የእናት ቤተክርስቲያን ሕጋዊ መብቶች ክርክር - Eotc ሲኖዶስ

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የእናት ቤተክርስቲያን ሕጋዊ መብቶች ክርክር - Eotc ሲኖዶስ

የእናት ቤተክርስቲያን ሕጋዊ መብቶች ክርክር - Eotc ሲኖዶስ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የእናት ቤተክርስቲያን ሕጋዊ መብቶች ክርክር - Eotc ሲኖዶስ, Religious organisation, Lideta, Addis Ababa.

በጸሎትም በችሎትም ~የእግድ ውሳኔውን ለመስማት የፊታችን ረቡዕ ተቀጥሯልየፍርድ ቤቱን ውሎ ጠበቆች በዝርዝር አስረድተዋልክስ ከመመስረቱ አስቀድሞ የሰው ሕይወትና የንብረት ውድመትን ለመታደግ ይ...
07/02/2023

በጸሎትም በችሎትም
~የእግድ ውሳኔውን ለመስማት የፊታችን ረቡዕ ተቀጥሯል

የፍርድ ቤቱን ውሎ ጠበቆች በዝርዝር አስረድተዋል

ክስ ከመመስረቱ አስቀድሞ የሰው ሕይወትና የንብረት ውድመትን ለመታደግ ይቻል ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ በውግዘት ከሕብረቱ የለያቸው ግለሰቦች እና ቡድኖች የቤተክርሲያኒቱን ህጋዊ ይዞታዎችን በኃይል ለመንጠቅ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በአስቸኳይ እገዳ እንዲጣልበት ለፍርድ ቤቱ በዝርዝር ማስረዳታቸውን ገልጸዋል።

የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አሟልቶ ክሱን ለመመስረት ከሶስት ወር የማያንስ ጊዜ የሚጠይቅ መኾኑን ለፍርድ ቤቱ ያብራሩት ጠበቆቹ፤ በዚህ የጊዜ ሂደት ውስጥ በእየአንዳንዱ ቀን የሰው ሕይወት እየጠፋ እንዳይሔድ በውግዘት የተለዩት ግለሰቦች ላይ ጊዜያዊ እግድ እንዲጣል እና በተከሳሽነት ስሙ የተጠቀሰው መንግስት ህግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳታቸውን አብራርተዋል።

ፍርድ ቤቱ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ችሎቶች በተሻለ መልኩ አፋጣኝ የኾኑ አገልግሎቶችን እንደሰጣቸው እና በዛሬው የችሎት ውሎ የፍርድ ቤቱ ቀልጣፋ አገልግሎት ምስጋና ሊቸረው የሚገባ መኾኑን ጠበቆቹ ገልጸዋል።

ፍርድ ቤቱ የእግድ ጥያቄውን አስመልክቶ በርካታ ማብራሪያዎች ጠይቆ ምላሾችን መስጠታቸውን በዝርዝር አብራርተዋል።

ከ1፣30 ሰዓት በላይ የዘለቀ ማብራሪያቸውን ያደመጠው ፍርድ ቤቱ የችሎት ውሎው ቅጂ በጽሑፍ ተገልብጦ ነገ ከእኩለ ቀን አስቀድሞ እንዲደርሰው ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ በአስቸኳይ እግዱ ላይ ውሳኔ ለመስጠት የፊታችን ረቡዕ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 8፣00 ሰዓት ላይ ቀጠሮ ሰጥቶ የዕለቱ የችሎት ውሎ ማጠናቀቁን አብራርተዋል።

ከፍርድ ቤቱ ውሎ ገለጻ ባሻገር የሕግ ባለሙያዎች ቡድን አባል የኾኑት የቤተክርስቲያኒቱ ጠበቃ አቶ አያሌው ቢታኒ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ባሰተላለፈው የምሕላ አዋጅ መሰረት በጾመ ነነዌ ሶስቱ ቀናት ከቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች የተላለፈው ትዕዛዝ የጾም የጸሎት የምህላ እና ጥቁር የመልበስ ትዕዛዛት ብቻ መኾኑን አስታውሰው፤ ከዚህ ውጪ ምንም አይነት የተለየ መልዕክቶችን የማስተላለፍ ትዕዛዝ እንዳልተሰጠ አስረግጠው በማስታወስ ምዕመናኑ በታዘዘው ብቻ እንዲጸኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ከጥቁር መልበስ ትዕዛዝ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት በህጋዊ ደብዳቤ ጭምር እገዳ ለመጣል የተሞከረው እንቅስቃሴ የእምነቱን ነጻነት እና የ
ግለሰቦች ያሻቸውን የመልበስ መብት የሚጋፋ እንቅስቃሴ መኾኑን እንደ ሕግ ባለሙያነታቸው የሚታዘቡት መኾኑን ገልጸው በቀጣይ በክስ ዝርዝር ውስጥ መካተት አለመካተት ይገባዋል በሚለው ቀሪ ስራዎችን እንደሚኖሯቸው ገልጸው መግለጫውን አጠናቀዋል።

(በወፍ በረር የለቀምኳቸው በመኾኑ ቃል በቃል አልተጻፈም)

Address

Lideta
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእናት ቤተክርስቲያን ሕጋዊ መብቶች ክርክር - Eotc ሲኖዶስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share