Gowth Micheal Esreal

Gowth Micheal Esreal መስቀል ሀይልነ መስቀል ፅንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መዳኒተ ነፍስነ አይሁድ ክሕዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ ...

28/07/2023

✝ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ✝

✝ #ሐምሌ ፳፪ (22) ቀን።

❤ እንኳን ለታላቁ ለሆኑት ለእውነተኛ ለኢትዮጲያዊው ጻድቅ ቀን መታሰቢያ በዓልና ዝዋይ ቅዱስ ገብርኤል የካህናት ማሰልጠኛን ለመሰረቱን ካልዕ ዕረፍት ቀን መታሰቢያ በሰላም አደረሰን።



✝ ✝ ✝
✝ ኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ፦ የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ በ1875 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ፡፡ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት እንደሚሞቱ አስቀድመው መምህራቸው በትንቢት ነግረዋቸው ነበር፡፡ "አለቃ ተጠምቀ" የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን አቡነ ጴጥሮስን ጠርተው "ኀይለ ማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፣ አደራ" ብለዋቸው ነበር፡፡ ይኸውም ትንቢት ደርሶ አቡነ ጴጥሮስ በሰማዕትነት ለማረፍ በቅተዋል፡፡

✝ ብፁዕ አባታችን የጵጵስና ስማቸውን ከማግኘታቸው በፊት መመህር ኀይለ ማርያም ይባሉ ነበር፡፡ በልጅነታቸው ወላጆቻቸው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ በሃይማኖትና በምግባር ተኮትኩተው እንዲያድጉ አድርገዋቸዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዓተ ትምህርት ከንባብ እስከ ቅኔ ያሉትን ትምህርቶች በሚያስገርም ፍጥነት ከተማሩ በኋላ ወደ ቅኔው አውድማ ጎጃም በመሄድ በሸዋራ የቅኔ ትምህርታቸውን ፈጽመው መምህር ሆነዋል፡፡ የዜማውንም ትምህርት ወደ ጎንደር ሄደው ተምረዋል፡፡ በመቀጠልም ወሎ ቦሩ ሜዳ ላይ ወንበር ዘርግተው የመጻሕፍትን ምሥጢር ይመግቡ ወደነበሩት ወደ ሊቁ አካለ ወልድ ዘንድ በመሄድ ዋና ዋናዎቹን የመጻሕፍት ትርጓሜ ማለትም ብሉያትን፣ ሐዲሳትንና ሊቃውንትን በሚገባ አሒዱ፡፡

✝ ከዚህ በኋላ በ1900 ዓ.ም ወሎ አምሐራ ሳይንት ሄደው በምስካበ ቅዱሳን ገዳም ገብተው ወንበር ዘርግተው ለ9 ዓመታት ቅኔንና መጻሕፍትን አስተማሩ፡፡ በ1910 ዓ.ም ወደ ደብረ ሊባኖስ መጥተው ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸሙ፡፡ ከዚያም መምህርነት ተሹመው ደብረ መንክራት ምሁር ኢየሱስ ገዳም ሄደው ለ6 ዓመታት ካስተማሩ በኋላ በ1916 ዓ.ም እንደገና በዝዋይ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም በመምህርነት ተሹመው ለ3 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በ1919 ዓ.ም ወደ አ.አ በመምጣት የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ መምህርና በቤተ መንግሥት የግርማዊ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ የንስሓ አባት ሆኑ፡፡

✝ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በራሷ ተወላጅ ጳጳሳት ልጆቿ እንድትመራ ከ1600 ዓመታት በኋላ ስለተፈቀደላት ከዚህ በኋላ በሃይማኖታቸውና በሥነ ምግባራቸው የተመሰከረላቸው አምስት ደጋግ አባቶች ሲመረጡ አንዱ አቡነ ጴጥሮስ ነበሩ፡፡ በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የራሷን ጳጳስ ስትሾም አቡነ ጴጥሮስ ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም ጵጵስና ተሾሙ፡፡ ከዚህም በኋላ ብፁዕ አባታችን "አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቀ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዐ" ተብለው በያኔው መንዝና ወሎ ሀገረ ስብከት ተሾሙ፡፡

✝ ብፁዕ አባታችንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ቅድስት ሀገራችን በጸሎታቸው፣ ሕዝቡን በትምህርታቸው እየጠበቁ በተጋድሎ እየኖሩ ሳለ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት በ1928 ዓ.ም በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን አውጆ ሕዝቡን በግፍ ይገድል ቤተ ክርስቲያንን ያቃጥል ጀመር፡፡ በየገዳማቱ እጅግ በርካታ ካህናትና መነኮሳት ተገደሉ፣ ብርቅዬ የቤተ ክርስቲያን ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ አቡነ ጴጥሮስም ይህንን ግፍ በማየታቸው ከሀገራችን አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎታቸው ሊዋጉት ተነሡ፡፡ አባታችን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ተከትለው ወደ ሰሜን ጦር ግንባር ማይጨው ዘምተዋል፡፡ ፋሺስቱ በማይጨው በመርዝ የተደገፈ ጦርነት ከማድረጉ የተነሣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሲበታተንም ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ወደ አ.አ የተመለሱት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው ለአገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ለሠላሌ አርበኞች በሚገባ አስተምረዋል፡፡

✝ በደብረ ሊባኖስ ጫካዎች ውስጥ መሽጎ የነበረው የእነ ደጃዝማች አበራ ካሣ አርበኛ ጦር እና በሸንኮራ በኩል መሽጎ የነበረው የእነ ፍቅረ ማርያም አርበኛ ጦር እንደሁም በምዕራብ ይመራ ከነበረው የእነ ደጃዝማች አባ ነፍሶ ጦር ሦስቱም በአንድ ጊዜ ወደ መሐል አ.አ በመግት አ.አ ላይ መሽጎ የነበረውን ፋሽስትን ለመውጋት ታቅዶ የነበረው ዕቅድ በመረጃ ክፍተት ምክንያት ውጤታማ ሳይሆን ቀረ፡፡ በተለያየ ጊዜ መሐል አ.አ እየደረሱ ማለትም በመጀመሪያ የእነ ፍቅረ ማርያም አርበኛ ጦር ለብቻው በኮተቤ አድጎ የካ ሚካኤል ላይ ሲድርስ ተመቶ ተመለሰ፤ ይሄኛው እንዳለቀ ቀጥሎ የእነ አባ ነፍሶ ጦር በባቡር ጣቢያ መጣሁ ቢልም በጠላት ጦር ድካሚ ተመቶ ተመለሰ፤ መጨረሻ ላይ የእነ ደጃዝማች አበራ ካሣ አርበኛ ጦር በእንጦጦ በኩል ቢመጣም እርሱም በጠላት ጦር ተመቶ ተመለሰ፡፡

✝ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ሦስቱም የአርበኞች ጦር በመረጃ ክፍተት ምክንያት እየተመታ ወደመጣበት ሲመለስ አቡነ ጴጥሮስ አብረው ከአርበኛው ጦር ጋር መመለሱን አልፈለጉትም ይልቁንም "ብችል ጠላት በኢትዮጵያውያን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ በቅርብ ርቀት ሆኖ የሚመለከተውን ሕዝብ በማትጋት በጠላት ላይ እንዲነሣ አደርገዋለሁ ካልሆነም ደግሞ እዚሁ እሞታለሁ" በማለት አባታችን ከአርበኞቹ ተነጥለው አ.አ ቀሩ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላዋ ከተማ ያሰማራቸው ባንዳዎች አባታችንን እንዳሰቡት ሊያነቀሳቅሷቸው አልቻሉም ነበር፡፡ በመሆኑም አባታችን "የሀገሬን ሕዝብ ለጠላት እንዳይገዛ በአደባባይ አውግዤ ጠላትን ረግሜ በሰማዕትነት ባልፍ ይሻለኛል" ብለው ራሳቸውን ለጠላት አሳልፈው ለመስጠት ወሰኑና የፋሺስት ኢጣሊያ እንደራሴ ለሆነው ለራስ ኀይሉ ሄደው እጃቸውን ሰጡት፡፡ እርሱም ብፁዕ አባታችንን ወስዶ ለግራዚያኒ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አሳልፎ ሰጧቸው፡፡ ግራዚያኒም ግማሽ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንዲገደሉ ወሰነባቸው፡፡ አቡነ ጴጥሮስ በፈቃዳቸው እጃቸውን አሳልፈው ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ በሰማዕትነት እስካለፉበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሒደት ኮርየሬ ዴላሴራ የተባለው ጋዜጣ ወኪልና የምሥራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው ፖጃሌ የተባለው ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ ሰኔ 15 ቀን 1936 ዓ.ም በአዲስ አበባ በነበረ ጊዜ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ የተሰጠውን ፍርድና የተፈጸመውን የግፍ ግድያ ባየውና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ጽፎ ነበር።

✝ "ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ፡፡ በዚህ ጊዜ አቡነ ቄርሎስ የተባሉት ግብፃዊ ጳጳስ ቀርበው "ለእስክንድርያው መንበረ ፓትርያርክ ምክር ቤት ሳታሰማ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ እንዳች ነገር ማድረግ አይገባህም" ሲሉ ለግራዚያኒ ነገሩት፡፡ አቡነ ቄርሎስ ይህን ማለታቸው በዲፕሎማቲክ ደረጃ ለዓለም ለማሰማትና የአቡነ ጴጥሮስን ሕይወት ለማትረፍ አስበው ነበር፡፡ ነገር ግን ግራዚያኒ የአቡነ ጴጥሮስ የሞት ፍርድ እንኳንስ እስከ ግብጽ ከአ.አ ውጭ እንኳ ከመሰማቱ በፊት በግማሽ ቀን እንዲፈጸም መመሪያ አስተላላፈ፡፡

✝ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ✝               ✝  #ሐምሌ ፲፪ (12) ቀን። ✝ እንኳን ለከበረ መልአክ ለመላእክት አለቃ   ወደ ሆነ ወደ ሰናክሬም ...
19/07/2023

✝ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ✝

✝ #ሐምሌ ፲፪ (12) ቀን።

✝ እንኳን ለከበረ መልአክ ለመላእክት አለቃ ወደ ሆነ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት እግዚአብሔር ለላከበት ቀን ረድቶ በአንድ ሌሊት ከሰናክሬም ሠራዊት መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ አርበኞች ለገደለበት ለወራዊ መታሰቢያ በዓልና ስርያቆስ ከሚባል አገር ለሆነ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፡፡

✝ ✝ ✝
✝ በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። በዚች ቀን የፋርስ ንጉሥ ወደ ሆነ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት እግዚአብሔር ላከው ከሰናክሬም ሠራዊት ከሰናክሬም ሠራዊትም መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ አርበኞች ገደለ።

✝ ይህም እንዲህ ነው ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን በከበባት ጊዜ ሕዝቅያስንና ፈጣሪው እግዚአብሔርን እየዘለፈ ወደ ሕዝቅያስ መልእክተኞችን ላከ እንዲህም አለ "እግዚአብሔር ያድናችኋል እያለ ሕዝቅያስ አያስታችሁ ከእጄ የሚያድናችሁ ማን ነው"።

✝ የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ እጅግ አዘነ ወገኖቹንና አገሩ ኢየሩሳሌምንም ያድን ዘንድ ማቅ ለብሶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። እግዚአብሔርም ልመናውን ተቀበሎ ወደ ፋርስ ንጉሥ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ላከለት። ድንቅ ሥራንም ሠርቶ ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ሰዎች ሁሉ አዳናቸው።

✝ ስለዚህም የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል መታሰቢያ በዚች ቀን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን ረድኤቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

✝ ✝ ✝
✝ ፦ ይህም አባት ስርያቆስ ከሚባል አገሩ ነው። አባቱም አንጠረኛ ነበር አንዲት እኅቱም ነበረችው። ጎልማሳም በሆነ ጊዜ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ወደ አገረ ፈርማ ሔደ በመኰንኑም ፊት ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ከሥቃዩም ድኖ ተነሣ። መኰንኑም በእጁ ላይ ጌታችን ያደረገውን ይህን ተአምር አይቶ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋራ አመነ። በሌላ መኰንን እጅም ከሚስቱና ከልጆቹ ጋራ በሰማዕትነት ሞተ።

✝ ቅዱስ አባ ሖርን ግን ወደ እንዴናው ላከው በዚያም በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ አሠቃዩት በመንኰራኵሮችም አበራዩት ዘቅዝቀውም ሰቅለው በእሳት በአጋሉት የብረት በትር ደበደቡት። መኰንኑም ከማሠቃየቱ የተነሣ በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ የሰማዕትነትን አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 12 ስንክሳር።

+ + +
✝ " ። አመ ጽዕለተ ተወክፈ ወበትረ ኀፂን ርሱነ። ወሶበ እምኔሁ ነጸረ ዕበየ ተአምር ዘኮነ። ምስለ ብእሲቱ ወደቂቁ ከዊኖ ፍልጣነ። በእደዊሁ መኰንን አምነ"። (አርኬ) ።

+ + +
✝ ፦"ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዓውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታምእሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር"። መዝ 33፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥30-36።

+ + +
✝ ፦ "ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኀ ሠራዊቱ። ወያርብህኒ ኢድኅነ በብዝኃ ኃይሉ። ወፈረስኒ ሐሰት ኢያድኅን"። መዝ 32፥16-17። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥17-30፣ ይሁ 1፥7-14 እና የሐዋ ሥራ 10፥3-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥1-9። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ነው። መልካም የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል የወራዊ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

 !They sowed wheat that day, planted grapes and acacia olives and sacrificed the day! The Ethiopian Tzadq 17" founded mo...
16/06/2023

!

They sowed wheat that day, planted grapes and acacia olives and sacrificed the day! The Ethiopian Tzadq 17" founded monasteries! Their birthplace is in North Wolo Down and they were born in December "T"! Their father's name is Malake Mkhrusu: their mother's name is Wolete Maryam! They learned all the alphabet and interpretation of books from teacher Kirakiros and accepted the deaconship from Abune Markos who was in his time! When Jesus was a monk, he became a priest and received the episcopate from Father Moses in succession! He performed all his miracles along with many active miracles and received a promise from the Lord that will mark generations and give blessings. They rested on the 9th of April. Amen!!

!

Abune Astifase Christ

"In the name of Father, Son, Spirit, One GodAmen".  29 (29) day.Greetings to those who stood on the   for seven years  ....
06/06/2023

"In the name of Father, Son, Spirit, One God

Amen".

29 (29) day.

Greetings to those who stood on the for seven years . In addition to the things that are thought of on this day: our Lord, from our God, from our Savior, from Jesus Christ the birth_commemoration, Mengkos Isaac and Philippus_lj from King's_Eskndr_Vusuk May God help us and bless us.

+ + +: This saint's father's name is John and his mother's name is Martha, and miracles happened because of him. That is, before his mother conceived him, Saint John the Baptist came to her and told her about the birth of this Saint Simon, and he revealed to her what would happen.

When he was born and became a father of seven, he went to a monastery in Antioch. He put himself under the yoke of impurity and fought a great battle. Angels appeared to him throughout the night and taught him how to fight impurity, just as they taught him. They revealed to him the methods of killing and impurity that cannot be destroyed. He persevered and fought more than all those who wore flesh, for angels always brought him spiritual food. After much struggle, he climbed up from a pillar and stood on it for seven years.

From there, he went to another mountain and lived in the hut he built for twenty years without leaving it until the end of twenty years. After this, he climbed up from the top of a great mountain and lived on it for forty- five years. His whole life was eighty- eight years. That is, at his father's house

Seven years in the monastery of Antioch, nine years on a pillar, seven years in a dungeon, and twenty years standing on a mountain, forty- five years in total, eighty- eight years.

But no one can count his miracles. He received many essays and reprimands, and instead translated many of the church's books for monks. After that, he rested peacefully on May 29. Praise be to God and teach us through Father Simeon's prayers and may his blessings be with us forever. Amen. Source: Sanksar of May 29.

+ + +

+ + + - Eltu_Ye- Mahlet_Msbak: "Msleke is the first in the power of the day. The burden is for the saints. I gave birth to the mother and the star." Ps 109:3. The Gospel to be read is Luke 2:1-8.

+++

day's liturgical message: "Wetesatsekke watu zeimehreni. Woarhabke kiedye metheteye. Woidekme sekonaye. Ps 17:38-39. The messages to be read Gal 4:1-12, 1 John 4:9-18 Acts of Eve 12:7-12. What is sanctified The Mass is the Mass of the Three Hundred or the Holy Apostles. Happy Abune Mezrate Christ, Father Guba, Abune Simeon's holiday, Abune Aftze's Sware holiday and fasting period for all of us.

12/05/2023
12/04/2023

https://youtu.be/lfKRAWxmnzU
ወር በገባ በ29 የሚከበሩት የምስራቁ ኮከብ
የደብረ ወገጉ መናኝ
የደብረ ኪሩብ መስራች
የሐረርና የኡጋዴን መብራት
እንደ ኢያሱ በኡጋዴን ሰማይ ጸሐይን ያቆመ
እንደ ኤልያስ ሙት ያስነሳ
እንደ ሙሴ የዋቢሸበሌን ወንዝ የከፈለ።
በደብረ ወገግ እልፍ ልጆችን በመንፈስ የወለደ።

ቅዱሱ አባታችን አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ(አሰቦት) በረከቱ ይደርብን❤

" ሊቅ በሊቅነቱ ሲያስተምርኽ ሊቅ ትሆናለህ ሊቅ በህይወቱ ሲያስተምርኽ ግን ክርስቲያን ትሆናለኽ "(አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)🙏
15/04/2022

" ሊቅ በሊቅነቱ ሲያስተምርኽ ሊቅ ትሆናለህ ሊቅ
በህይወቱ ሲያስተምርኽ ግን ክርስቲያን ትሆናለኽ "

(አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)🙏

14/04/2022
12/04/2022

ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ምህረትህን ላክልንመሀሪ ነህናማረን

💐እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ
💐 እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ
💐 እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ

3 💒💐
💐 እንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ
💐 በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ

3💒💐
💐በእንተ መላዕክት መሐረነ ክርስቶ
💐 በእንተ መላዕክ መሐረነክርስቶስ
💐በእንተ መላዕክት መሐረነክርስቶስ

3 💐💒
💐 በእንተ ነቢያት መሐረነ ክርስቶስ-
💐 በእንተ ነቢያት መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ነቢያት መሐረነክርስቶስ
3 💐💒

💐በእንተ ቅዱሳን መሐረነ ክርስቶስ
💐 በእንተ ቅዱሳን መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ቅዱሳን መሐረነ ክርስቶስ

3💐💒
💐በእንተ ሰማዕታት መሐረነ ክርስቶስ
💐 በእንተ ሰማዕታት መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ሰማዕታት መሐረነ ክርስቶስ

3💐💒
💐 በእንተ ሐዋርያት መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ሐዋርያት መሐረነ ክርስቶስ
💐በእንተ ሐዋርያት መሐረነ ክርስቶስ

3 💐💒
💐እግዚኦ አምላክ
💐💒እግዚኦ አምላክ
💐እግዚኦ አምላክ

3 ክርስቶስ
💐እግዚኦ ክርስቶስ
💐 እግዚኦ ክርስቶስ
💐እግዚኦ ክርስቶስ

3 💐💒
💐ኤሎሄ
💐 ኤሎሄ
💐ኤሎሄ

3 💐💒
💐 ያድህነነ እመዓቱ ይሰውረነ በምህረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ
💐ያድህነነ እመዓቱ ይሰውረነ በምህረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ
💐ያድህነነ እመዓቱ ይሰውረነ በምህረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ

3 💐💒

💐 ስምዓነ አምላክነ ወመድሀኒነ
💐ስምዓነ አምላክነ ወመድሀኒነ
💐ስምዓነ አምላክነ ወመድሀኒነ

1 እግዚኦ መሀርነ ክርስቶስ

2እግዚኦ መሀርነ ክርስቶስ

3 እግዚኦ መሀርነ ክርስቶስ

💒እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920545857

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gowth Micheal Esreal posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share