ጠራጊዎች እንደ አሸን
የፈሉበትና ምልክቱን በሰው እጅና ግንባር ለመቅበር
የተነሣሡበት ጊዜ ነውና ሰውነታችንን በመላ ለአውሬው
ንቅሳት ሳይኾን ለፈጣሪያችን ለክርስቶስ ብቻ መስጠት
የሚገባን ጊዜ ነው፡፡
የጊዜያት ባለቤት መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በምሕረቱ
ይጐብኘን፡፡
ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

Timket Celebration in Addis Ababa_Ethiopia
19/01/2017

Timket Celebration in Addis Ababa_Ethiopia

Epiphany which locally know as Timket Celebration in Addis Ababa, Ethiopia. Recorded by Beide Mariam Ejigu Retta in January 2016.

01/06/2016

*** *** ** ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› ማለት ሊቀር ነውን? ** ** ** ** **

ቅዱስ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን እንደራሴ ሹመት በተመለከተ ለመወያት የያዘው አጀንዳ የመንግሥት ተወካይ ባለበት እንዲታይ መወሰኑን ዛሬ ጠዋት ሰማን፡፡ ከብጹዐን ጳጳሳት በቀር ካህናትና ቆሞሳት እንኳን የማይገቡበት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ አማኝ ይሁን ኢአማኒ፣ ሙስሊም ይሁን ክርስቲያን የማይታወቅ የመንግሥት ተወካይ እንዲገኝበት መጋበዙ የደረስንበትን የውርደት ደረጃ የሚያሳየን ነው፡፡

በአንድ በኩል የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ወሳኝ አካል መሆኑን ስናስበው፤ በሌላ በኩል የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሚደረገው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ነው፤ ውሳኔውም በሐዋርያት ሥራ እንደተገለጠው ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› የሚባልበት ነው(የሐዋ. 15፣29) የሚለውን ስናየው ‹የመንግሥት ተወካይ ይኑርልን› የሚለውን ውሳኔ ኢሃይማኖታዊ ነው ያሰኘዋል፡፡ ለአንድ የሲኖዶስ ጉባኤ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት አልበቃው ብሎ ነው የመንግሥትን ተወካይ የሚጋብዘው? ‹ሱባኤ ይዘን፣ ጸሎት አድርገን፤ አንድ ገዳም ወርደን፣ ከእግዚአብሔር ጋር መክረን› አይደለም ይሉን አባቶቻችን፡፡ ‹የመንግሥትን ተወካይ ጋብዘን› ነው ያሉን፡፡ እንዲያውም ቀኖናው የሊቀ ጳጳሳቱ(ፓትርያርኩ) ጉዳይ ሲታይ ‹በመቀመጫቸው መካከል አንድ ወንበር አስቀምጠው፣ ቅዱስ ወንጌሉን በዚያ ላይ አኑረው፣ ሊቀ ጳጳሳቱ በፊታቸው ተቀምጦ፣ አንድነት ተነሥተው በሩን ዘግተው ይጸልዩ፤ የተሰበሰቡበትንም ጉዳይ በሥውር(በኅቡእ) ይመርምሩ› ነው የሚለው(ፍ.ነ. ዐ.168)፡፡ እንዴት ተደርጎ ነው የመንግሥት ተወካይ ባለበት የሚታየው? አግዚአብሔር ያየናል የሚለው ጠፍቶ ታዛቢ ቢያስፈልግ እንኳን የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ለታዛቢነት አይበቁም? ቅዱስ ጳውሎስ ‹በወንድሞች መካከል ሽማግሌ ሊሆን የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ አይገኝምን?› (1ኛቆሮ. 6፣5) ያለው ለዚህ ጊዜ አይሆነንም?

በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ የመንግሥት ተወካይ እንዲገኝ መጋበዙ በአንድ በኩል የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና የሚነካ በሌላ በኩልም ሕገ መንግሥቱን የሚጥስ፤ በመጨረሻም ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የሚያፈርስ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ያለ ማንም ጣልቃ ገብነትና ታዛቢነት የራስዋን ጉዳዮች በራስዋ ሕግጋት፣ ቀኖናና ሥርዓት መሠረት የመወሰን መብት አላት፡፡ አባቶቻችን ከንጉሥ ሐርቤ ዘመን ጀምረው ከግብጽ ሲኖዶስ ጋር ሲሟገቱ የኖሩት ይህን ሉዐላዊነት ለቤተ ክርስቲያናቸው ለማስገኘት ነው፡፡ ጳጳሳትን ለማግኘት የግብጽ ሡልጣኖች መለማመጥ፣ የግብጽንም ፓትርያርኮች መለመን ሰልችቷቸው፡፡ ከግብጽ ቀድማ ክርስትናና የተቀበለች ሀገር፣ የራስዋን ጉዳይ ለመወሰን አለመቻሏ አስደናቂ ስለሆነባቸው፡፡ ከቤተ ክርስቲያንዋ ታላቅነትና ከሀገሪቱ ክብር ጋር ስላልተመጣጠነላቸው፡፡

ዛሬ ያ ሁሉ ተረስቶ መንግሥትን በገዛ ፈቃዳቸው ‹አንተ በመካከላችን ካልተገኘህ አንሰበሰብም› የሚሉ አባቶች መጡ፡፡ ቀደምት አበው ‹አንተ ከኛ ጋር ሁን› የሚሉት ፈጣሪያቸው ነበር፡፡ ዘመን ተቀየረ፡፡ በቀደመው ጊዜ ‹መንግሥት ለምን በጉዳያችን ውስጥ ይገባል?› ነበር ክርክሩ፡፡ ‹አሁን መንግሥት ከሌለ ይህንን አጀንዳ አናይም› የሚባልበት ዘመን ላይ ደረስን፡፡ የፓትርያርክ እንደራሴ ጉዳይ የሃይማኖት ጉዳይ ነው፡፡ እንደራሴውም የሚፈጽመው ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ነው፡፡ የሥልጣን ክልሉም በቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን ክልል ነው፡፡ ታድያ ለምንድን ነው መንግሥት ያስፈለገው? ይህንን ጥያቄ ፓትርያርኩ ጠይቀውት ይሆናል፡፡ እንደመከራከሪያ ቢያቀርቡት አይገርምም፤ ቢያሳዝንም፡፡ የምልዐተ ጉባኤው መቀበል ግን ሕመም ነው፡፡

መንግሥትስ ቢሆን ምን ብሎ ነው ተወካይ የሚልከው? ምናልባት ‹ጠሩኝ፣ ሄድኩ› ካላለ በቀር፡፡ ሕገ መንግሥታችን መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ በግልጽ እየደነገገ እንዴት አድርጎ ነው በቀኖናዊ ስብሰባ ላይ የሚገኘው? ውሳኔውንስ ከየትኞቹ የቀኖና መጻሕፍት ጋር ሊያገናዝብ ነው? በጉባኤው የሚኖረውስ ሚና ምን ሊሆን ነው? ምን ዓይነት ወኪልስ ነው የሚወክለው? በየትኛው ሥልጣንና ሕግ ነው የሚገኘው? የዚህ ዓይነቱ አሠራርስ መጨረሻው ምን ይሆናል? በጉባኤው ላይ የሚተላለፈው ውሳኔ የማን ውሳኔ ነው? ‹የእኛና መንፈስ ቅዱስ› ወይስ ‹የእኛና የመንግሥት›? መንግሥትም ጉዳዩን ሊያስብበት ይገባል፤ ‹ሲጠሩት አቤት› ሳይሆን ‹ሲጠሩት ለምን?› መሆን አለበት፡፡

የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ኤጲስ ቆጶስ በዚህ ዓለም መኳንንት ርዳታ አንዳይቆም ያዝዛል፡፡ በእምነቱና በእግዚአብሔር ቃል ብቻ እንዲጸና፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ 176፤ረስጠብ 21) በዲድስቅልያም ላይ ‹ከቤተ ክርስቲያን ሹሞች በቀር ሕዝባዊ አይፍረድ› ይላል (ዐንቀጽ 71)፡፡ ታድያ በምን ሕግ ነው የመንግሥት ተወካይ ባለበት የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤውን የሚያደርገው?

ዛሬ እንደዋዛ የሚከፈተው በር ነገ እንዝጋህ ቢሉት አስቸጋሪ ነው፡፡ አንድ አባት የመንግሥት ተወካይ ይገኝልኝ ባለ ቁጥር የሚፈቀድ ከሆነ፤ ነገ ደግሞ ወንድሜ ባለበት፤ እናቴ ባለችበት፤ ሐኪሜ ባለበት፣ ፖሊስ በተገኘበት ይሄ አጀንዳ ይታይ የሚል ነገር መስማታችን አይቀሬ ነው፡፡ ጋባዡም፤ ተጋባዡም ቆመው ሊያስቡበት ይገባል፡፡ መቼም እንደዘንድሮ የእንጦንስና ጳውሊ ራእይ በተግባር የታየበት ዘመን የለም፡፡

09/04/2016

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ አሜን፡፡
ሠላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ከእኔም ከሁላችንም ጋር ይሁን ፡፡
አሜን ፡፡
ለዛሬ ይህንን ጥያቄ ለበረከትም ለእውቀትም መልሱ፡
✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍
ምላሽን በትክክል ቀድመው ለመለሱ 5 አንባባያን ተአምረኛዋ እሳቷ
ፅዮን ማርያም ገዳም ሙሉ የሶስት ቀን እና የደርሶ መልስ ወጪ
ይሸፈንሎቷል፡፡ከአዲስ አበባ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ያላችሁ በአዲስ አበባ
ለሚገኘው ቤተሠቦቻችሁን ወይም ጓደኞቻችሁን መወከል ትችላለችሁ፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
1, በዛሬው እለት ማለትም ሚያዝያ 1 ታስበው ከሚዉሉት ወርሀዊ
በአላት መካከል ሁለቱን ጥቀሱ?
2,በቤተክርስቲያናችን ስርአት ወንድ ልጅእና ሴት ልጅ በተወለዱ
በስንተኛው ቀን ይጠመቃሉ?
3,የአብይ ፆም እንደ ቅዱስ ያሬድ አሰያየም ስምንቱን የሣምንታት ስያሜ
ጥቀሱ?
4,በነገው እለት ስንተኛው ሳምንት ላይ እነገኛለን ? ስያሜውስ
ምንይባላል?በዚህ ቀን የሚነበበው የመፃሀፍ ቅዱስ ክፍል ምንድ ነው?
5, ታአምረኛዋ እሳቷፅዮን ማርያም በየትኛው የኢትዮጵያ ክልል ፤ዞን እና
ወረዳ ትገኛለች፡፡ልዮ ስሟስ ምን ይባላል?
፠፠፠ ፠፠፠ ፠፠፠፠ ፠፠፠፠
መልሱን ስትመልሱ የክርስትና ስማችሁን አለማዊ ስማችሁን ሰልክ
ቁጥራችሁን መፃፉችሁን አትርሱ ፡፡ይህ ለበረከት የተጠየቀ ጥያቄ ነው፡፡
★ ምላሹን በአማረኛ "ጌትነት ተመስጌን ነኝ "በሚለውየፌስቡክ ገፅ
ላይክ ከአደረጋችሁ በሀላ ዛሬከምሽቱ 5:00 ላይ ይለቀቃል፡፡
★መልሰችሁን በኢንቦክስ ወይም ኮሜንት ላይ ማስቀመጥ ትችላላችሁ
፡፡
ይህ ጥያቄ በየሣምንቱ ይቀጥላል ፡፡
መልካም አድል፡፡፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

11/03/2016

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምለክ አሜን !!
ለዐቢይ ፆም (እንኳን አደረሳችሁ)
ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ የሚጾሙት አጽዋማት 7 ናቸው፡፡ ይኸውም ዐቢይ ጾም ፣ ጾመ ሐዋርያት ፣ ጾመ ፍልሰታ ፣ ጾመ ጋድ (ለውጥ) ፣ ጾመ ድህነት ( ዕሮብ እና ዓርብ ) ፣ ጾመ ነቢያት ፣ ጾመ ነነዌ ሲሆኑ ከዚህም መካከል ዋና ከሆነው አንዱ አሁን የሚጾመው የዐቢይ ፆም ነው ፡፡
ይህ ፆም ደግሞ በልዩ ልዩ ስሞች በአራት አይነት ይታወቃል
ለምሳሌ፡- * ዐቢይ ፆም
* ፆመ ኢየሱስ
* ፆመ ሁዳዴ
* 40/ አርባ ፆም
1ኛ/ ዐቢይ ፆም ፡- ዐቢይ ማለት በግዕዙ ትልቅ ማለት ሲሆን ይህ ፆም ዐቢይ ተብሏል ምክንያቱም አምላካችን በመጀመሪያ ለሰዎች አብነት ለመሆን የፆመው ስለሆነ ትልቁ ጾም ተብሎ ይጠራል በቁጥርም ከሌሎች አፅዋማት ከፍ ያለ ነው ፡፡
2ኛ/ ፆመ ኢየሱስ ፡- በቅዱስ መጽሐፍ ተጠቅሶ እንደሚገኝ ኢየሱስ ክርስቶስ የፆመው ፆም ነውና ፆመ ኢየሱስ ይባላል ፡፡ (ማቴ 4÷1)
3ኛ/ ፆመ ሁዳዴ ፡- ይህ ስያሜ የወጣው ሁዳድ ከሚለው ሲሆን ሁዳድ ማለት ሰፊ የእርሻ ቦታ ማለት ሲሆን እንደ ሚታወቀው ሁሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሀገራችን ክፍለ ሀገር በየ አውራጃው እና በየ ወረዳው ሁዳድ የሚባል ሰፊ የእርሻ ቦታ ነበር ታዲያ ይህ ቦታ የሚያርሱት ከታረሰም በኋላ የሚዘሩት ዘሩም ከበቀለ በኋላ አረሙን የሚያርሙና አጭደው ወደ ጎተራ የሚከቱት አጠቃላይ ስራው ( ሁዳዱ ) በሚገኝበት አካባቢ የሚገኘው ህብረተሰብ ነበር ፡፡
ይህ ስራ የሚሰሩትም በውዴታ ሳይሆን በግዴታ ወንዱም ሴቱም ህጻኑም ሳይቀር እንደ ነበር ታሪክ ያስታውሳል ታዲያ ይህ ዐብይ ፆምም የሥላሴን ልጅነት ያገኙ ክርስቲያኖች በሙሉ እድሜያቸው (ከ7) ዓመት በታች ከሆኑት በስተቀር ሰፊ እና ትልቅ ወደ ሆነው ካገኙት የማያጡት ወደ መንግሰተ ሰማያት የሚያደርስ ስለሆነ ሁሉም የሚፆመው ፆም በመሆኑ አባቶቻችን ፆመ ሁዳዴ ብለው ሰይመውታል ፡፡
4ኛ/ 40 /አርባ/ ፆም በመባል ይጠራል ፡- ይኸውም ጌታ ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሔደ 40 ቀንና 40 ሌሊት ፆመ ፀለየ ብሎ በቅዱስ መጽሀፍ በማቴዎስ 4÷2 ላይ እንደ ተፃፈው ጌታ አርባ ቀን የፆመው ፆም ስለሆነ ነው ፡፡
ነገር ግን እርሱ (40) ቀን ነው የፆመው ለምን ? አሁን (55) ቀን ይፆማል የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል ምክንያቱ ደግሞ ይህ ነው የመጀመሪያው እና የመጨረሻው ሳምንታት ተጨምረው ነው 55 ቀናት የሆኑት
ለምሳሌ፡- የመጀመሪያው ሳምንት ፆመ ህርቃል ይባላል ፡፡ ታሪኩም እንዲህ ነው
በ7ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ የሮም ንጉሰ ነገስት እና የፋርስ መንግስት ዓለምን ጠቅልለው ለመግዛት ከነበራቸው ፍላጎት የተነሳ የከረረ ጦርነት ያደርጉ እና ይዋጉ እንደ ነበር በዚህ ጊዜ እንደሰው ሰውኛ አንድ ጊዜ አንዱን ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ደግሞ ሌላኛው ሲያሸንፍ ከቆዩ በኋላ የፋርስ መንግስት ሀይሉን አጠናክሮ የሮም መንግስትን ድል ነስቶ የሮም ግዛት የነበረውን የመካከለኛውን ምስራቅ ፍልስጤምን በቁጥጥር ስር አደረገ ካደረገም በኋላ ኢየሩሌምን በጦር ኃይል ይዞ ወደ 6000 ሺህ ህዝብ በማስገደል ትልቁ ቆስጠንጢኖስ እና ንግስት እሌኒ በኢየሩሳሌም ያሰሯቸው አብያተ ክርስቲያናት በማቃጠል በውስጡም የነበሩትን የከበረ ንዋየ ቅድሳት እና የጌታችን መስቀል ወስዶ ነበር ፡፡ በዚህ ንብረት በተለይም የጌታችን መስቀል መወሰድ ለህዝቡ ታላቅ ሀዘን እና ውርደት ሆኖባቸው ነበር ፡፡
ነገር ግን ከጥቂት ግዜ በኋላ በዚሁ ዘመን ህርቃል ( ሔራቅሊያስ ) የተባለ ጀግና ሰው የሮም ንጉስ ሆኖ በነገሰ ጊዜ ወዲያውኑ አላማ አድርጎ የተነሳው የህዝቡን እንባ ለማበስ እና ሀዘናቸውን ወደ ደስታ ለመቀየር ማለትም የተወሰደባቸውን ንዋየ ቅድሳት እና የጌታን መስቀል ለመመለስ የመጀመሪያውን ስራ በማድረግ በፋርስ እና በባቢሎን ጦነትን በማወጅ ዘመቻውም እንዲቀናው ደግሞ ጉልበት እና መሳሪያ አድርጎ ለመጠቀም የፈለገው እና ያመነው በፆም እና በፀሎት ሀይል ስለ ነበር ክርስቲያኖችን ሁሉ አንድ ሱባኤ ለአንድ ሳምንት ፆም እና ፀሎት እንዲያደርጉ አዘዘ እርሱም ወደ ፋርስ በመዝመት ያንን ጦር ድል አድርጎት ተመለሰ ፡፡
የተወሰደውም ንብረት እና የጌታን መስቀልም አስመለሰ ታዲያ ከዚያን ጊዜ ጅምሮ ይህ ፆም ትልቅ ዋጋ ያስገኘ ስለ ሆነ ፆመ ህርቃል / የህርቃል ፆም/ ተብሎ ለብዙ ጊዜ ሲፆም ከተቆየ በኋላ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ሲተውት የኛ ቤተ ክርስቲያን ግን ከዐቢይ ፆም ጋር ደርባ እስከ ዛሬ ድረስ ትፆማለች ታስፆማለች የመጀመሪያው ሳምንትም ምክንያት ይህ ነው ፡፡
ሌላው የመጨረሻው ሳምንት ነው ይህ የመጨረሻው ሳምንት (ሰሙነ ህመማት) ይባላል ይህ ሳምንት ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የደረሰውን ስቃይ እና መከራ፣ ስቅላት እና ሞት የሚታሰብበት ሳምንት ነው ፡፡ ስለሆነም ከ55 ቀናት ውስጥ እነዚህ የመጀመሪያው እና የመጨረሻው ሁለት ሳምንታት ሲቀነስ 40 ቀን ይሆናል ማለት ነው ፡፡
ከዚህ በላይ ስለስያሜው ይህን ያህል ከተረዳን ጥቂት ደግሞ
ሀ/ የፆም ዓላማ
ለ/ ፆም ምንድን ነው ?
ሐ/ ፆም መቼ እና በስንት ዓይነት ?
መ/ ፆም ለምን ?
ሠ/ ፆም እንዴት ? ይፆማል የሚሉትን ነጥቦች በዝርዝር እናያለን
ሀ/ የፆም ዓላማ ፡- የፆም ዋና ዓላማ አማኝ የሆነ ሰው አምላኩን እንዲያገኝ ሁለንተናውን ከዓለማዊ እና ስጋዊ ሀሳብ ወይም ምኞት ተለይቶ በመንፈሳዊ ህይወት ሙሉ በሙሉ በማረፍ ከእግዚአብሔር ጋር ብቻ እንዲገናኝ የሚያደርግ መንፈሳዊ መሣሪያ ነው ፡፡
ለ/ ፆም ምንድን ነው ? :-ፆም ማለት መከልከል መለየት ፣ መተው ፣ ማለት ሲሆን ፆም የስጋን ምኞት የምታጠፋ የነፍስን ቁስል የምታደርቅ ለጎልማሶች ትእግስትን ፀጥታን እና እርጋታን የምታስተምር ከእንስሳዊ ግብር እና ጠባይ የምትለይ እና ሰው ፍፁም አምላኩን እና መላእክትን መስሎ እንዲኖር የሚያደርግ ትልቅ ሀይል ያለው መንፈሳዊ መሳሪያ ነው ፡፡
የፆም አዋጅ ያወጀው አምላካችን እግዚአብሔር ሲሆን የታወጀውም ገና አዳምን በፈጠረበት ጊዜ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ለመብላትም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ ከምድር አበቀለ በገነትም መካከል የህይወትን ዛፍ መልካሙን እና ክፉውን የሚያሳይ አበቀለ ዘፍ. 2÷9 አዳምን ፈጥሮ በገነት ባኖረው ግዜ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካሙን እና ክፉውን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከዕርሱም በበላህ ጊዜ የሞት ሞትን ትሞታለህ ያለው አምላካዊ ቃል አለ ይህ አትብላ የሚለው ቃል ትዕዛዝ ቢሆንም ነገር ግን አላማው የፆምን አዋጅ የሚያውጅ ነበር ዛሬም ቢሆን ስለ እውነተኛው ፆም እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ ኢሳያስ እና ኢዩኤል ላይ አድሮ የተናገረው ስለ ፆም አዋጅ ነው ፡፡ ኢሳ 55÷1 ኢዩ 2÷15
ሐ/ ፆም መቼ እና በስንት ዓይነት ? ፡- ፆም በሁለት ይከፈላል ይኸውም የግል እና የማህበር በመባል ይታወቃል
1ኛ የማህበር ወይም የአዋጅ ፆም ነው ፡፡ ይህ ፆም በአንድነት እና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሰረት ማለትም አሁን እየተፆመ ያለው ፆም ዓይነት የማህበር ፆመ ይባላል ፡፡
2ኛ የግል ወይም የፍቃድ ፆም ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሰው በራሱ ጊዜ ወይም በንስሀ አባቱ አማካኝነት የሚፆመው ፆም ነው፡፡ ለምሳሌ ፆመ ፅጌ ፣ ፆመ ጳግሜ ፣ የንሰሐ ፆም ናቸው ፡፡
መ/ ፆም ለምን ፡-
ፆም በቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ላይ የዲያብሎስን ሽንገላ ታቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔር ጦር እቃ ሁሉ ልበሱ ከተባሉት ዋናው ሲሆን የሰይጣንን ረቂቅ እና ተንኮል የሚመከትበት ጋሻም ነው፡፡ (ኤፌ 6፡10)
ፆም ለምዕመናን ወደ ንስሀ የሚጠራ መንፈሳዊ ሀብታችው ለቅዱሳን ደግሞ አጋንንትን የሚያርቁበት እና የሚቀጠቅጡበት ክብራቸው ነው ፡፡ (ማቴ 17፡21)
1ኛ/ የፆም ጥቅም ከእግዚአብሔር ትልቅ ዋጋ የሚየሰጥ ከመሆኑ ባሻገር በፆም የሚገኘውን ተሰፋ በማድረግ በሀጢአት ምክንያት ከመጣብን መከራ ለማምለጥ እና ፀጋ እግዚአብሔርን ለመቀበል ይፆማል ይፀለያል ፡፡
ለምሳሌ ፡- ሀ/ ሙሴ መኮሬብ ተራራ ላይ ህዝበ እስራኤልን የሚመራበት የቃል ኪዳኑን ታቦት
የተቀበለው አርባ ቀን እና አርባ ሌሊት በመፆም እና በመፀለይ ነው (ዘዳ 9÷9)
ለ/ የቤተ ክርስቲያን ሹመት በፆም እና በፀሎት ነው፡፡ ሐዋርያት በርናባስን እና
ሳውልን ሲሾሙ በፆም በፀሎት ነበር ፡፡ (የሐዋ ስራ 13፡2 )
2ኛ/ በማንኛውም ችግር ጊዜ በሀገር፣ በቤተ ክርስቲያን በግል ህይወትም ቢሆን የመጣውና የሚመጣው ፈተና ለማሸነፍ የፆማል ይፀለያል ፡፡
ለምሳሌ ፡- ሀ/ የነነዌ ሰዎች ከመጣባቸው መዓት የዳኑት በፆም ነው፡፡ (ዮናስ 3÷1)
ለ/አስቴር እና መርዶክዮስ በወገኖቻቸው ላይ በሐማ ተንኮል ምክንያት በታወጀባቸው
የሞት አዋጅ የዳኑት እና በሦስት ቀን ፆም እና ጸሎት ነው፡፡ (አሰቴር 4፡1)
ሐ/ ዳዊትም ልጁን በሞት ባጣ ጊዜ ከሞት እንዲነሳለት እንዲሁም ስለ ኃጢዓቱ
ስርየት ፆሟል (2ኛ ሳሙ 12÷1) ነፍሴን በመፆም አስመረርኳት (መዝ 69÷10)
መ/ የእስራኤል ልጆች ከብንያማውያን በሚዋጉበት ጊዜ ሲሸነፉ ፆመዋል ፀልየዋል
(መሳ 20÷24 ) ወደ እግዚአብሔር ለመንን እርሱም ተለመነን (ዕዝ 8÷23)
ሠ/ ፆም እንዴት ይፆማል ፡- ፆም ሲፆም ጥንቃቄ ያስፈልጋል
1ኛ/ ፆም ሲፆም ከብዙ ነገሮች መጠንቀቅ የሚያስፈልግ እንደሆነ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴዎስ 6÷16 ላይ ስትጾሙ እንደ ግብዞች አትሁኑ በማለት ፆምን ለተርዕዮ ፣ለጉራ፤ ለታይታ፤ ለውዳሴ ከንቱ እንዳይሆን መጠንቀቅ እንደ ሚያስፈልግ ደግሞም ሲፆም ዋጋ ማግኝት የሚቻለው ከዕርሱ ጋር ብቻ በመነጋገር መሆኑን ማመን ምክንያቱም አንዳንድ ሰዎች ባለማወቅ መፆማቸውን እና መፀለያቸውን እንዲታወቅላቸው ወይም የሚበሉትን ጥሬ እንደ ሆነ እስከ 6፤9፤12፤ ሰዓታት ሳይበሉ መቆየታቸውን ሲናገሩ ይስተዋላሉ ፡፡
እንዲህ አይነቱ አስተሳሰብ ጌታ በማስጠንቀቂያ ስትፆሙ ፣ ስትፀልዩ ፣ ስትመፀውቱ እንደ ግብዞች አትሁኑ በማለት አስተምሯል ፡፡ ማቴ 6÷1፡18
2ኛ/ በፆም ወቅት ከምግብ እና ከጥሉላት ነገሮች መፆም ብቻ እንዳልሆነ ሲናገር ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የስሜት ህዋሳቶችን በሙሉ መቆጣጠር እና ማስፆም እንደሚገባ (ይፁም አይን ይፁም ልሳን እዝንኒ ይፁም ዕምሰሚዓ ሕሱም ለተናግሮ ) በማለት አይን ክፉ ነገር ከማየት፣ አንደበት ክፉ ነገር ከመናገር፣ ጀሮ ክፉ ነገር ከመስማት፣ ልብ ክፉ ነገር ከማሰብ፣ እግርን ወደ ክፉ ቦታ ከማስኬድ በመከልከል እና በመፆም ይሁን በማለት ዘምሯል፡፡
በተጨማሪም በፆም ወቅት አመፅን እና በደልን አስመሳይነትን፤ ጠብ እና ክርክርን ጭካኔን በማስወገድ ለክርስቲያን ወገኖች በሙሉ አርዓያ መሆን እንደሚገባ በቅዱስ መጽሐፍ ተጠቅሷል (ኢሳ 58÷1-13 ) (ኢር 14÷10)
እንዲሁም ነቢዩ ዳንኤል በዚያም ወራት እኔ ዳንኤል ሦስት ሣምንት እስኪፈፀም ድረስ ስጋ እና ጠጅ በአፌ አልገባም ሲል መስክሯል ፡፡ ( ዳን 10÷2) (ነህ1÷4 )
(3ኛ) ሦስተኛው እና የመጨረሻው ጥንቃቄ ድሆችን በማሰብ መፆሞ ነው ፡፡
በዘዳግም 15÷7 ላይ እግዚአብሔር በድሀው ወገንህ ላይ ልብህ አይጨክን በማለት ያዛል ፡፡
ይህ ማለት ከፆም ውጪ ባሉት ቀናት ውስጥ ቁርስ ምሳ ይበላል አሁን ደግሞ ይህ የለም ፆም ነው ታዳያ በፆም ጊዜ የቁርስ እና የምሳ ፋንታ ማሰቀመጥ ሳይሆን ለድሆች በመስጠት ወይም በገንዘብ ተምኖ ለቤተ ክርስቲያን ለእጣን፤ለጧፍ ለልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት ወይም ለስብከተ ወንጌል ማስፋፈያ መስጠት ያስፈልጋል ሲል ነው ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ፆም ሳይሆን የሚሆነው የኑሮ ቁጠባ ወይም የረሃብ አድማ ነው የሚባለው ፡፡
ጌታ ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜም ከሚጠይቃቸው አንዱ እና ዋናው ጥያቄዎች ተርቤ አላበላችሁኝም ፤ተጠምቼ አላጠጣችሁኝም፤ታምሜ አልጠየቃችሁኝም፤ ታርዤ አላለበሳችሁኝም ነው የሚለው፡፡
በዚህ ጊዜ መች አየሁ ? የሚል ባለ ምክንያት ካለ የጌታ መልስ ከእነዚህ ከሁሉ ለሚያንሰው ለአንዱ ለድሃው ብታደርጉ ለእኔ እንደ አደረጋችሁ አደለምን? ነው (ማቴ 25÷35-46)
በመጨረሻም ማስገንዘቢያ ( አሁንስ ይላል በፍፁም ልባችሁ በፆምም በልቅሶ እና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ፡፡ ኢዩ 2÷12) የፆም ፀሎት ድካም ከንቱ እንዳይቀር መደረግ የሚገባውን በማድረግ ደግሞም መደረግ የማይገባውን ባለማድረግ በፍፁም ልብ በመመለስ ከሆነ እግዚአብሔር የሚቀበል መሀሪ እና ይቅርባይ ታማኝ አባትና አምላክ እንደሆነ የልጀቹን ፆም እና ፀሎት በደስታ እንደ ሚቀበል ቅዱስ መፅሐፍ ያረጋግጣል፡፡ ( የጌታ አይኖች ወደ ፃድቃን ናቸው ጆሮዎቹም ለፀሎታቸው ተከፍተዋል (1 ጴጥ 3÷12)
ፆሙን ፡- * የሐጢዓት መደምሰሻ
* የዲያብሎስ ድል መንሻ
* የመንግስተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አዘጋጅ ፡- መምህር እዝራ ንዋይ

☆•♥• ☆  #ቅዳሴ ☆•♥• ☆+♥ በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው? ♥ 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት እነማን ይሆኑ?♥ ካህናት በቅዳሴ ወቅት 2: 3: 4: 5: 7: 12: ወይም 24: ሆነ...
24/12/2015

☆•♥• ☆ #ቅዳሴ ☆•♥• ☆
+
♥ በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
♥ 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት እነማን ይሆኑ?
♥ ካህናት በቅዳሴ ወቅት 2: 3: 4: 5: 7: 12: ወይም 24: ሆነው ከቀደሱ ምሳሌነቱ ምን ምን ይሆን?
♥ እኛ ክርስቲያኖች ቅዳሴን ባስቀደስን ቁጥር 4 ነገሮች እናገኛለን ምን ይሆኑ?
♥ አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ እንዴት?
♥ ♥ ♥
አውቀነው እንጠቀምበት ዘንድ ይነበብ.....ለሌሎች ሰማያዊ ምሥጢርን አካፍለን የተሰጠንን መክሊት እናተርፍበት ዘንድ እንትጋ
+
☆•♥• ☆ #ቅዳሴ ☆•♥• ☆
ቅዳሴ በሥርዓተ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት በኅብረት የሚጸለይ የኅብረት ጸሎት ነው፡፡ ከፀሎቶች ሁሉ የላቀ የፀሎት ክፍል ነው፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ፭ቱ ምሥዋዕቶች ተሞልተው ይገኙበታል እዚህንም ፭ቱን መሥዋዕቶች ማንኛውም ክርስተያን ለፈጣሪው የሚያቀርበው ነው፡፡

፩. የቁርባን መስዋዕት፡-
+
በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ውስጥ ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ መለኮት ወይኑ ተለውጦ ደመ መለኮት የሚሆነው በቅዳሴው ፀሎት ነው ሳናስቀድስ አንቆርብምና የቁርባን መስዋዕት የሚፈጸመው በሥርዓተ ቅዳሴ ብቻ ነው፡፡ መስዋዕቱም በቤተልሔም ይዘጋጃል በቤተክርስቲያን ውስጥ በቤተ-መቅደስ ውስጥ ደግሞ ይቀርባል ወይም ይታደላል፡፡ ጌታችን ሲወለደ በቤተልሔም ተወልዶ ቀራንዮ ለዓለም ሁሉ መስዋዕት ሆኗልና ቀራንዮ በተባለች በቤተክርስቲያን ቅዱሱ መስዋዕት ለሕዝብ ይታደላል፡፡

፪. የከንፈር መስዋዕት፡-
+
ካህኑ፣ ዲያቆኑና ሕዝቡ በመቀባበል በአንድነት ምስጋና ለፈጣሪያቸው የሚያቀርቡበት የከንፈራችን ፍሬ የሚሰዋበት የፀሎት ክፍል ፀሎተ ቅዳሴ ነው፡፡

፫. የመብራት መስዋዕት፡-
+
በቅዳሴ ጊዜ የሚበራው ጦፍ ለእግዚአብሔር
የሚቀርብ የሚሰጥ የመብራት መስዋዕት ነው፡፡ ምሳሌነቱም የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው ይህውም ጌታችን ጨላመ ለሆነ ዓለም
ብርሃን ሆኖ ብርሃንን ሊያበራ ወደ ዓለም መቷልና ነው፡፡

፬. የዕጣን መስዋዕት፡-
+
የዕጣን ፀሎት ካህኑ ብቻ የሚያጥነው ሲሆን ይህውም በማዕጠንቱ አማካኝነት ቅዱሱን እጣን በመንበሩ፣ በቅዱሳን ስዕላቱ፣ በሕዝቡ መካከል ያጥናል ይህውም የሕዝቡን ፀሎት ወደላይ በደሥላሴ መንበር ይዞ ይወጣል በሰማይም ያሉ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሥላሴን መንበር እንደሚያጥኑ ሁሉ በምድርም ያለው ካህን የሰማያዊው ምሳሌ ነውና በምድር ያውን መንበር በማጠን ለእግዚአብሔር የዕጣን መስዋዕት ያቀርባል፡፡

፭. የሰውነት መስዋዕትነት፡-
+
በቅዳሴ ጊዜ አብዛኛውን ሰዓት ሙሉውን ማለት ይቻላል በመቆም የሚፀለይ የፀሎት ክፍል ነው፡፡ በመሐል 2 ጊዜያት ብቻ የስገዱ ትዕዛዝ ሲተላለፍ ሕዝቡ ሁሉ ፊቱን ወደ ፈጣሪው አዞሮ እራሱን አዋርዶ ይሰግዳል በእግዚአብሔር ፊት መቆምም ሆነ መስገድ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ የሰውነት መሥዋዕት ነው፡፡
☆•♥• ☆ •♥• ☆•♥• ☆
ይህ የፀሎት ክፍል (ቅዳሴ) በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላ
፩. የዝግጅት ክፍል
፪. የንባብና የትምህርት ክፍል
፫. ፍሬ ቅዳሴ
እዚህ ፍሬ ቅዳሴያት እንደየበዓሉ ይለዋወጣተሉ ብዛታቸውም ፲፬ (14) ናቸው እነዚህም፡-

፫.፩. ሥርዓተ ቅዳሴ
፫.፪. ቅዳሴ ዘሐዋርያት
፫.፫. ቅዳሴ እግዚእ
፫.፬. ቅዳሴ ማርያም
፫.፭. ቅዳሴ ዘዮሐንስ ወልደ ነጓድጓድ
፫.፮. ቅዳሴ ዘሠለስቱ ምዕት
፫.፯. ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ
፫.፰. ቅዳሴ ባስልዮስ
፫.፱. ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
፫.፲. ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ
፫.፲፩. ቅዳሴ ዘዮሐንስ አፈወርቅ
፫.፲፪. ቅዳሴ ዘቄርሎስ
፫.፲፫. ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ
፫.፲፬. ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ
♥♥♥
-የጌታችን በዓል ከሆነ … (ቅዳሴ እግዚእ)
-የጌታችን ምጽአት፣ ጶጉሜ እሁድ ቀን ከዋለች ሰንበት … (ቅዳሴ አትናቴዎስ)
-የእመቤታችን በዓል ከሆነ ቅዳሴ ማርያም … (ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ)
-የመላእክትና የሐዋርያት በዓል ከሆነ … (ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ)
-ከዘመነ ልደት እስከ ዘመነ ግዝረት … (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልዕ)
☆•♥• ☆ •♥• ☆•♥• ☆
ቅዳሴን ለመቀደስ ብዙ ጊዜ ፭ሆነው ይቀድሳሉ ይህው የአምስቱ አዕማደ ምሥጢራት ምሣሌ ናቸው፡፡ ነገር ግን ከዚያም በሚያንስም ሆነ በሚበዛ ሰው ቅዳሴን መቀደስ ይቻላል ለምሳሌ ፯ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ይመስላሉ ፲፫ በ12ቱ ሐዋርያት እና በጌታችን ምሳሌ ሆነው ይቀድሳሉ፤ 24 በሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይህ የሚሆነው እንደ ካህናቱ ብዛት ነው ጭራሽ ካህን ከጠፋ ደግሞ 1 ቄስና 1 ዲያቆን ሆነው መቀደስ ይችላሉ ሁለትነታቸው የመለኮትና የትስብዕት (የሥጋ) ምሳሌ ሆነው ይቀድሳሉ በሦስት ከሆነ በሦስቱ ሥላሴዎች አራት ከሆኑ በ4ቱ ወንጌላውያን ይመሰላሉ ከሁለት ባነሰ ግን 1 ሆኖ ግን ቅዳሴ አይቀደስም ቀኖናው የቤተክርስቲያኒቱ ሥርዓት ይከለክላል፡፡
☆•♥• ☆ •♥• ☆•♥• ☆
“ጸልዩ” ይህ የቅዳሴው የፀሎት ዓይነት ሲሆን ለ13 ጊዜያት ይባላል፡፡
በሦስተኛው ክፍለ ቅዳሴ 4 ጊዜ ይባላል ፀልዩን ዲያቆኑ ሲያውጅ ፊቱን ወደ ህዝቡ ይመልስና እንዲጸልዩ ያውጃል፡፡ በዚህ ጊዜ ተሰጥዖ ካለ ተሰጥዖ ይመለሳል ከሌለ ግን “አቡነ ዘበሰማያት” ሕዝቡ እንዲደግሙ ያውጃል፡፡
+
ለምሳሌ፡-
ንፍቁ ዲያቆን “ፀልዩ በእንተ እለያበዕኡ መባዕ … መባን ስለሚያገቡ
ሰዎች ፀልዩ” ሲል በዚህ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት አይደገምም ምክንያቱም
የራሱ ተሰጥዖ ስላለው “ተወከፍ መባዖሙ ለአሃው ወተወከፍ መባዖን…”
ይህ አቡነ ዘበሰማያት የሚተካ ፀሎት ነው፡፡
ድርገት ሲወርዱ “ፀልዩ በእንቲአነ” በሚባልበት ጊዜ እንድንጸልየው
የሚያዘው የዳዊትን መዝሙር 150ኛውን መዝሙር ነው፡፡ ፀልዩ ብሎ
ያዘዘው በዚህ ክፍል ያለ የዳዊትን 150ኛውን የመዝሙር ክፍል ነው
ማለት ነው፡፡
☆•♥• ☆ •♥• ☆•♥• ☆
እኛ ክርስቲያኖች ቅዳሴን ባስቀደስን ቁጥር
1ኛ የኃጢአት ሥርየት ይገኛል ምክንያቱም በአንቃዕዶ ሕሊና ይቅርታን ስለሚጠይቅ፣
2ኛ በነፍስም በስጋም በረከትን ያገኛል፣
3ኛ ጸሎቱም ይደመጣል፣
4ኛ የመላእክትን በረከት በቀጥታ እንሳተፋልን ቅዳሴን አስቀድሶ ሥጋ ወደሙ ሲቀበል የዘለዓለምን በረከት ያገኛል፡፡
+
በተጨማሪም ቅዳሴ በማስቀደስ
4 ነገሮች ይገኛሉ እነዚህም፡-
heart emoticon
፩. ትምህርት
+
የቤተክርስቲያኒቱን ዶግማ እና የሥርዓተ ቤተክርስቲያን ትምህርት በቅዳሴ ገዚ ያገኛል፡፡ ለምሳሌ የማርያምን ቅዳሴ አባ ሕርያቆስ የደረሰውን ይህን ቅዳሴ ሲቀደስ በውስጡ ምሥጢረ ሥላሴ፣ እና ምሥጢረ ሥጋዊ እና ነገረ ማርያምን አምልቶ ይነግራል፡፡
heart emoticon
፪. ታሪክ
+
14ቱንም ቅዳሴ የሚያስቀድስ ሰው የቤተክርስቲያንን ታሪክ በቅዳሴ ውስጥ እንማራለን፡፡
heart emoticon
፫. ምክር
+
በቅዳሴ ውስጥ ተፋቀሩ፣ መጽውቱ፣ ተስማሙ፣ ጹሙ፣ ጸልዩ እየተባለ በቅዳሴ ውስጥ ሰፋ ባለመልኩ ምክር ይሰጣል ስለዚህ ቅዳሴን በማስቀደስ ምክርን ማግኝት ይቻላል ማለት ነው፡፡
heart emoticon
፬. ተግሣጽ
+
ቅዳሴ ውስጡ ተግሣጽን ይዞ እናገኝዋለን ለምሳሌ በቅዳሴ እግዚእ ላይ ከወንድሙ ጋር የተጣለ ቢኖር ይተውለት ይላል በዚህ የቅዳሴ ክፍል ውስጥ ራሳችንን ምን ላይ እንደቆምን ከሰዎች ጋር ያለንን ኅብረት ስምምነት ለፈጣሪ ራሳችንን ማስገዛታችንን እየገሠፀ ይነግረናል፡፡ እነዚህን መሠረታዊ የሆኑትን ለሰው ልጆች ጠቃሚ የሆኑ ነገሮችን ቅዳሴ በማስቀደስ እናገኛቸዋለን፡፡
heart emoticon heart emoticon heart emoticon heart emoticon heart emoticon
-ቅዳሴ ንባብም ዜማም የሚቀርብበት የፀሎት ክፍል ነው፡፡ ሁላችንም የምንሳተፍበት ቄሴም ዲያቆኑም ምእመኑም የሚሳተፉበት ነው፡፡
“ኢትቁም እራቀከ ቅድመ ነቢየ እግዚአብሔር … በእግዚአብሔር ነብይ ፊት ራቁትህን አትቁም” ይህ ማለት በቅዳሴ ጊዜ ሰው ካለ መባ፣ ካለ እጅ መንሻ በእግዚአብሔር ፊት ሳይዙ መቆም እንደሌለበት ያጠይቃል፡፡ ምንም ባይኖረን እንኳን ያለንን አነሰ ብለን ሳንሳቀቅ ደግሞም ሳንንቃት ይዘን በፊቱ መቅረብ አለብን ከቻልን እጣኑን፣ ዘቢቡን፣ ጦፉን ሌላም ሌላም ይዘን መሄድ ተገቢ ነው፡፡ ምክንያቱም ካህኑ በቅዳሴው መሃል ምዕናን ስለሚያስገቡት መባ የሚፀልየው ፀሎት አለ ምዕመኑም መባን ይዞ የማይመጣ ከሆነ ይህ ፀሎት ለማን ነው? ብሎ መጠየቅም ይገባል፡፡
-ስለዚህ ቅዳሴን የምናስቀድሰው አስቀድመን ተዘጋጅተንበት መሆን አለበት፡፡ ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ጊዜ ባይኖረን ለቅዳሴ ግን ጊዜ መድበንለት ልናስቀድስ ይገባል፡፡ ቅዳሴ ለማስቀደስ ወደ ቤተክርስቲያን ስንመጣ ራሳችን
+
1ኛ ቆምን ለማስቀደስ
2ኛ የሚነበቡትን መጻሕፍቶች ከሕይወታችን ጋር እያዛመድን ለማዳመጥ ለመስራት
3ኛ ቅዱስ ቁርባን ለመውሰድ የዘለዓለም ሕይወትንም ለማግኝት አምኖ መምጣት አለበት
-በቅዳሴው የመግቢያ ክፍል ይህንኑ በዜማ “እስመጨረሻው ቅዳሴውን ያላስቀደስ ቅዱሳን መጻሕፍትን ሲነበቡ ቆሞ ያላዳመጠ በመጨረሻም ቅዱስ ቁርባን ያልተቀበለ ከቤተክርስቲያን ኅብረት ልጅነት ይሰደድ” ይላል ስዚህ ራሱን አዘጋጅቶ መምጣት ይገባል፡፡
☆•♥• ☆ •♥• ☆•♥• ☆
-በተጨማሪም ሰው ለቅዳሴ ሲቆም 5ቱን የሥሜት ሕዋሳቶቹን ሰብስቦ ወደ ቅዳሴው ትኩረት ሰጥቶ በንቃት ለቅዳሴ መቆም አለበት ለዚህም ዲያቆኑ በመሃል በመሃል “ለፀሎት ተነሱ” እያለ ያውጃል ምዕመኑም ራሱን በእግዚአብሔር ፊት አዋርዶ ይቅርታን በመጠየቅ “አቤቱ ይቅር በለን” ይላል፡፡ አምስቱ የስሜት ሕዋሳት የሚባሉት አይን፣ ጆሮ፣ አፍንጫ፣ እጅ እና ምላስ በአንድት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ
ለምሳሌ፡-
heart emoticon
ዐይን፡-
ካህኑ ቅዳሴን ሲቀድስ በመንበሩ አጠገብ ቆሞ ብቻ አይደለም የተለያዩ ዓይነት እንቅስቃሴዎች አሉ እነዛን እንቅስሴዎች ደግሞ ራሳቸውን የቻሉ መንፈሳዊ ምሥጢራዊ ትርጓሜዎች አሉዋቸው እነዚህን እንቅስቃሴዎች አይን ያያል ስለዚህ ዐይን ያስቀድሳል ማለት ነው፡፡
heart emoticon
ጆሮ፡-
ካህኑም ዲያቆኑም ምእመኑም በአንድትም ሆነ በተናጠል የሚያዜሙትን ዜማ፣ የሚያነቡትን ንባብ ይሰማል በዚህ ጊዜ ጆሮአችን ያስቀድሳል ማለት ነው፡፡
heart emoticon
አፍንጫ፡-
የዕጣኑን መዓዛ በማሽተት አፍንጫችን ያስቀድሳል
heart emoticon
ምላስ፡-
ቅዱስ ቁርባን በመውሰድ፣ የቅዳሴውን ፀበል በመጠጣት በዚህ ጊዜ የመቅመስ ስሜታችን ያስቀድሳል፡፡
heart emoticon
የመዳሰስ፡-
የመዳሰስ ስቀሜታችንም ስግዱ በተባለ ጊዜ፣ ወንጌል ከተነበበ በኋላ ወንጌሉን ሲስም በመጨረሻም ሰዓት የካህኑን እጅ ለመባረክ ስንስም የመዳሰስ ስሜታችን ያስቀድሳል ማለት ነው፡፡
♥♥♥
ስለዚህ አምስቱም የስሜት ሕዋሶቻችን በተሟላ መንገድ ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት መንገድ ምንድን ነው ቢባል ቅዳሴ ነው። በቅዳሴ ውስጥ የምናገኘው ትምህርት በአውደምህረት በኮርስ ከምናገኝው ትምህርት የተለየ ነው ይኽውም በዜማ የታሸ ብዙ ሊቃውንት የደከሙበት መንፈስ ቅዱስ እንደገለፀላቸው ለሰው በቀላሉ የሚገቡ ትምህርቶች ናቸው ሌላው ደግሞ ወንጌል ይነበባል መልዕክታት፣ የሐዋርያት ሥራ፣ ከዓለም አቀፍ ከሆኑ ሁሉ እና በዜማ ስለሆነ ነው እንጂ (ምስባክ) የምንለው ከመዝሙረ ዳዊትም ውስጥ ይነበባል።
+ስለዚህ 1 ሰው ቅዳሴን ሲያስቀድስ ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን ከብሉይ እስከ ሐዲስ ድረስ ይማራል ማለት ነው። ረጅም ዘመን ያስቀደሰ በሕይወቱ ውስጥ ምሁር ማለት እርሱ ነው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ከላይ እንዳልነው ነው፡፡ የመላእክትን ህይወት በምድር ላይ መኖር ማለት ነው፡፡
በቤተክርስቲያናችን ትልቁ ሱታፊ ቅዳሴን ማስቀደስ ነው ይህንንም ከራስ አልፎ ወገኖቻችን ይህን ምሥጢር እንዲሳተፉ ማድረግ ይገባል ልጆቻችን ከቅዳሴው እንዲሳተፉ ተሰጥዖ እንዲመልሱ፣ መባን ይዘው እንዲመጡ፣ ቅዳሴ ለማስቀደስ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ፣ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀበሉ ማድረግ ተገቢ ነው ያለበለዚያ የምሰጠውን የምናጣበት ደረጃ ላይ እንዳንደርስ የቀደመውን ሥርዓተ አምልኮ የሚፈፀምበት ሥርዓት እንዳይጠፋ የሚረከበን እንዳናጣ የቀደመው ለተተኪው ትውልድ ማስረከብ መቻል አለበት ሰማያዊ ምሥጢር በምድረ ከተሰራባት ከመላእክት ጋር አንድ ሆነን ፈጣሪን ከምናመሰግንባት ከቅድስት ቤተክርስቲያን ሳያናውጥ ያኑረን አሜን፡
♥♥♥
ምንጭ:- FNOTE SELAM ተዋህዶ ሐይማኖቴ ደህረ ገጽ
♥♥♥
†♥† †♥† †♥† †♥† †♥†
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም
በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ
ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ ጾሙን ጾመ ሥርየት ፤ጾመ
መድኃኒት ያድርግልን- አሜን ፡፡
†♥† †♥† †♥† †♥† †♥†
ከዋክብት የሚያመሰግኑት በስማቸውም የሚጠራቸው: የፀጋው ብዛት የማይታወቅ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው ለእኛም ግለጽልን። አሜን አሜን አሜን!!!
†♥† †♥† †♥† †♥† †♥†
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር
ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ ድ ን ግ ል
ወ ለ መ ስ ቀ ሉ ክ ቡ ር
†♥† †♥† †♥† †♥† †♥†

17/12/2015

-የቅድስት ሥላሴ ደብር አዲስ አበባ 1894—
Good Morning Addis Ababa
Local time: Friday 1:28 AM
Weather: 58°F (14°C), Wind E at 7 mph (11 km/h), 63% Humidity
መልካም የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓል ከዚህ አጭር ታሪክ ጋር እመኛለሁ።
ይህ ድንቅ ታሪካዊ ምስል የተቀረጸው ከላይ በተጠቀሰው ዓ ም አናያ ጋብሪል በተባለ የአረመን ሰፋሪ መሆኑን የሚገልጹ ሰነዶች አሉ። ታዲያ ይህ መረጃ ሥላሴወችን ደብር የመሰረቱት ቀዳማዊ ኋይለ/ሥላሴ ናቸው እየተባለ ለአያሌ አመታት ሲነገር የነበረውን ታሪክ አጠያያቂ ያደርገዋል።
የታሪክ ዋንኛው አስደሳች ገጽታ እየዋለ እያደረ የተለያዩ ምክንያቶችን ከተቀበሩበት አውጥቶ ኣያቀረበ ታምኖባቸው የተቀመጡ ጥንታዊ ትዕይንቶች ላይ አጠያያቂነት ፈጥሮ ለውይይት በር መክፈቱ ነው።
የሥላሴወችን ደብር አሐዱ ብለው የመሠረት ድንጋይ አኖረው የገነቧት የስልጣኔን የመጀመሪያ በር ከፋቹ እና ታላቁ የዘመኑ ድንቅ ክስተት አጤ ምንሊክ ናቸው።
ከጣሊያን ወረራ ጥቂት ዓመታት በፊት ቀደም ብለው ዘውድ የወረሱት ቀዳማዊ ኋይለ/ሥላሴ አልጋ ወራሽ በነበሩበት በ1920ወቹ ግማሽ ላይ በዘመናዊ የድንጋይ ስራ ይህችን ቅዱስ ደብር አነጿት። እውነተኛው የሥላሴ ቤተክርስቲያን አመሰራረት እና ግንባታ ይህ ነው።
ጥንታዊት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለዘለዓለም ትኑር።

ምንጭ Eduardo Byrono

ጠያቂ፡-ጠበል ምንድን ነው?ኦርቶዶክስ፡– ጠበል ማለት በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ህሙማን የሚፈወሱበት ተአምራት የሚደረጉበት ቅዱስ ውሃ ነው::ጠያቂ፡–መጽሀፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አለህ?...
12/12/2015

ጠያቂ፡-ጠበል ምንድን ነው?

ኦርቶዶክስ፡– ጠበል ማለት በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ህሙማን የሚፈወሱበት ተአምራት የሚደረጉበት ቅዱስ ውሃ ነው::

ጠያቂ፡–መጽሀፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አለህ?

ኦርቶዶክስ ፡- በሚገባ..ንዕማን ለምጻም እንደነበር እና በጠበል ሐይል እንደዳነ መጽሃፍ ቅዱስ ያስተምረናል
"ንዕማንም በፈረሱና በሰረገላው መጣ፥ በኤልሳዕም ቤት ደጃፍ ውጭ ቆመ። ኤልሳዕም ሂድ፥ በዮርዳኖስም ሰባት ጊዜ ታጠብ፤ ሥጋህም ይፈወሳል፥ አንተም ንጹሕ ትሆናለህ…… ወረደም፥ የእግዚአብሔርም ሰው እንደ ተናገረው በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ፤ ሥጋውም እንደ ገና እንደ ትንሽ ብላቴና ሥጋ ሆኖ ተመለሰ፥ ንጹሕም ሆነ።”2ነገሥት 5፡1-19
እንዲሁም ክርስቶስ በ ዮሐንስ 9:1-8
"ኢየሱስ ይህን ብሎ ወደ መሬት እንትፍ አለ በምራቁም ጭቃ አድርጎ በጭቃው የዕውሩን ዓይኖች ቀባና። ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ አለው… ስለዚህ ሄዶ ታጠበ እያየም መጣ።
ክርስቶስ በቃሉ ብቻ አይንህ ይብራልህ ብሎ ማዳን ይችላል ግን በብሉይ ኪዳን ህመምተኞች ይፈወሱበት ፣ተአምራት ይደረግበት የነበረው ጠበል በሐዲስ ኪዳንም የተባረከና ፈቅዶ የሰጠን ጸጋ መሆኑን ለማስረዳት “ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ” አለው፡፡

ጠያቂ ፡— ታዲያ ጠበሎች ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መጠራት ሲኖርባቸው ለምን የማርያም ጠበል፤የሚካኤል ጠበል ፤የጊዮርጊስ ጠበል ይባላል?

ኦርቶዶክስ ፡–መልሱ አጭር ነው ይኸውም በጠበሉ ቅዱሳን እንዲታሰቡበት ነው

ጠያቂ ፡–መጽሀፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አለህ?

ኦርቶዶክስ ፡- አዎ በሚገባ ..ቅድስት ቤተክርስትያን ሁሉ ነገሯ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ነው
"እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና። በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።”(ኢሳይያስ 56:4-5 )
እንዲሁም “የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው” (ምሳሌ 10:7) በሚለው መጽሀፍ ቅዱሳዊ መረጃ መሰረት በጸበሉ ቅዱሳኑ መጠራታቸው መታሰቢያቸው እንዲሆን ነው፡፡ጠበሉን የፈጠረው መድሐኒአለም ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን እና በጠበሉም አድሮ ህሙማንን የሚፈውሰው እና ተአምራትን የሚያደርገው የእግዚአብሔር ሐይል መሆኑን በደንብ እናውቃለን፡፡

ጠያቂ–አመሰግናለው ወንድሜ

ኦርቶዶክስ–ቅድስት ቤተክስትያን ለሁሉም ጥያቄ መልስ አላት፣ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የቀደመችው እውነተኛይቱ መንገድ! ለኛ ለምናምነው ፀበሉን በእምነትና በንፅህና በፈሪሃ እግዚአብሔር ከተጠቀምንበት ፈውስ እንደሚሆነን አንጠራጠም።ፀበሉ ሁላችንን ከስጋዊና ከመንፈሳዊ ደዌ ይፈውሰን! ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር!!!
ተዋህዶን እንደኔ የምትወዱና በተዋህዶ መልስ ሁሌም የምትኮሩ የተዋህዶ ልጆች መልዕክቱን share አድርጉ! እግዚአብሔር ሁላችንን በተዋህዶ ያፅናን! እኛን በጎቹን ከነጣቂ ተኩላዎች ይጠብቀን!!!

Address

Arat Kilo
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 20:00 - 08:00
Tuesday 20:00 - 08:00
Wednesday 20:00 - 08:00
Thursday 20:00 - 08:00
Friday 20:00 - 08:00
Saturday 20:00 - 08:00
Sunday 20:00 - 08:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share