05/11/2015
ቤተ ክርቲያን “ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን” የቤተ ክርስቲያን ምንነት ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር የተጠሩ ሰዎች ስብስብ ጉባኤ ወይም ማኅበር ናት እንጂ ሕንፃ ወይም ሌላ አይደለችም፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቤት ለመሆን እንደሕያዋን ድንጋዮች በሚገነቡ ምዕመናን የተሞላች መንፈሳዊት ሕንፃ ናት ኤፌ. 2÷20-22 1ኛ ጴጥ.2÷4-5፡፡ ብዙ ብልቶች የያዘች አንድ አካልም ናት 1ኛ ቆሮ.12÷12-27፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ ቤተ ክርስትያን የክርስቶስ አካል ነች ይህም ሁሉን በሁሉ የሚሞላ ሙላቱ የሚገለጽባት ታላቅ መንፈሳዊ አካል መሆኗን ያመለክታል ኤፌ.1÷22-23፡፡ ቤተ ክርስቲያን አንዲት የክርስቶስ አካል ናት እንጂ ብዙ አካላት አይደለችም፡፡ ለትምህርተ ሐዋርያት የታመኑ ብዙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ለአደረጃጀት እና ምዕመናንን ለመጠበቅ እንዲመች ቢኖሩም ብዙ አካላት ግን አይደሉም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ የተሠራች በመሆኗ የገሀነም ደጆች አይችሏትም ማቴ.16-18፡፡ ቤተ ክርስቲያን የማን ነች አንዳንዶች በተለምዶ ቤተክርስቲያኔ ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ ይህ ስህተት ሲሆን የቤተክርስቲያን ባለቤት ራሱ የሠራት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማቴ.16÷18 ኤፌ. 5÷23፣25-27 የሐዋ. 20÷28፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን የማንም አይደለችም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቤተክርስቲያን ሠሪ እና ራሷም ነው ኤፌ.5÷23፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቤተክርስቲያን እረኞች አለቃም ነው 1ኛ ጴጥ.5÷2-4፡፡ ስለዚህ የቤተክርስቲያን እረኞች ወይም አለቆች (መሪዎች) ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠየቂዎች ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ለቤተክርስቲያን ያለው ዓላማ ያለነውርና እድፍ የሆነች ንጽሕት ቤተክርስቲያን ለራሱ ማቅረብ ኤፌ. 5÷25-27፡፡ በቤተክርስቲያን በኩል ወንጌልን ለሰዎች በማድረስ ደቀመዛሙርት ማድረግ ማቴ.28÷18-20 የሐዋ.ሥራ 1÷7-8፡፡ ለዘላለም በመንግሥቱ የሚኖር አንድ ሰማያዊ ቤተሰብ መፍጠር ኤፌ. 2÷19 የቤተ ክርስቲያን ምግባራት ቤተክርስቲያን ፣ ወንጌልን መስበክ፣ ሥርዓተ ጥምቀትን መፈጸም፣ ያመኑትን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ማድረግ ማቴ.28÷18-20፣ ስርዓተ ቁርባንን መፈጸም 1ኛ ቆሮ.11÷23-26፣ ሥርዓተ ጋብቻን መፈጸም፣ ምእመናንን ማነጽ 2ኞ ቆሮ.11÷23-26፣ ሥርዓተ ጋብቻን መፈጸም፣ ምእምናንን ማነጽ 2ኛ ቆሮ.10÷8 እና ባልቴቶችንና ደሃ አደጎችን የመንከባከብ ትልቅ ኃላፊነት አለባት 1ኛ ጢሞ.5÷16 ያዕቆብ 1÷27፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሥልጣን ማኅበረ ምዕመናንና አገልጋዮች ለቤተክርስቲያን መሪዎች ሊታዘዙ ይገባል ዕብ.13÷17፡፡ ቤተ ክርስቲያን በሐሰት ትምህርት የተገኘውን የመለየት ሥልጣንም አላት፡፡ የቤተ ክርስቲያን አራቱ ምልክቶች “ከሁሉ በላይ የምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፡ 1. ቤተ ክርስቲያን አንዲት ናት፡፡ ክርስቶስ አንድ እንደሆነ ሁሉ በምንም ሁኔታ ይሁን ቤተ ክርስቲያን አንዲት ናት (ዮሐ.17÷21) ቤተ ክርስቲያን መከፋፈል አትችልም ከተከፋፈለችም አንድ መሆን አትችልም አንድ መሆን ካልቻለች ቤተ ክርስቲያን መሆን አትችልም፡፡ 2. ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡ ቅድስና የቤተ ክርስቲያን ተፈጥሮና ባህርይ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያንን በመቀደሰ በመምራትና በመጠበቅ ሥራ ላይ ነው፡፡ (ኤፌ.5÷26-27) ክርስቶስም በቃሉ እድፈት ነውር እንዳይኖርባት ያነጻታል፡፡ 3. ቤተ ክርስቲያን በሁሉም ስፍራ ያለች ዓለም አቀፋዊት ናት፡፡ እያንዳንዱ ቤተ ክርስቲያን የዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን አካል ናት፡፡ ( ማቴ.28÷19፣ ማር.16÷8) 4. ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት፡፡ ጌታ ለሐዋርያት አባቴ እኔን እንደላከኝ እኔም እናንተን እልካችኋለሁ (ዮሐ.20÷21) ጌታ ሐዋርያትን ደቀ መዛሙርት አድርጉ በማለት ታላቅ አደራ ሰጠቷቸዋል፡፡ በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፡፡ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ (ኤፌ.2÷20)
http://nigat.net/%e1%89%a4%e1%89%b0-%e1%8a%ad%e1%88%ad%e1%89%b2%e1%8b%ab%e1%8a%95/
ቤተ ክርቲያን “ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን” የቤተ ክርስቲያን ምንነት ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር የተጠሩ ሰዎች ስብስብ ጉባኤ ወይም ማኅበር ናት እንጂ ሕንፃ ወይም ሌላ አይደለችም፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቤት ለመሆን እንደሕያዋን ድንጋዮች በሚገነቡ…