Bahai Ethiopia

Bahai Ethiopia የኢትዮጵያ የባሃኢ ማኅበረሠብ
Welcome to the Bahá’ís of Ethiopia. This year we are celebrating the 200th year of the Birthday of Bahá'u'lláh.

በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ባሃኢዎች፥ የዘመኑ የእግዚኣብሔር መልዕክተኛና የባሃኢ ዕምነት መሥራች የሆነውን ባሃኦላህ 200ኛ ዓመት የልደት በዓል፥ ጥቅምት 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ከ200 በሚበልጡ ሀገራትና ግዛቶች፥ ከ100 ሺህ በላይ በሆኑ ከተማዎችና ክልሎች ውስጥ ያከብራሉ፡፡ የዓለም ዓቀፍ ባሃኢ ማኅበረሠብ አካል የሆነው የኢትዮጵያ የባሃኢ ማኅበረሠብም ይህን ክብረ-በዓል በደመቀ ሁኔታ የሚያከብር ሲሆን፤ በየአካባቢው የሚገኙ ባሃኢዎች ከዘመድ ወዳጆቻቸው፥ ጎረቤቶቻቸው፥ የስራ ባልደረቦቻቸው እና ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን የጥቅምት ወርን በሙሉ ልደቱን በማሰብ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ያደርጋሉ፡፡ Welcome to the Bahá’í community of Ethiopia.

17/05/2020
25/11/2017

አምላክን እንዴት ማወቅ ይቻላል?

የእግዚአብሔር መሠረታዊ ባሕርይ የማይታወቅ ቢሆንም የፀጋው ምልክት በያለበት በግልጽ ይታያል። “የመጀመሪያው ምክንያት” ሊታወቅ ባይችልም የመኖሩ ኃይል ለመላው አካላችን ይሰማናል። የሰዓሊውን ስዕል ማየት ለተቺው የሰዓሊውን ዕውቀት እንደሚያስረዳው ሁሉ፥ የሁለንተን ዓለም ዕውቀት ወይም የሰው ባሕርይ እንዲሁም የሚታዩና የማይታዩ ነገሮችን ማወቅ የእግዚአብሔርን ጥበብ ማወቅ ነው። ይህም መለኮታዊ እውነትን ለሚመረምር እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ክብር ለማወቅ ይረዳል።

“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ ጠፈሮችም የእርሱን የእጅ ሥራ ይገልጻሉ፥ ቀን ለቀን ይናገራል። ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀት ያሳያል።” (መዝ.19 1-2)

መለኮታዊ ክስተቶች

የፀሐይ ብርሃን የሚያርፍባቸው ነገሮች ሁሉ ብርሃንን አነሰም በዛ እንደሚያንጸባርቁ ሁሉ ማናቸውም ነገር የእግዚአብሔርን ጸጋ አነሰም በዛ በግልጽ ያሳያል። የከሰል ክምር አነስ፥ ድንጋይ ከፍ፥ የኖራ ድንጋይ ከዚያ በለጥ ያለ ብርሃን ያንጸባርቃሉ። ሆኖም ከነዚህ በማንኛቸውም ነፀብራቅ ደማቁን የፀሐይን መልክና ቀለም ልናይ አንችልም። ንፁሕ መስተዋት ግን ፀሐይን እራሷን እንደምናያት ያህል መልኳንና ቀለሟን ሊያሳየን ይችላል። ሌሎችም ነገሮች ስለእግዚአብሔር የሚነግሩን በዚህ ዓይነት ነው። ድንጋይ ስለመለኮታዊ ባሕርይ ሊነግረን ይችላል። አበባ በለጥ አደርጎ ይገልጽልናል። አስደናቂ ባሕርያት፥ ስሜትና፥ እንቅስቃሴ ያላቸው እንስሳት ደግሞ ከዚያም በበለጠ ይነግሩናል። በታናናሾቹ መሰል ወንድሞቻችን የፈጣሪን አስገራሚነት የሚናገሩ አስደናቂ የሰውነትክፍሎች እናገኛለን። በባለቅኔው፥ በቅዱሳን፥ በጠበብቱ ታላላቅ የእግዚአብሔር መገለጫዎች እናያለን። ሆኖም ታላላቁ ነብያትና የሃይማኖት መሥራቾች የእግዚአብሔር ፍቅርና ጥበብ ለመላው ሰው ልጅ የሚገለጥባቸው ንፁሕ መስተዋቶች ናቸው። የሌሎቹ ሰዎች መስተዋቶች በከንቱ ጥላቻና በራስ ወዳድነት ጉድፍ ቦዘዋል። ነቢያቱ ግን ንጹሕና እንከን የሌላቸው ለእግዚአብሔር ፈቃድ በሙሉ ያደሩ ናቸው። ስለዚህ የሰው ዘር ታላላቅ መምህራን ይሆናሉ።

እግዚአብሔር ሰውን በሌላ ሰው ላይ አድሮ ስለሚረዳ መለኮታዊው ትምህርትና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በእነርሱ ላይ እየሰፈነ የሰው ልጅ ሥልጣኔ ምክንያት ይሆናሉ፥ቀድሞም ሆነዋል። በሕይወት መሰላል ከፍተኛ ሥፍራ ላይ የሚገኝ ማንኛውም ሰው ከበታች ለሚገኘው ሌላ ሰው ረዳት ነው። እጅግ በጣም ከፍተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ደግሞ ለጠቅላላው የሰው ልጅ ረዳቶች ናቸው። ይህም ሁኔታ ሰዎች በተለጣጭ ክሮች እርስ በርስ እንደተሳሰሩ ዓይነት ነው። ከጠቅላላው ኅብረተሰብ መካከል አንዱ ከፍ ሲል ክሩ ይሳባል። የቀሩት ጓደኞቹ መልሰው ወደታች ሊስቡት ይሞክራሉ። ግን በተመሳሳይ ኃይል እርሱ ደግሞ ወደ ላይ ይስባቸዋል። ከፍ እያለ በሄደ ቁጥር የዓለም ሸክም የበለጠ እየከበደውና ወደታች እየሳበው ይሄዳል። ይህም በሆነ ቁጥር ከእርሱ ከፍ ብለው በሚገኙት ሰዎች በኩል የበለጠ የመለኮት ድጋፍ ያሻዋል። እነዚህን የመሳሰሉት ሰዎች ሁሉ ከፍተኛውን ሥፍራ የያዙት እነዚያ በየዘመናቸው አለአንዳች ምድራዊ ድጋፍና ጓደኛ የመላውን ዓለም ክብደት በእግዚአብሔር ኃይል የተሸከሙት ንጹሐን ነቢያት፥ መድኃኒቶችና፥ የመለኮት “ክስተቶች” ናቸው። “የኃጢአታችን ሸክም በእርሱ ላይ ነበር” የሚለው ትምህርት ሁሉንም ነቢያት ይመለከታል። እያንዳንዱ ለተከታዮቹ “ዕውነትም፥ ሕይወትም፥ መንገድም ነው።” እያንዳንዱ ለሚቀበለው ልብ ሁሉ የእግዚአብሔር በረከት መውረጃ አሸንዳ ነው። እያንዳንዳቸው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ዕድገት ባዘጋጀው መንገድ ተካፋይ ነበሩ።

02/11/2017

ባሃኡላህ (ክብረ-አምላክ)

ባሃኦላህ ከጥንት ጀምሮ እንዲመጣ ይጠበቅ የነበረው የሰዎች አሰልጣኝ፤ መምህርና ከእርሱ በፊት ከነበሩት ሁሉ የላቀ የአንድ ግሩም ጸጋ መታያ መሆኑን እንዲሁም ወንዞች በውቅያኖሶች ውስጥ እንደሚዋሐዱ ሁሉ ከአሁን በፊት ለነበሩት ሃይማኖቶችም አዋሐጅ መሆኑን ደጋግሞ በግልጽ አስታውቋል። ነቢያት የተነበዩለትና ባለቅኔዎችም ያዜሙለት፤ ሰላምም በምድር ላይ፤ በጎ ፈቃድም በሰዎች መካከል ለተባለው ጊዜ መክፈቻና ለዓለም ሕብረት መነሻ የሚሆን መሠረት ጥሏል።

እውነትን በቅንነት መፈለግ፤ የሰው ልጅ አንድነት፤ በምሥራቅም ሆነ በምዕራብ የሚገኙ ሃይማኖቶች፤ ዘሮችና ሕዝቦች አንድነት፤ የሃይማኖትና የሳይንስ መስማማት፤ የጥላቻና የከንቱ እምነት መደምሰስ፤ የሴቶችና የወንዶች እኩልነት፤ የፍትህና የጽድቅ መቋቋም፤ አንድ ጠቅላይ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት መቋቋም፤ የቋንቋዎች አንድነት፤ የግዴታ ትምህርትን ማሰራጨት፤ እነዚህና ብዙዎችም እነዚህን የመሳሰሉትም ከ19ነኛው ምዕተ ዓመት የመጨረሻው አጋማሽ በፊት ከባሃኦላህ ብዕር በመፍለቅ ቁጥራቸው ላቅ ባለ መጻሕፍትና መልእክቶች የሰፈሩ ሲሆ ከነዚህ መልእክቶች ብዙዎቹ በዚያን ጊዜ ለነበሩት የዓለም ነገሥታትና ገዥዎች የተጻፉ ናቸው።

በመጠኑና በዓላማው ወደር የሌለው መልእክቱ በሚያስገርም አኳኋን ከዘመኑ ምልክትና ፍላጎት ጋር የተስማማ ነው። አዲሶቹ ችግሮች እንደአሁኑ እጅግ የጎሉና የተወሳሰቡ ሆነው ሰውን ከዚህ በፊት ከቶ አልገጠሙትም። ለእነዚህ ችግሮች ማሸነፊያ እንዲሆኑ የቀረቡት አስተያየቶች እንደዚህ ጊዜ በዝተውና ተፋላሽ ሆነው አያውቁም። የአንድ ታላቅ የዓለም መምህር አስፈላጊነት እንደዚህ ጊዜ ጠንክሮ አያውቅም። ምናልባትም ይህን የመሰለው መምህር የመምጣት ምኞት እንደአሁን ጊዜ የተጋነነና የተረጋገጠ ሆኖ ከቶ አያውቅም።

Interview with Dr. Senay Aregawi about the Baha'i Faith in Tigrigna.
27/10/2017

Interview with Dr. Senay Aregawi about the Baha'i Faith in Tigrigna.

እምነት ባሃኢ ብ1844 ዓ.ም. ኣብ ሃገረ ኢራን ብዝተወልደ ብሃኡላህ እዩ ተጀሚሩ። ንሱ ንሙሴ፡ ንክርስቶስ፡ ነቢይ መሓመድን ንብዱሃን ተከቲሉ ካብ ኣምላኽ ዝተላእከ ናይ መወዳእታን ሓምሻይን ነቢይ እዩ ኢሎም ብሚሊዮናት ዝቑጸሩ ኣመንቱ መዓልቲ ልደት ቡሃኡላህ በብዓመቱ የኽብርሉ። ኣብ መቐለ ብ ኣመንቲ በሃኢ መበል 200 ዓመተ ልደት ቡሃኡላህ ኣብ ተኸብረሉ እዋን ብዛዕባ’ቲ እምነት ናይ ባሃኢ ኣማኒ ዝኾኑ ዶክተር ሰናይ ኣረጋዊ ዝሃቡና መብርሂ ኣብዚ ቀሪቡ ኣሎ።

23/10/2017

Security forces opened fire on a small gathering in Yemen yesterday. Persecution in Iran intensifies.

23/10/2017

Just a few glimpses of countless artistic expressions from individuals and communities around the world inspired by the occasion of the Birth of Bahá’u’lláh.

17/10/2017

እሁድ ጥቅምት 12 ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት በባሃኢ ማዕከል ስለ ባሃኢ እምነት የመግቢያ (የትውውቅ) ዝግጅት ይኖረናል። ሁላችሁም እንድትመጡ ተጋብዛችኋል። የባሃኢ ማዕከሉ ከሩዋንዳ ኤምባሲ ወደ ደሳለኝ ሆቴል በሚወ ደው መንገድ በስተቀኝ በኩል ይገኛል። በስልክ ቁጥር +251-962-08-08-08 ወይም +251-962-23-23-23 መደወል ትችላላችሁ።

እግዚአብሔርን መውደድየእግዚአብሔርን ክስተት ማወቅ ማለት፥ እርሱንም መውደድ ነው። አንዱ ያለሌላው ሊሆን አይችልም። እንደ ባሃኦላህ አነጋገር ሰው የተፈጠረበት ምክንያት እግዚአብሔርን ያውቅና ...
17/10/2017

እግዚአብሔርን መውደድ
የእግዚአብሔርን ክስተት ማወቅ ማለት፥ እርሱንም መውደድ ነው። አንዱ ያለሌላው ሊሆን አይችልም። እንደ ባሃኦላህ አነጋገር ሰው የተፈጠረበት ምክንያት እግዚአብሔርን ያውቅና ይወደውም ዘንድ ነው

ከመልእክቶቹ በአንዱ እንዲህ ይላል፦
“ለሁሉም ፍጥረት የመፈጠር ምክንያት ፍቅር ነው፥ በታወቀው ባህላዊ አነጋገር ‘ድብቅ ዕንቁ ነበርሁ ለመታወቅም ወደድሁ፤ ስለዚህ እታወቅ ዘንድ ፍጥረትን ፈጠርኩ’ ይላል።”

በኅቡአተ ቃላት እንዲህ ይላል፦
“የሕያው ልጅ ሆይ!
“አፍቅረኝ አፈቅርህ ዘንድ፥ ባታፈቅረኝ ግን የእኔም ፍቅር በምንም ዓይነት ሊደርስህ አይችልም። ይህንን እወቅ አገልጋይ ሆይ!”

“የአንጸባቂ ራዕይ ልጅ ሆይ!
“በውስጥህ የእኔን የራሴን መንፈስ እስትንፋስ ተንፍሼአለሁ፥ አፍቃሪዬ ትሆን ዘንድ፥ ለምን እኔን ትተህ ሌላ ወዳጅ ፈለግህ?”

የእግዚአብሔር አፍቃሪ መሆን! ይህ ብቻ ነው የባሃኢ ዋና የሕይወቱ መሠረተ ዓላማ። ፍጹም የደስታ ምንጭ የሆነው እግዚአብሔርን እንደዋና ቅርብ ጓደኛና ዘመድ፥ አቻ እንደሌለው ወዳጅ መውሰድ! እግዚአብሔርን መውደድ ማለት ማንንም፥ ሁሉንም መውደድ ማለት ነው። ሁሉም የእግዚአብሔር ናቸውና። እውነተኛ ባሃኢ ፍጹም አፍቃሪ ይሆናል። በንጹህ ልብ ሁሉንም ከልብ ይወዳል። ማንንም አይጠላም። የታላቁ ወዳጁን መልክ በእያንዳንዱ ፊት ማየት ስለሚችልና ምልክቱንም በያለበት ስለሚያገኘው ማንንም አይንቅም። ፍቅሩ የሃይማኖት፥ የሀገር፥ የነገድ፥ የጎሳ ወሰን አያውቅም።

ባሃኦላህ እንዲህ ይላል፦
“በቀድሞ ዘመን እንዲህ ተብሏል፥ ‘የአንድን ትውልድ አገር ማፍቀር ሃይማኖት ነው።’ የታላቁ ሥልጣን አንደበት ግን በዚህ ክስተቱ ዘመን እንዲህ ይላል፦ ‘መመካት የእርሱ ሐገሩን የሚወድ አይደለም፥ መመካት ግን ለእርሱ የሰውን ዘር ለሚወድ እንጂ’” (ታብሌት ኦፍ ዘወርልድ)“እርሱ ወንድሙን ከእራሱ የማያስቀድም የተባረከ ነው። እንዲህም ያደረገ ከባሃ ሕዝብ እንደ አንዱ ነው።” (ወርድስ ኦፍ ፓራዳይስ)http://www.bahaiethiopia.org

15/10/2017

ባሃኡላህ ሲያስተምረን የሃይማኖቶች ሁሉ ምንጭ አንድ ነው ይላል፡፡ በማንኛውም ት/ቤት የሚማረው አማኝ ዋና አላማው እውነተኛና ሩህሩህ ለመሆን ነው፡፡ ወደ ከፍተኛ ደረጃ በምንሸጋገርበት ጊዜ እነዚህ መሰረታዊ ሕግጋት አይለወጡም፡፡ ነገር ግን በአንደኛ፤ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ እነዚሁ መለኮታዊ ፀጋዎች ሁልጊዜ ይመሰገናሉ፡፡ እነዚህ እውነተኝነታቸው በጊዜ ብዛት የማይለወጥና ዘላለማዊነት ያለው መሰረቶች ናቸው፡፡ ሆኖም መሰረት ብቻውን በቂ አይደለም፡፡በዚህ መሰረት ላይ በየጊዜው የሚያስፈልጉን አንዳንድ ነገሮች መገንባት አለባቸው፡፡ ሃይማኖትም የሚያስተምረው ይህንኑን ነው፡፡ ሃይማኖት የሰውን እውቀትና ችሎታ ወደከፍተኛ ደረጃ እንዲያደርስ ያደርገዋል፡፡ ይህንንም ሲያደርግ ህግጋቱን የሚገነባው ቀደም ካሉት የእግዚአብሔር መልዕክተኞች ባገኘው እውቀት መሰረት ላይ ነው፡፡ ይህም ማለት በልጅነታችን ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ የሚሰጠው የሂሳብ ትምህርት መሰረቱን የሚያገኘው በዝቅተኛ ደረጃ ከተማርነው ትምህርት ነው፡፡

የባሃኢ እምነት ፥ ምንጩ ፥ ትምህርቶቹ እና ገቢሮቹ እንደዚሁም የባሃኢ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ

14/10/2017

የኢትዮጵያ ባሃኢ ማህበረሰብ የባሃኦላህን 200ኛ ዓመት የልደት ክብረ በዓል ለማክበር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ባሃኢዎች ብሔራዊ መንፈሳዊ ጉባኤ አስታውቋል፡፡ ይህ በዓል በዓለም ላይ ከ200 በሚበልጡ

Address

From Rwanda Embassy On The Road To Desalegn Hotel
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahai Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share