ABBA Heylemelekot

ABBA Heylemelekot እስመ ዘይነብር በ፩ ትምህርት ሐካይ ውእቱ "መ..ወ"
በአንድ ትምህርት ብቻ የሚኖር ሰው እሱ ሰነፍ ነው።
(1)

፨ጾማችን ምን ይምሰል???*ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ             ወንትፋቀር በበይናቲነ(ቅ/ያሬድ*ጾምን እንጹም ባልንጀራችነንም እንውደድእርበርሳችንም እንዋደድ( እንተሳሰብ)ይለናል ሃይ...
24/11/2025

፨ጾማችን ምን ይምሰል???
*ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ
ወንትፋቀር በበይናቲነ(ቅ/ያሬድ
*ጾምን እንጹም ባልንጀራችነንም እንውደድ
እርበርሳችንም እንዋደድ( እንተሳሰብ)ይለናል ሃይማኖተኛው ሊቅና ጻድቅ ኢትዮጵያዊ ቅዱስ
*አዋጁ ይኽ ነው ጾሙንም ጀመርነው
ግን እኛ እንዴት ነው የምንጾመው?ሊቁ እንደነገረን
ከባልንጀሮቻችን ጋራ ተስማምተን ተግባብተን እርስበርሳችን ተፋቅረን ከቤተሰቦቻችንስ ጋር ተሳስበን ተከባብረንና ተዛዝነን ነው?
ወይንስ ዝም ብለን በተለምዶ ነው የምንጾመው?
መጠየቅ አለብን እኮ ሰዎች እንደ ባለአእምሮ
በያለንበት እንደተቋም ምን ላይ ነው ያለነው?
እንደ ሀገርስ እንዴት እየኖርን ነው ?
አሁን ለመተርጎም የሚያስቸግር ሁኔታ ነው ያለው
አንባ ጓሮ የበረከተበት ዘመን ፈታኝና መዘዘኛ
ሃይማኖተኛው ጠበኛ ፖለቲከኛው ጦረኛ
በአነስተኛ ኑሮ ውስጥ ያለው ቧልተኛ
ሥራየ ብሎ ነገር እሚያቀሳስር ሟርተኛ
በተለያየ መንገድ ኅነት ያስጨነቀው ወሬኛ
ልዩነትን የበለጠ የሚያሰፋ ቁስል የሚፈጥር እንጅ ፈዋሽ አጽናኝ ያልሆነ የተሰበሰበውን የሚበትን ተስፋ ያለውን ተስፋ የሚያስቆርጥ ሰላማዊውንም አእምሮ የሚበጠብጥ ክፉ ወሬ እያወራን እየሰማን?
እንዴት ነው መጾም ያለብን?
ሁለንተናችን እንዲጾም ወስነን ነው?
እንደሱ ከሆነ ጾማችን ውጤታማ ይሆናል
እንደ አባቶቻችን ጩኸታችን መልስ ያስገኛል
ይኽን ጾም የጾሙት አበው ነቢያት ሲሆኑ የመከራውን ዘመን አርቀውቀታል አሳልፈውበታል
የተነገረውን ተስፋም እውን ሆኖ አይተውበታልና
እኛም እራሳችነን ከክፉ ነገር ሁሉ ቆጥበንና አርቀን
አእምሮአችነንም ሰብስበን በክት ልቡና ከጾምነው
የምንሻውን ውጤት እናገኝበታለን።
ካልሆነ ግን ከንቱ እንደክማለንና ክርስቲያናዊ ምክሬ
እንደ ሊቁ ምክርም እንመጽሐፍ ቃልም እንጹመው

በሰባራው ልቤ ልጠይቅ ጥያቄ???እዳትፈርዱብኝ ግን ባለማወቄይኸንን ገዳይ ሟች ይኸንን ሟች ገዳይ!!ይህን ገዳይ መንጋ ልጠይቅ??? አጥብቄ!!!       ፨ግን የማይሞት ማን ነው???ንጉሡ እን...
05/11/2025

በሰባራው ልቤ ልጠይቅ ጥያቄ???
እዳትፈርዱብኝ ግን ባለማወቄ
ይኸንን ገዳይ ሟች ይኸንን ሟች ገዳይ!!
ይህን ገዳይ መንጋ ልጠይቅ??? አጥብቄ!!!
፨ግን የማይሞት ማን ነው???
ንጉሡ እንዳለን እሱ ባለቅኔው
አስገዳዩ ይሆን? ወይንስ ገዳዩ ነው?
መናኙ? ለማኙ ? ወይንስ ምጻተኛው ?
አድፋጩ ?አልማጩ? ሽፍታው ጉልበተኛው ?
የጸጥታው አካል ወይ ደንብ አስከባሪው ?
ሕዝብ አደራ ያለው መሪው ፊት አውራሪው?
ደጉን እየገፋ ከገዳይ ያደረው?
ወይንስ ፍትሕ አጉዳዩ ቸልተኛው ዳኛው?
ንገሩኝ እባካችሁ የማይሞተው ማን ነው???
ቄሱ ነው? ፖሊሱ?
መሪው ነው? ጳጳሱ?
ንግሥቷ?ንጉሡ?ማን ነው የማይሞተው?
የትኞቹ ናቸው ወደ አፈርነትስ የማይመለሱ?
ለሁሉም ጥያቄ የለም አይደል? መልሱ!
ሁሉም ያው ከሆኑ ሞትን ከቀመሱ
ወደ መሬት ገብተው አፈር ከለበሱ
ለምን ይሆን ታዲያ አብሮ አለመኖሩ ?
አብሮ አለማዘኑ? አብሮ አለማልቀሱ???
ስለአልገባኝ ጠየቅሁ እናንተ መልሱ

በዚህ ዘመን የሚያስፈልጉ ሰውን በሰውነቱ ብቻ የሚለኩ ለክተውም የሚያከብሩ የሚጠጉ የሚያስጠጉ አስተዋይ ታላቅ መንፈሳዊ አባት አጥተናል ለእንደነዚህ አይነት ሰዎች ይኸን ዘመን ትቶ መሄድ እረፍ...
19/10/2025

በዚህ ዘመን የሚያስፈልጉ ሰውን በሰውነቱ ብቻ የሚለኩ ለክተውም የሚያከብሩ የሚጠጉ የሚያስጠጉ አስተዋይ ታላቅ መንፈሳዊ አባት አጥተናል ለእንደነዚህ አይነት ሰዎች ይኸን ዘመን ትቶ መሄድ እረፍት ይመስለኛል ደግሞም እውነት ነው።
ለዚህ ፈተና ለበዛበትና ፈተና ለሆነ ትውልደ ግን እንዲህ አይነት ሰዎች ያስፈልጉታልና ሰው ይፍጠርልን!!!
ምንጊዜም እናከብርዎታለን ነፍስዎት በሰላም ትረፍል!!!

መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት።ሕያው ኾኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?እንዳለ ባለቅኔው ነቢይ ሊቅነት ፣ደግነት፣ርኅራኄ፣ ትዕግስት፣ጾም፣ተኀራሚነት፣ገድልና ትሩፋት የማይገድበው አዳም...
01/10/2025

መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት።
ሕያው ኾኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?እንዳለ ባለቅኔው ነቢይ ሊቅነት ፣ደግነት፣ርኅራኄ፣ ትዕግስት፣ጾም፣ተኀራሚነት፣ገድልና ትሩፋት የማይገድበው አዳም ያመጣው ሞት ከኄራን ተሐራምያን ምሁራን አንዱን ሃይማኖት ያጸኑ በምግባር የተቃኑ 318ቱ ሊቃውንት በተሰበሰቡት ታሪካዊ ቀን ነጠቀን አዛኝ፣ደግ፣ጸሎተኛ፣በዚህ ክፉ ዘመን በጸሎት ያስቡን የምንላቸው ቢለምኑ ቸሩ አምላክ የሚሰማቸው ዓለምን የተጸየፉ ፍትወት፣ስስት፣ ቁጣ፣በጥቅሉ የዚህ ዓለም ጣጣ የራቀላቸው አረጋዊ ሊቅ አጣን እሳቸው ጨረሱ ደጋጎቹ አበው ከደረሱበት ደረሱ ሲዘምሩ ሊዘምሩ ሲቀድሱም ሊቀድሱ ወደ አባቶቻቸው ገሰገሱ።
እናት ቤተክርስቲያንንና እኛ ልጆቿ ልጆቻቸውን እግዚአብሔር ያጽናን ሰው ይተካልን በረከታቸው ይድረሰን ነፍስ ይማር እንዳልል እምትጸድቀውን ነፍስ ጎረቤት ያውቃታል እንዲሉ አበው አንዳች ምክንያት አበሳም የለባቸው ምክንያተ ኃጢአት የማይገኝባቸው ፍጹም ምሁር ናቸውና ደግሜ እላለሁ የሚታካቸው ይተካልን በረከታቸው ይድረሰን ይደርብን!!!

✨በቸርነቱ ዘመንን በዘመን የሚተካ መአቱ የራቀ ምሕረቱ የበዛ ፈጣሬ ፍጥረታት ወሀቤ ሐብታት መጋቤ ዓለማት አምላከ አበው እግዚአብሔር ✨🌼 እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ 🌼በሰላም ...
10/09/2025

✨በቸርነቱ ዘመንን በዘመን የሚተካ መአቱ የራቀ ምሕረቱ የበዛ ፈጣሬ ፍጥረታት ወሀቤ ሐብታት መጋቤ ዓለማት አምላከ አበው እግዚአብሔር ✨

🌼 እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ 🌼

በሰላም አሸጋገራችሁ አዲሱ ዓመት
🌻 በሃይማኖት ጸንተን
🌻 በጸሎት በርትተን የምንቆምበት
🌸የሥራ
🌸የሰላምና
🌸የጤንነት
🌸የእርካታና
🌸የበረከትና
🌸የስኬት ዘመን
እንዲሆን በጎውን ሁሉ እመኛለሁ
መልካም አዲስ ዓመት

፨ቤተክርስቲያ አንድ ከሩቅ የሚያበራ እነቁዕ አጣች የተፈጥሮ ግዴታ ሆኖ እኒህን እንቁዕ ሁለንተናዊ ሊቅ መንፈሳዊ ረቂቅ አወቅሁ ብለው የማይታበዩ ትሁት ሳላጋንን በእውነት በምድር (በዚህ ዓለም...
18/07/2025

፨ቤተክርስቲያ አንድ ከሩቅ የሚያበራ እነቁዕ አጣች የተፈጥሮ ግዴታ ሆኖ እኒህን እንቁዕ ሁለንተናዊ ሊቅ መንፈሳዊ ረቂቅ አወቅሁ ብለው የማይታበዩ ትሁት ሳላጋንን በእውነት በምድር (በዚህ ዓለም)ያየናቸው እምትጸድቀውን ነፍስ ጎረቤት ያውቃታል እንዲሉ አምነን አፋችንን ሞልተን የምንመሰክርላቸው እውነተኛ ጻድቅ
በሥጋ ሰብእ የሚታዩ በምሥጢር ሠረገላ ዓለመ ነፍስን የቃኙ ባለአእምሮ እሩቅና ምጡቅ ነበሩ።
ሊቁ የኔታ ወልደ ትንሣኤ ዘታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም አብነት
የኔታ የተፈጥሮ ሕግ ነውና እንግዲህ ምን እንላለን ነፍስዎት በሰላም ትረፍልን!!!

18/06/2025

322 likes, 13 comments. “አሁንም በድጋሜ እዛው እስራኤል ውስጥ ዘኪዮስ ጌታን ለማየት የወጣባትን ዛፍ 🌴 ጎብኝተናል።”

17/06/2025

ከፍ ብላ ተፈጥራ
፨ከምድር ሁሉ በላይ እጅግ ልቃ ሂዳ
ብድግ ተደርጋ ከፍ ብላ ተፈጥራ!!
ታሪክ ጽፋ ይዛ ደርድራ ሰድራ
ለይታ ለይታ በክፍል በጎራ
በቃል ሳትናገር ከሩቅ ስትጣራ
አቤት ስትፈራ አቤት ስታስፈራ
አቤት ስትኮራ አቤት ስታኮራ
አየኋት ቁጭ ብየ ከኢትዮጵያውያኑ ከልጆቼ ጋራ
ጠላት ስትመክት አይቀጡ ስትቀጣ በደል ቆጥራ ሰፍራ
የዳዊትን ሀገር የአምላክን ተራራ ሞርያ ላይ ሆኜ ቆሜ ሊቶስጥራ

06/06/2025

#ኦርቶዶክስ #መዝሙርተዋህዶ #መዝሙር ሁሉም በእጅ ስልኩ እየተሰበከ ነው || በዐቢ...

09/05/2025

58 likes, 7 comments. “ልደታ ለማርያም❤ ሙሉውን ♦️በዩቲዩብ♦️ ገጻችን ያገኙታል።”

19/04/2025

✨ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሳኤሁ አግሀደ ✨
🙏 እንኳን ለዚህች ቀዳም ስዑር አደረሳችሁ።🙏

ቀዳም ስዑር ማለት የተሻረች ቅዳሜ ማለት ነው።
ለምን ተሻረች ከምን ተሻረች ካልን ደግሞ
ቀድሞ በጥንተ ፍጥረት ቸሩ አምላክ ከእለተ እሑድ እስከ እለተ ዓርብ ዓለምን ሠርቶ ጨርሶ ስነ ፍጥረቱን አጠናቆ በእለተ ቀዳም አርፏል ሢሠራት አረፈባት የሠራት ለእረፍት ነው ማለት ነው ።
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም ሰንበትየ ቅድስትየ እንተ አእረፍኩ እምኩሉ ግብርየ ብሎ ገልጧታል።
ነቢዩ ኤርምያስም ወኢታብኡ ጾረ ክቡደ ውስተ ኀዋኅዊኀ ለኢየሩሳሌም ብሎ በዚህች ቀን በእለተ ቀዳሚት ሰንበት እንዲያርፉባት እንጂ ሸክም እንኳን እዳይሸከሙባት ትዕዛዝ ሰጥቶ እናገኘዋለን።
በሐዲስ ኪዳንም ጠዋት ቀድሰን እናቆርባለን ያገኘነውን ምግበ ሥጋም በጥዋት እንመገባለን እንጅ ጾምም ቢሆን ቀዳሚት ሰንበትን አንጾምም ጾመንን አንውልም‼️
⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️
የምንጾማት በዚህ እለት ብቻ ነው ምክንያቱም ሰንበትየ ቅድስትየ ብሎ ያከበራት ስነ ፍጥረቱንም አጠናቆ ያረፈባት ጌታ በመቃብር አድሮ ስለዋለባት ውሎም ስአደረባት ቅድስቱ እናቱና ቅዱሳን ሐዋርያትም በኃዘን አድረው ስለዋሉባት ውለውም ስለአደሩባት ለእኛ ለክርስቲያኖች አምላክ መቃብር የነበረባት የኃዘን መታሰቢያ እንጅ የደስታ ቀናችን ስለአይደለች አረፍትነቷን ሽረን ጾም አድረን ጾም ስለምንውልባት ጾም ውለንም ትንሣኤው እስከሚበሠርልን ስለምናከፍልባት ቀዳም ስዑር(ስዑር የተሻች ቅዳሜ) ተብላለች።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
፨በሌላ መልኩ ደግሞ የኃጢአቱ የፍዳው የመከራው ዘመን ማለፉን የኃጢአቱ ባሕር መጉደሉን ለማብሠር አባቶቻችን (ካህናት)በርግበ ኖኅ የታየውን ለምለም ምልክት(ቄጤማ) ያድሉናል ገብረ ሰላመ በመስቀሉ በማለትም የሰላም ድምጽ ያሰሙናል።

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
1000

Telephone

+251910013333

Website

https://www.tiktok.com/@haymet_media?_r=1&_t=ZS-9453pDpkmrQ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ABBA Heylemelekot posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ABBA Heylemelekot:

Share