Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council EIASC is a legal entity as per proclamation 1207/2020 that represents the spiritual and developmental interests of Ethiopian Muslims at the Federal level.
(1)

It has branch offices at all the regional states.

24/05/2026

ለአረህማን እንግዶች የጤና ቅድመ ጥንቃቄ ሙያዊ ምክር በዶክተር አብዱሶመድ ሁሴን።

የአረህማን እንግዶች ማምሻውን ወደ ሚና ጉዞ ይጀምራሉ።ዙል ሂጃ 8 ኛው ቀን ወይም "የተውሊያ ቀን" (የየውሙ አት-ተርዊያህ) የሐጅ ስነስርዓት የሚጀመርበት ቀን ነው።በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮ...
24/05/2026

የአረህማን እንግዶች ማምሻውን ወደ ሚና ጉዞ ይጀምራሉ።

ዙል ሂጃ 8 ኛው ቀን ወይም "የተውሊያ ቀን" (የየውሙ አት-ተርዊያህ) የሐጅ ስነስርዓት የሚጀመርበት ቀን ነው።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሪነት 5 ሺህ 6 መቶ 13 የአረህማን እንግዶች የሀጅ ኢባዳቸውን ለመጀመር የኢህራም ልብሳቸውን ለብሰው ተልቢያህ እያደረጉ ዛሬ ምሽቱን ወደ ሚና ይጓዛሉ።

የተከበሩ የአረሕማን እንግዶች ሚና ደርሰው አምስት ወቅት እቅት ሶላታቸውን አሳጥረው በመስገድ እና አላህን በማውሳት የሚያሳልፉ ሲሆን በወጣዩ ቀን ማለዳ የሐጅ ታላቁ ስነ-ስርዓት ወደሚከናወንበት አረፋ ይጓዛሉ።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሀጅና ዑምራ ዘርፍ የአረህማን እንግዶች በሚያርፉባቸው ቦታዎች ሁሉ አስፈላጊውን አገልግሎትና መስተንግዶ እየሰጠ ይገኛል።

ግንቦት 16/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 7/1447 ዓ.ሒ

መረጃዎቹን በተከታዮቹ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የማህበራዊ የትስስር ገጾች ይከታተሉ
••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

24/05/2026

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ አብራሂም ቱፋ በሚና የአረህማነ3 እንግዶችን ማረፊያ ሲጎበኙ።

በሀጅ አገልግሎትና መስተንግዶ ዙሪያ ጥናት ሊሰራ ነው።•••••••••••••••••••••••••••••••••••••ግንቦት 14/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 7/1447 ዓ.ሒ               ...
24/05/2026

በሀጅ አገልግሎትና መስተንግዶ ዙሪያ ጥናት ሊሰራ ነው።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 14/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 7/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መዲና |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን በሐጅ አገልግሎት እርካታ ዙሪያ የዳሰሳ ጥናት መስራት ጀመረ።

ኮሚሽኑ ሁሉም የአረህማን እንግዶች የሚሳተፉበት የዲጂታል እና የወረቀት መጠይቆችን አዘጋጅቶ ሁሉም ሁጃጆች እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል።

የሀጅ አገልግሎት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለህዝበ ሙስሊሙ ከሚያቀርባቸው አገልግሎቶች ዋናው ሲሆን ይህን የአገልግሎት ዘርፍ ፍጹም እንግልት አልባ ለማድረግ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ እየሰራ ይገኛል።

ሁጃጆች እየቀረበላቸው ባለው አገልግሎትና መስተንግዶ ዙሪያ ያላቸውን ሃሳብ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ያዘጋጀውን QR ኮድ ስካን በማድረግ ወይም ለዚሁ ዓላማ ተብሎ የተዘጋጀውን የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ በመጠቀም በነጻነት መግለጽ ይችላሉ።

የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽኑ እያከናወነ ያለው ጥናት ጠቅላይ ምክር ቤቱ የጀመረውን የሀጅ አገልግሎት ማሻሻያ የለውጥ ስራ ፍጥነትና ጥራት እንዲኖረው ግብዓት ሆኖ ያገለግላል።
••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በሚና የሚገኘውን የሁጃጆች ማረፊያ ድንኳንን ጎበኙ።••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••ግንቦት 15/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 6/14...
24/05/2026

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በሚና የሚገኘውን የሁጃጆች ማረፊያ ድንኳንን ጎበኙ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 15/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 6/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሚና |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሚና የሚገኘውን የሐጃጆች ማረፊያ ድንኳን ጎበኙ።

ፕሬዝዳንቱ ማረፊያውን የጎበኙት በስፍራዉ አስፈላጊ አቅርቦቶች መሟላታቸውን ለማረጋገጥና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው።

የክብር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሀጅና ዑምራ ዘርፍ ምቹ የድንኳን ማረፊያ ማዘጋጀቱን እና በቂ የቅድመ ዝግጅት ስራ መስራቱን መመልከታቸው ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የአረህማን እንግዶች ደህንነት፣ ጤንነትና ምቾት ዋና ትኩረታችን ነው ያሉት ፕሬዝደንቱ ሁጃጆች ዒባዳቸውን ያለምንም እንግል እንዲያጠናቅቁ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።

በሚና በተደረገው ጉብኝት ላይ የኡለማ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍ፣ የአስተዳደር ጉዳዮች እና የተቋማት ልህቀት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንት ዑስታዝ ተምኪን አብዱሏሒ፣ በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሙሐመድ ሷሊህን ጨምሮ ሌሎች ሥራ አስፈፃሚዎችና የሥራ ኅላፊዎች የተገኙ ሲሆን ጉብኝቱ ፕሬዝደንቱ ለዘርፉ የሰጡትን ትኩረት ያሳያልም ተብሏል
••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

23/05/2026

ለአረህማን እንግዶች የተዘጋጁ ክሊኒኮችን አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ በስራ ኃላፊዎችና በጤና ባለሙያዎች የቀረበ ማብራሪያ።

21/05/2026

የአረህማን እንግዶች ስለተዘጋጀላቸው የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጡት አስተያዬት።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ በኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርአን ማህበር የዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድና መድረሳ የግንባታ ሂደትን ጎበኘ፡፡•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••...
21/05/2026

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ በኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርአን ማህበር የዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድና መድረሳ የግንባታ ሂደትን ጎበኘ፡፡
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 13/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 4/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ|

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን የመሩት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ልዑክ በኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርአን ማህበር የዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድና መድረሳ የግንባታ ሂደትን ጎበኘ፡፡

1980 ዓ.ል የተመሰረተው በኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርአን ማህበር የዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድና መድረሳ የነዞር እና የሒፍዝ ቂርአት ማዕከላት እንዲሁም የቁርአን ኮለጅ አሉት።

የፕሮጀክቱ ዋና ጸኃፊ ዑስታዝ አብዱልፈታህ ሸይኽ ምስጦፋ ለልዑኩ ስለ ፕሮጀክቱ ገለጻ እያደረጉ ያስጎበኙ ሲሆን አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በቀጣዩ አንድ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝና የመስጂዱን ግንባታ ደግሞ በሶስት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ ዑስታዝ አብዱልፈታህ አብራርተዋል።

ዑስታዝ አብዱልፈታህ አክለውም መድረሳው አሁን በግንባታ ሂደት ላይ ባለበት ሁኔታም የተመላላሽ ቂርአት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ጠቅላይ ምክር ቤቱ ድጋፍ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።

የልዑኩ መሪ ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን የመስጂድና መድረሳ ግንባታው በልብ ንጽህና እየተገነባ የሚገኝ በመሆኑ ሁሉም እየመጣ እንዲጎበኝና ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርግ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስም ጥሪ አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዑለማ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሸይኽ ሙሀመድዘይን ዘኽረዲን በበኩላቸው በሀገሪቱ መዲና እየተከናወነ ያለው ይህ ኢስላማዊ ማዕከል ልዩ መሆኑን ገልጸው ሁሉም የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርአን ማህበር የዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድና መድረሳ መስራች ሸይኽ ምስጦፋ አብደሏህ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ ፕሮጀክቱን ስለጎበኘ ምስጋና አቅርበዋል።

ልዑኩ በዑስታዝ አብዱልፈታህ ሸይኽ ምስጦፋ የሚመራውን አል አማና ሁቡል አይታም ወል መሳኪን አብዱልፈታህ ፋውንዴሽን በመጎብኘትም ለዑስታዝ አብዱልፈታህ የእውቅና የምስክር ወረቀትና የክብር ካባ ስጦታ አበርክቷል።

እውቅናና ሽልማቱ ወጣቱ ዳዒ ዑስታዝ አብዱልፈታህ ሸይኽ ምስጦፋ በቀጣይ የበለጠ እንዲሰሩ ለማበረታታት እንደሆነ ሸይኽ አብዱልከሪም ገልጸዋል።
••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የ2018 ዓ.ል የኢድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓልን አስመልክቶ ከፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ።በኢትዩጵያና በመላው ዓለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን...
21/05/2026

የ2018 ዓ.ል የኢድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓልን አስመልክቶ ከፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት የተሰጠ መግለጫ።

በኢትዩጵያና በመላው ዓለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሒ የኢድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆንም አላህን እንለምናለን፡፡

ዘንድሮ የሐጂ ዋና ቀን (ውቅፍ ዓረፋ) ዙል ሒጃ 9 ማክሰኞ ሲሆን ረቡዕ ዙል ሒጃ 10 (ግንቦት 19 2018 ዓ.ል) ኢደ አል አድሀ (ዐረፋ) በዓል ተከብሮ እንደሚውል እየገለጽን በዓሉን ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳት እንድናከብርም በአላህ ስም እንጠይቃለን፡፡

ፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍፍርድ ቤት

በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም የተመራው ልዑክ የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለህጻን አይነ ስውራን ተማሪዎች የአልባሳት ድጋፍ አደረገ፡፡•••••••••••••••••••••...
21/05/2026

በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም የተመራው ልዑክ የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለህጻን አይነ ስውራን ተማሪዎች የአልባሳት ድጋፍ አደረገ፡፡
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 13/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 4/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ|

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን የጠቅላይ ምክር ቤቱን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ልዑክ በመምራት የአብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም አዳሪ የህጻናት አይነስውራን ትምህርት ቤት ጎበኙ፡፡

ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንቱ የመሩት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ መጪውን የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ በአብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም አዳሪ የአይነ ስውራን ትምህርት ቤት ለሚማሩ ህፃን አይነስውር ተማሪዎች የበዓል አልባሳት ያበረከተ ሲሆን የአልባሳት ድጋፉ ህፃን አይነ ስውራኑ በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ ለማድረግ ታስቦ የተደረገ ነው።

በአልባሳት ድጋፉ ስነ ስርዓቱ ወቅት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ባስተላለፉት መልዕክት እንደ አረፋ ባሉ ታላላቅ በዓላት ልዩ ትኩረትና ድጋፍ የሚሹ ህጻናትን እና አቅመ ደካማ ወገኖችን ማሰብ፣ መደገፍና አብሮ ማክበር የእስልምና አስተምህሮ ዋና መሰረት ነው ብለዋል፡፡

ተቀዳሚ ምልትል ፕሬዝደንቱ አክለውም አዳሪ የህፃን አይነ ስውራን ትምህርት ቤቱ ህፃን አይነ ስውራንን በሁለንተናዊ መንገድ ለማብቃት ለሚያደርገው ጥረት ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በቀጣይም መሰል ማህበራዊ ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።

የአብደላህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም አዳሪ የህጻናት አይነስውራን ትምህርት ቤት አመራሮችና መምህራን የጠቅላይ ምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ለተማሪዎቹ ላሳዩት ፍቅርና ላደረጉት የበዓል አልባሳት ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን በመጎብኘት ድጋፍ በማድረግ እያበረታታ ይገኛል።
••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ከ25 ዓመታት በላይ ሳይሻሻል የቆየው የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ በአዲስ ሊተካ ነው።••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••ግንቦት 12/2018...
20/05/2026

ከ25 ዓመታት በላይ ሳይሻሻል የቆየው የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ በአዲስ ሊተካ ነው።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 12/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 3/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ|

በፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል አዲስ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።

​አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ከ25 ዓመታት በላይ ሳይሻሻል የቆየውን የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 188/1992 ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።

የሕግ ማርቀቅ ሥራው የተከናወነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በተዋቀረ ባለ 7 አባላት ያሉት የዳኞችና የባለሙያዎች ኮሚቴ ነው።

​ኮሚቴው የውጭ ሀገራት ተሞክሮዎችንና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተገኙ ጠቃሚ ግብዓቶችን በማካተት ያዘጋጀውን የመጨረሻ ረቂቅ አዋጅ እና የድንጋጌዎቹን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ለፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት እና ለእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አቅርቧል።

​ሰባት ክፍሎችን ይዞ በአዲስ መልክ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ አዋጅ የፍርድ ቤቶቹን የዳኝነት ሥልጣን፣ አደረጃጀትና አሠራር፣ የዳኞች አሿሿምና በጀት፣ እንዲሁም የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤን በአዲስ መልክ ማቋቋምን ጨምሮ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን በዝርዝር አካቷል።
••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Address

Tor Hayloch, Next To Holland Embassy
Addis Ababa
28441

Opening Hours

Monday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:00
Tuesday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:00
Wednesday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:00
Thursday 08:30 - 12:30
13:30 - 17:01
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251113729965

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council:

Share