OJ Kapho Dhoosa

OJ Kapho Dhoosa Itiyophiyu Hawaariyate Amma'nota Kaphonsa Mittu Mittunkunni Kolaanseemmo!! IYESUUSI MOOTICHIMMA DUDUMBEEMMO!! Roomu Sokka 10:9

Yesuusi Mooticha ikkinota, afiikkinni farci'rittoronna Maganu reyotenni kayisinosita wodanikkinni ammanittoro gatatto.

 ⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳ኢየሱስ ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ትንፋሹ ነው የሚል አስተምህሮ  በኦጄ ቤት ሁሌ የሚዘወር የአንድ አምላክ ቀመራቸው ነው...
30/07/2026


⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳

ኢየሱስ ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ትንፋሹ ነው የሚል አስተምህሮ በኦጄ ቤት ሁሌ የሚዘወር የአንድ አምላክ ቀመራቸው ነው።
እኛም ከዚህ በመነሳት ጥያቄ ልንጠይቃቸው ወደድን።

የጥያቄው ክፍል የዮሐንስ ወንጌል 12:27-28 ነው።
ክፍሉ ኢየሱስ ታልፎ ልሰጥ ሰዓቱ ደርሶ ወደ አባቱ ወደ አብ ሲጸልይ አብ ደግሞ እዛው የመለሰለትን ኩነት የሚያሰቃኘን ክፍል ነው።

የሐ 12:27-28(AMH)

²⁷ "አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ።
²⁸ አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም። አከበርሁት ደግሞም አከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።"

ጥያቄ ለኦጄ
ኢየሱስ ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው ብላችሁ የአንድ አምላክ ቀመርን ስታስተምሩ ሰምተናል።

1. በዮሐ 12:27-28 በተጻፈው መሠረት የኢየሱስ ነብሱ የት ነው ያለችው?
2. የኢየሱስ መለኮትነት አብ በመሆኑ ከሆነ፡ እራሱም አብ ከሆነ ጸሎቱን ያቀረበው ወደ ማነው፤ ጸሎቱንም የመለሰለት ማነው?

3. መቼም ኢየሱስ ሰው መሆኑን አትክዱም።
የአንድ ሰው ነብስ ጸሎትን ሰምቶ ምላሽ ይሰጣልን?

4. ሰው ወደ አምላኩ ሲጸልይ የሚጸልየው በነብሱና በመንፈሱ ነው ወይስ በሥጋው ብቻ ነው?

5. ሥጋ ብቻ መጸለይ የሚችል ከሆነ የሞተ ሰው ለምን አይጸልይም?

ኦጄዎች ሲያዩት አይናቸው የሚቀላው እውነታየዮሐንስ ራእይ 19:11-13 (AMH)••••••••••¹¹ ሰማይም ተከፍቶ አየሁ፥ እነሆም አምባላይ ፈረስ፥ የተቀመጠበትም የታመነና እውነተኛ ይባላል፥...
29/07/2026

ኦጄዎች ሲያዩት አይናቸው የሚቀላው እውነታ

የዮሐንስ ራእይ 19:11-13 (AMH)
••••••••••
¹¹ ሰማይም ተከፍቶ አየሁ፥ እነሆም አምባላይ ፈረስ፥ የተቀመጠበትም የታመነና እውነተኛ ይባላል፥ በጽድቅም ይፈርዳል ይዋጋልም።
¹² ዓይኖቹም እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፥ በራሱ ላይም ብዙ ዘውዶች አሉ፥ ከእርሱም በቀር አንድ እንኳ የማያውቀው የተጻፈ ስም አለው፤
¹³ በደምም የተረጨ ልብስ ተጐናጽፎአል፥ ተብሎአል።"

ዮሐንስ ያየው የእግዚአብሔር ቃል የተባለውን በደም የተረጨ ልብስ የለበሰውን በአምባላይ ፈረስ ላይ የተቀመጠው ።

ይህ የእግዚአብሔር ቃል የተባለው ኢየሱስ መሆኑን የሚነግሩን ተጨማሪ ማስረጃዎች እነሆኝ።

የዮሐንስ ወንጌል 1:1-2,14 (AMH)
••••••••••
¹ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።
² ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ።..........
¹⁴ ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።

ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ/ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ቃል እግዚአብሔር ነው። ንግግር ወይም ሥጋ ወይም ትንፋሽ አይደለም።
እግዚአብሔር ነው እንጂ።

በራዕ 19:13 ላይ የእግዚአብሔር ቃል የተባለው ማንነት ያለውን በመሆኑ፤ በዮሐ1:1 ላይ ቃል የተባለው እግዚአብሔር በመሆኑ ቃል የተባለው ንግግር አለመሆኑን ተረድተናል።

በአጭሩ ዮሐ1:17 ላይ ንግግር ሥጋ ለበሰ ሳይሆን በመጀመሪያውም ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው እግዚአብሔር ሥጋ ለበሰ ማለቱ ነው።

ከኑፋቄ ተጠበቁ!!
ሠናይ ምሽት!!

Mittu Magani ooso, xonama xonantawo!Maganu Maaronsa!!
29/07/2026

Mittu Magani ooso, xonama xonantawo!
Maganu Maaronsa!!

Who said that "galloping the hyena is a salvational miracle?😂 Jesus has been crucified for sinners, but Bishop Tekle gal...
29/07/2026

Who said that "galloping the hyena is a salvational miracle?😂

Jesus has been crucified for sinners, but Bishop Tekle galloped hyena for OJs😂

ኢየሱስ ነብሱ ብቻ አይደለም የተጨነቀው። መንፈሱም ታውኳል። የዮሐንስ ወንጌል 13:21 (AMH)••••••••••²¹ ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ...
29/07/2026

ኢየሱስ ነብሱ ብቻ አይደለም የተጨነቀው።
መንፈሱም ታውኳል። የዮሐንስ ወንጌል 13:21 (AMH)
••••••••••
²¹ ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አለ።

መንፈሴ ታወከ ማለቱ መንፈስ ቅዱስ ታወከ ማለት አይደለም።

ኢየሱስ እንደ ማንኛውም ሰው ሥጋ+ነብስ+መንፈስ ያለው በመሆኑ ፍጹም ሰው ነው። እነዚህ የሌሉት ቢሆን ሰው ባልተባለ ነበር።

ኢየሱስ ከእኛ የተለየበት ዋነኛው ነገሩ መለኮትነቱ ነው። በሰውነቱ የተገለጠው መለኮትነቱ የእራሱ ነው እንጂ የአብ አይደለም።

በመጽሐፍ ቅዱሳችን የኢየሱስ ነብሱ አብ ነው ተብሎ አልተጻፈም!!
ይህ የተጻፈው በተክሌ የቅዠት እርኩስ መጽሐፍ "ኢየሱስን ማን ይሉታል" በሚል በተጻፈ መጽሐፍ ውስጥ ነው!

29/07/2026

ወልድ ኢየሱስ ከሆነ አብ ማነው?

ወልድ (ኢየሱስ) ሰው ሆኖ ወደ ዓለም የመጣው፣ እኛን በደሙ የዋጀን እና በሥጋ የተገለጠው መለኮታዊ አካል ከሆነ፣ አብ ደግሞ የሁሉም ነገር ምንጭ፣ ወልድን ወደ ዓለም የላከው እና የወልድ (የኢየሱስ) አባት የሆነው መለኮታዊ አካል ነው!
ሁለቱም (አብ እና ወልድ) ከአንድ ከእግዚአብሔር መንፈሳዊ ባሕርይ (Essence/Substance) የተቀዱ አንድ አምላክ ናቸው፤ ነገር ግን በአካል (Personhood) ሁለት የተለዩ ናቸው።
አብ ማን እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ በሚከተሉት 3 ዋና እውነታዎች ይገልጸዋል፦
1. አብ የላከውና የአምላክነት ሁሉ ምንጭ ነው (The Sender)
መጽሐፍ ቅዱስ አብን የዓለም ሁሉ እና የዕቅድ ሁሉ መነሻ አድርጎ ያቀርበዋል።
• ኢየሱስ ራሱ ስለ አብ ሲናገር፦ "እኔ ከአብ ወጥቼ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ደግሞ ዓለምን እተዋለሁ ወደ አብም እሄዳለሁ" (ዮሐንስ 16:28) ብሏል።
• ላኪው አብ ነው፦ "እግዚአብሔር (አብ) አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወዶአልና" (ዮሐንስ 3:16)። እዚህ ላይ አብ አፍቃሪውና ልጁን የላከው አባት ነው።
2. አብ የኢየሱስ አባት ነው (The Father of the Son)
በአብ እና በወልድ መካከል ያለው ግንኙነት የ"አባት እና ልጅ" ግንኙነት ነው። ይህ ሲባል ግን አብ ወልድን ፈጠረው ማለት ሳይሆን፣ በባሕርይ፣ በፍቅር እና በክብር ዘላለማዊ የሆነ አንድነት አላቸው ማለት ነው።
• በኢየሱስ ጥምቀት ጊዜ አብ ከሰማይ ሆኖ፦ "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው" (ማቴዎስ 3:17) ሲል መስክሯል።
• ኢየሱስም ሁልጊዜ ወደ አብ ሲጸልይ፦ "አባት ሆይ..." (Abba, Father) እያለ ይናገራል።
3. አብ የማይታየውና የማይዳሰሰው መለኮት ነው
አብ በዓይን የሚታይ ሥጋ አልለበሰም። እርሱ በክብሩ በሚያበራ ብርሃን ውስጥ የሚኖር፣ ማንም ሰው ያላየውና ሊያየው የማይችለው ነው (1 ጢሞቴዎስ 6:16)።
• አብ በወልድ ተገለጠ፦ ያ የማይታየው አብ ማን እንደሆነ፣ ፍቅሩና ማንነቱ ምን እንደሚመስል ለማሳየት ወልድ (ኢየሱስ) ሥጋ ለብሶ ወደ እኛ መጣ። ለዚህ ነው ኢየሱስ "እግዚአብሔርን ማንም ያየው የለም፤ በእቅፉ ያለው አንድ ልጁ እርሱ ተረከው (ገለጠው)" ያለው (ዮሐንስ 1:18)።

እናንተ "ኢየሱስ ራሱ አብ ነው" በማለት አብንና ወልድን አንድ አካል ታደርጋላችሁ። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፦
ወልድ (ኢየሱስ) = ሰው ሆኖ የመጣውና የሞተልን አምላካችን ነው።
አብ = ወልድን የላከው፣ የኢየሱስ አባትና የፍቅር ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላካችን ነው።
ሁለቱም አካላት (ከመንፈስ ቅዱስ ጋር) በአምላክነታቸው፣ በኃይላቸውና በዘላላማዊነታቸው አንድ እግዚአብሔር እንጂ ሦስት አማልክት አይደሉም!

ኦጄዎች በየትኛው Algebra Formula ሰርተው ነው ኢየሱስን ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው ፥ መንፈስ ቅዱስ ግን ትንፋሹ ነው የሚሉን? በዮሐንስ ወንጌል 12:27 ላይ ኢየሱስ እየጸለየ²⁷ "...
28/07/2026

ኦጄዎች በየትኛው Algebra Formula ሰርተው ነው ኢየሱስን ሥጋ ነው፣ አብ ነብሱ ነው ፥ መንፈስ ቅዱስ ግን ትንፋሹ ነው የሚሉን?

በዮሐንስ ወንጌል 12:27 ላይ ኢየሱስ እየጸለየ

²⁷ "አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ።" ብሏል።

ሥጋ ወደ ነብሱ ይጸልያልን?

ኢየሱስ ፍጹም ሰው በመሆኑ እንደማንኛውም ሰው የሰውነት 3 Components አሉት። እነሱም ስጋ፣ ነብስ እና መንፈስ አሉት።

እስክ ኢየሱስ ከስጋው ወደ ነብሱ እንዴት እንደጸለየ የሚያስረዳኝ ጀግና ኦጄ አለ?

28/07/2026

ሥላሴ አጋንንት ነው ብለው እግዚአብሔርን ለሚሰድቡ በሙሉ።

ይህ በደል ቀጥታ ያስወግር እንደነበር ታውቁ ኖሯል?

ኦሪት ዘሌዋውያን 24:16 (AMH)
••••••••••
¹⁶ "የእግዚአብሔርንም ስም የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል፤ ማኅበሩም ሁሉ ይውገሩት፤ መጻተኛ ወይም የአገር ልጅ ቢሆን፥ የእግዚአብሔርን ስም በሰደበ ጊዜ ይገደል።"

እግዚአብሔር በማረ ተደፈረ😥

28/07/2026

ኢየሱስ የዘላለም አባት ነው።
አብ የኢየሱስ አባት ነው።
ስለዚህ ኢየሱስ አብ አይደለም!

Address

African Union
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when OJ Kapho Dhoosa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to OJ Kapho Dhoosa:

Shortcuts

Share