24/06/2024
1 ዮሐንስ 3፥22-23 (አመት)
ትእዛዞቹንም ስለምንጠብቅና በፊቱም ደስ የሚያሰኘውን ስለምናደርግ የምንለምነውን ሁሉ ከእርሱ እንቀበላለን።
ትእዛዙም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እንድናምንና እርሱ እንዳዘዘንም እርስ በርሳችን እንድንዋደድ ነው።
በዚህ የዮሐንስ መልእክት ውስጥ ጨምሮ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ከክርስቶስ ጋር ያለን ግንኙነት እና ለክርስቶስ ያለን ምላሽ ሌሎችን ከመውደድ ጋር የተያያዘ መሆኑን እናያለን። ግን ሌሎችን መውደድ ማለት ምን ማለት ነው? ምን ይመስላል? ክርስቶስ ያዘዘው ፍቅር በዮሐንስ 15፡12-13 እንደተመለከተው ከራስ ወዳድነት ነፃ በሆነ መስዋዕትነት ይገለጻል። ኤፌሶን 4:32 ደግሞ እርስ በርሳችን መዋደድ ርኅራኄና ይቅር ባይነት ማሳየትን ይጨምራል ይለናል። በዮሐንስ 13፡34-35 ውስጥ፣ የክርስቶስ እርስ በርስ እንድንዋደድ የሰጠው ትእዛዝ በአማኞች መካከል አንድነት እና የማህበረሰብ ስሜት ለመፍጠር እንደሆነ እናያለን። በገላትያ 5፡13 በክርስቲያናዊ አውድ ውስጥ መዋደድ የሚገለጠው በአገልግሎት እና በመደጋገፍ እንደሆነ ይነግረናል። 1ኛ ቆሮንቶስ 13፣ እርስ በርሳችን መዋደድ ማለት ትዕግሥትንና ትሕትናን በመለማመድ የራሳችንን ጉድለት በመገንዘብ ለሌሎች ጸጋን በመስጠት ነው። በክርስቲያናዊ አውድ እርስ በርስ መዋደድ ሸክምም ዕድልም ነው። ይህንን የታዘዝነውን አይነት መዋደድ ለማሳየት ለእያንዳንዱ ቀን የክርስቶስ ጸጋ ያስፈልገናል። እርስ በርሳችን መዋደድ ቃላቶቻችንን፣ ድርጊቶቻችንን እና አስተሳሰባችንን ይቀርፃል። ዛሬ ጌታ ልብሽ ወደ ፍቅር እንዲያዘነብል እጸልይልሻለሁ።
1 John 3:22-23
And whatsoever we ask, we receive of him, because we keep his commandments, and do those things that are pleasing in his sight. And this is his commandment, That we should believe on the name of his Son Jesus Christ, and love one another, as he gave us
We see in many parts of the Bible, including here in the epistle of John, that our relationship and response to Christ is heavily involved with loving others. But what does it really mean to love others? What does that look like? The love Christ commands is characterized by selflessness and sacrifice as indicated in John 15:12-13. Ephesians 4:32 tells us that loving one another involves showing compassion and forgiveness. In John 13:34-35, we see that Christ’s commandment to love one another is meant to create unity and a sense of community among believers. Galatians 5:13 tells us that love in the Christian context is demonstrated through service and support. 1 Corinthians 13, often referred to as the "Love Chapter," tells us that loving one another means practicing patience and humility, recognizing our own imperfections while extending grace to others. Loving one another in the Christian context is both a burden and a privilege; one we need the grace of Christ for each day. Loving one another shapes our words, actions, and thoughts. I pray today the Lord inclines your heart to love, as He has loved you so wholly.