30/07/2026
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
ኢየሱስ ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ትንፋሹ ነው የሚል አስተምህሮ በኦጄ ቤት ሁሌ የሚዘወር የአንድ አምላክ ቀመራቸው ነው።
እኛም ከዚህ በመነሳት ጥያቄ ልንጠይቃቸው ወደድን።
የጥያቄው ክፍል የዮሐንስ ወንጌል 12:27-28 ነው።
ክፍሉ ኢየሱስ ታልፎ ልሰጥ ሰዓቱ ደርሶ ወደ አባቱ ወደ አብ ሲጸልይ አብ ደግሞ እዛው የመለሰለትን ኩነት የሚያሰቃኘን ክፍል ነው።
የሐ 12:27-28(AMH)
²⁷ "አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ።
²⁸ አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም። አከበርሁት ደግሞም አከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።"
ጥያቄ ለኦጄ
ኢየሱስ ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው ብላችሁ የአንድ አምላክ ቀመርን ስታስተምሩ ሰምተናል።
1. በዮሐ 12:27-28 በተጻፈው መሠረት የኢየሱስ ነብሱ የት ነው ያለችው?
2. የኢየሱስ መለኮትነት አብ በመሆኑ ከሆነ፡ እራሱም አብ ከሆነ ጸሎቱን ያቀረበው ወደ ማነው፤ ጸሎቱንም የመለሰለት ማነው?
3. መቼም ኢየሱስ ሰው መሆኑን አትክዱም።
የአንድ ሰው ነብስ ጸሎትን ሰምቶ ምላሽ ይሰጣልን?
4. ሰው ወደ አምላኩ ሲጸልይ የሚጸልየው በነብሱና በመንፈሱ ነው ወይስ በሥጋው ብቻ ነው?
5. ሥጋ ብቻ መጸለይ የሚችል ከሆነ የሞተ ሰው ለምን አይጸልይም?