የአማኑኤል ልጆች ye Amanueal jejoch

የአማኑኤል ልጆች ye Amanueal jejoch ye ethiopian ortodox tewahdo lijoch page

“በብሔር በሀበ ፈለስኩ ………..”እንዲል  ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየመጣ ያለው የአካባቢ ተወላጅ የሆኑ ትሩፋት አገልጋይ የማግለል እና ማሸማቀቅ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና አላስፈላጊ ደረጃ እ...
24/11/2025

“በብሔር በሀበ ፈለስኩ ………..”
እንዲል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየመጣ ያለው የአካባቢ ተወላጅ የሆኑ ትሩፋት አገልጋይ የማግለል እና ማሸማቀቅ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና አላስፈላጊ ደረጃ እየደረሰ ነው

በቅኔ ማህሌት በቤተመቅደስ በአውደምህረት አንያችሁ እያሉ ማባረር እና ከአገልግሎት ማራቅ እንደትልቅ ስራ እና መሪነት ደረጃ የሚያዩ አለቆች ፀሀፍት እና አገልጋይ ካህናት ተበራክተዋል ፧ ደጀፀኝ እያሉ የነበረውን ታሪክ ተረስቶ፧

ዛሬም ያየነው የሰማነው ይህንን ይመሰክራል እውነት የሽሮሜዳ ዲያቆናት አገልግሎት ለብዙ ደብራት አገልግሎት ትኩረት እንዲሰጡ መነሳሳት የፈጠሩ የአገልግሎት ፍቅር ያላቸው ቀናኢ የቤተክርስቲያን ልጆች ለመሆናቸው ምስክር ለመሆን አይኔን አላሽም

ይህንን አገልግሎት እና የአገልግሎት ፍቅር መደገፍ ሲገባ አናቃችሁም መባል እንደ አንድ የአዲስ አበባ ልጅ እና የችግሩ ቀማሽ እንደሆነ ሰው በጣም ያማል “የበሬውን ምስጋና ወሰደው ፈረሱ“ አለሁ አበው

-የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ውዝግብ
-የአገልጋዮች መገፋት
-የአዲስ አበባ ልጅ በአደገበት በሰራው ደብር መገፍት እና መሰደብ ባይተዋር ማድረግ ሊቆም የሚገባው መሆኑ አምናለሁ ለዚህም ከጎናችሁ ነን

እግዚአብሔር ሀይል ይሁነን

ዲ/ን ቅዱስ

12/09/2024

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የዕረፍቱ ቀን መታሰቢያ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን !!!

" እነሆ፥ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ..."
ማር. ፩፥፭ /1፥3/

✝️ መጥምቀ መለኮት ቅደለስ ዮሐንስ በእግዚአብሔር ፊት ቅዱስ ከሆኑት ካህኑ ዘካርያስ እና ቅድስት ኤልሳቤጥ ተወለደ

✝️ ገና በማኅፀን ሳለ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ፣ በመንፈስ ቅዱስ ጥበቃ ተወልዶ ያደገ አባት ነው

✝️ ወላጆቹ በልጅነቱ ስለሞቱ በበረሃ አደገ፣ ልብሱም የግመል ጠፍር ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበር

✝️ ከኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቅ የሚበልጠው ቅዱስ ዮሐንስ "መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" እያለ እየሰበከ ከበረሀ መጣ

✝️ ስለ መሲሁ እየሰበከ ብዙዎችን አስተምሮ የንስሐ ጥምቀትን በዮርዳኖስ ወንዝ እያጠመቀ ሰነበተ
✝️ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የሮማ ወታደሮችን ሳይፈራ ከሱ ኋላ ስለሚመጣው፣ ሕዝቡን በእሳትና በመንፈስ ቅዱስ ስለሚያጠምቀው የእግዚአብሔር ልጅ፤ ስለ መልካምነት ሲያስተምር ቆየ

➻ ለሕዝቡ፥ ሁለት ልብስ ያለው አንዱን ለሌላው ይስጥ፤ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ
➻ ለቀራጮች፥ ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ
➻ ለጭፍሮች፥ በማንም ግፍ አትስሩ፣ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፣ ደመወዛችሁ ይብቃችሁ

✝️ እነዚህን የመሳሰሉ መልካም ትምህርቶችን እያስተማረ ሕዝቡን ከበደል ይርቁ ዘንድ ይገስጽ ነበር

✝️ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ጌታውን ያጠመቀ፣ ክርስቶስ በወንጌሉ "ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም" ያለለት ታላቅ አባት ነው

✝️ የአራተኛው ክፍል ገዥ ንጉሥ ሄሮድስ የወንድሙን ሚስት፣ ሄሮድያዳን በማግባቱ በእግዚአብሔር ፊት ነውርን ሰርተሃልና ብሎ ወቀሰው።

✝️ ንጉሥ ሄሮድስም ይህንን ወቀሳ ተከትሎ ቅዱስ ዮሐንስን በወሕኒ አሰረው

✝️ ታዲያ በአንዲት ዕለት ይህ ዓለማዊ ንጉሥ ልደቱን ሲያከብር ሳለ የሄሮድያዳ ልጅ በዘፈን ስላስደሰተችው የምትፈልገውን እንደሚሰጣት በመሐላ ቃል ገባላት

✝️ በእናትየውም ክፉ ምክር ተመርታ የቅዱስ ዮሐንስን ራስ በወጭት ይሰጣት ዘንድ ለመነች።ንጉሡም እያዘነ የቅዱስ ዮሐንስን ራስ አስቆርጦ ለሄሮድያዳ ልጅ ሰጣት

✝️ ሐዋርያው ፣ ቅዱሱ፣ ሰባኪው ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በዚህ ቀን መስከረም ፪ ሰማዕትነትን ተቀበለ

የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ምልጃና በረከት አይለየን። በጸሎቱ ከእኛ ጋር ይሁን።





#ተዋህዶ

#ኢትዮጵያ

08/09/2024
08/09/2024

ሩፋኤል አሳድገን

❤ በዚህ በተለየ ቀን፣ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የሲመቱ መታሰቢያ ክብረ በዓል ላይ ዝናብ ይዘንባል

❤ ታዲያ በዚህን ጊዜ የአንድ አከባቢ ልጆች በዝናቡ ውስጥ ልብሳቸውን አውልቀው "ሩፋኤል አሳድገኝ" እያሉ እየዘመሩ ይሮጣሉ
➻ በጠበሉም ይጠመቃሉ

❤ በዚህ ዕለት የሚዘንበው ዝናብ ጠበል ነውና በተለያዩ እቃዎች እየተቀዳ በስነ ስርዓት ይቀመጣል።

➻ የታመመ ሰው፣ በምጥ የተቸገረች እናት ስትኖር በጠበሉ አበስ አበስ ይደረጋሉ
➻ እንደ እምነታችን መጠን እንፈወሳለን። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን የእምነታችን መጠን መሰረት ነውና

" የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል..."
ማቴ. ፲፯፥፳ /17፥20/

❤ በዚህ ቀን አዋቂዎች በጸሎትና በልመና፣ ታቦት በማንገስ ቀኑን ሲያሳልፉ ህጻናት በዝናብ እየዘመሩ ይውላሉ

❤ ይህ ከዘመን ዘመን ሲሸጋገር የመጣ ሃይማኖታዊ ብሎም ባህላዊ ተግባር በዚህ ጊዜ እየተዘነጋ እንደመጣ አስተውለናል
➻ ወላጆች በዚህ ላይ ትልቅ ሀላፊነት መወጣት ይገባናል፤ ትውፊት፣ ወግና ባህላችንን መዘንጋት አይገባምና

እኛ ግን ዛሬም "ሩፋኤል አሳድገኝ" እንላለን። በእምነት ያሳድገን።




#ተዋህዶ

#ኢትዮጵያ

07/09/2024

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን !!!

ሩፋኤል አሳድገኝ
እንደ ታላቆቼ አድርገኝ
እያልን ጳጉሜ ሶስት
ሮጠናል ያለ ፍርሃት
በልጅነት በየዋህነት
አሳድገኝ ሩፋኤል
በእምነቴ እንዳልዋልል

እንኳን አደረሳችሁ፣ አደረሰን። ሁሌም የማይዘነጋ የልጅነት የጠበል ቀን ጳጉሜ ፫፣ ቅዱስ ሩፋኤል።





#ተዋህዶ

#ኢትዮጵያ

Address

Addis Ababa
00000

Telephone

+251912610531

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአማኑኤል ልጆች ye Amanueal jejoch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የአማኑኤል ልጆች ye Amanueal jejoch:

Share