Adane Getachew Ministry

Adane Getachew Ministry እምነት ፀጋ የሰጠውን ይወስዳል ...

ማነህ አንተ ??? Who are you ? ! ላላችሁኝ በሞላ ... መልሴ ይኸው... ይኸው ማንነቴ ...      MY IDENTITY IN CHRIST እኔ የኢየሱስ  አማኝ ነኝ! እማኝ ነኝ ስል...
25/05/2026

ማነህ አንተ ???

Who are you ? !

ላላችሁኝ በሞላ ...

መልሴ ይኸው...

ይኸው ማንነቴ ...

MY IDENTITY IN CHRIST

እኔ የኢየሱስ አማኝ ነኝ!

እማኝ ነኝ ስል....

ኃጢአተኛ መሆኔን አምኜ ...ለመዳን ...ጌታ ኢየሱስን ተቀብየአለሁ ... አድነኝ ብዬ....ጌታ ነህ ብዬ ኢየሱስን አምኜ መሰክሬአለሁ...ጥሪ አድርጌአለሁ በአደባባይ ጥያቄን ለእግዚአብሔር አቅርቤአለሁ ... ጌታን የምትቀበሉ እጃችሁን አውጡ ሲባል ?

እጄን አውጥቼ ጌታን በግሌ ተቀብዬአለሁ ... ጌታ ኢየሱስን ከኃጢአት ያድነኛል ብዬ አምኜ ተቀብየዋለሁ ።

ስለዚህ አማኝ ነኝ ብዬአለሁ ።ለኃጢአት ሞቶ... ለጽድቅ የተነሳውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምኜዋአለሁ ።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም አያሳፍረኝም... እርሱ ታማኝ ስለሆነ ።

ድኛለሁ።

ፀድቄአለሁ ።

አምልጫለሁ።

ሮሜ 10 (Romans)
9፤ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
10፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
11፤ መጽሐፍ፡— በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም፥ ይላልና።

የኢየሱስ አማኝ በመሆኔ ብቻ...

ከታች በዝርዝር የቀረበውን ማንነት ( IDENTITY ) አግኝቻለሁ

."የፀጋው ስጦታ"

ከዚህ በታች በዝርዝር የማቀርበው "እውነት"

እኛ አማኞች ብቻ ....

ዳግም በተወለደው መንፈስቸን ውስጥ በነፃ ያገኘናቸው በረከቶች እና የጸጋ ስጦታዎች ናቸው ።

ይህን "ነፃ ሰጦታ"( Grace )ማንም ሰው (who so ever) ኢየሱስን አምኖ እና ለኃጢአቱ ይቅርታ ጠይቆ ... አሁኑኑ ... መቀበል ይችላል....

እደግመዋለሁ!

ማንም ሰው ( who so ever ) አሁኑኑ ባለበት ቦታ እና ሁኔታ ውስጥ ሆኖ... በምንም ሁኔታ ውስጥም ቢሆንም ... አባት እግዚአብሔርን ምህረት ጠይቆ...ጌታን እርሱም ክርስቶስ ኢየሱስን ተቀብሎ ...

አሁኑኑ ... በነፃ ... የጸጋ ስጦታዎቹን መቀበል ይችላል።

"አማኝ ያልሆናችሁ"

እባካችሁ!
ዛሬ!
አሁኑኑ!
ባላችሁበት ቦታ ላይ ሆናችሁ

ይህን ከታች ያለውን ፀሎት ከእኛ ጋር በእምነት ፀልዩና ተጠቀሙ!

ወዲያውም(immediately )

ይህን የስጦታ በረከት ትቀበላላችሁ!

እግዚአብሔር ሁሌም ይወዳችኋልና!!! ፈጥኖ ያደርግላችህዋል።

በሉ ቶሎ አብረን እንጸልይ ...

ይኸው ፀሎቱ....

" እግዚአብሔር ሆይ እኔ ኀጢያተኛ ነኝ በደሌን ይቅር በለኝ ለኃጢአት ይቅርታ የፈሰሰውን የልጅህን የኢየሱስ ክርስቶስን ደም እቀበላለሁ
ጌታን አዳኜ አድርጌ በግሌ አሁኑኑ እቀበላለሁ ።

አሜን!

በልጅህ ደም ስላነፃሀኝ አመሰግናለሁ"

አሜን!

እንኳን ደስ አለን ።

ተወዳጁ (የማይወደድ የለም)

አሁን

ዕውቀት እንካ ...

ዳግም ተወልደሃል... እንዲህም ሆኖልሃል ...

ምን ሆኖልኛል ? አትልም ?

እንዲህ ሆኖልሃል....

በመንፈስህ ዳግም ተወልደሃል ።

ዳግም ስለ ተወለደው መንፈስ ደግሞ ዝርዝር እንካ...

ዳግም የተወለደው መንፈሳችን
(our born again spirit )

የእኛ በኢየሱስ ያመንን አማኞች ማንነት ( IDENTITY) ይኸው ...

እኛ አማኞች!

ኃጢያተኝነታችንን አውቀን!

ለበደላችንም ይቅርታ ለማግኘት ስንል ኢየሱስን አምነን ! የዳንን እና የፀደቅን..

ጌታንም እንደግል አዳኛችን በመቀበላችን ብቻ

ያገኘናቸው ልዩ ጥቅሞች እና ማንነት ከዚህ በታች ተዘርዝሯል...

እነሱም (የፀጋ ስጦታዎቹ) የሚከተሉት ናቸው:-

ዝርዝር ወደፊት

ጠብቁ

በዝርዝር እና በጥልቀት ይቀርባል ...

ከገጹ ላይ አትጥፉ

ወዳጃችሁ #አዳነነኝ
መንፈሳዊ ሰው ።

ሁሉ ነገር perfect አይደለምብዙውንም perfect እንዳልሆነ አየሁቃልህ ግን perfect ነው እስከአሁን ቃልህ perfect አለመሆኑን አላረጋገጥኩም ።ቃልህ ብቻ perfect .
24/05/2026

ሁሉ ነገር perfect አይደለም
ብዙውንም perfect እንዳልሆነ አየሁ

ቃልህ ግን perfect ነው
እስከአሁን ቃልህ perfect አለመሆኑን አላረጋገጥኩም ።

ቃልህ ብቻ perfect .

ደስታ happiness ደስተኛ happy ትንሽ ስለ ደስታ ለዛሬ አማርኛ እና እንግሊዘኛ እየቀላቀልን እናጥና... እንግሊዝኛ የማይመቻችሁ...ለአሁኑ ታገሱኝ happy የሚለውን እንግሊዝኛ ቃል ...
21/05/2026

ደስታ happiness
ደስተኛ happy

ትንሽ ስለ ደስታ

ለዛሬ አማርኛ እና እንግሊዘኛ እየቀላቀልን እናጥና...
እንግሊዝኛ የማይመቻችሁ...

ለአሁኑ ታገሱኝ

happy የሚለውን እንግሊዝኛ ቃል ... አማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ ... ምስጉን እያለ ተርጉሟል

ስለዚህ

ምስጉን = ደስታ = happy

ከዚህ ትርጓሜ ተነስታችሁ

ምስጉን ሲያጋጥም ደስታ እያላችሁ ተረዱ...
እንግሊዝኛ እያስቀደምኩ .. ለትርጉም አማርኛ እከተላለሁ

አማርኛ የሚመቻችሁ... እየዘለላቸሁ.... አማርኛውን ብቻ አንብቡ ።

ENJOY ?

ተወዳጆች ሆይ

ፊትን የሚያበራ ደስታ ...
ፊትን ፏ የሚያደርግ ደስታ...
ሥጋን የሚፈውስ ደስታ የሚሆነው ...

ከውስጥ ...

ከልብ ... የተገኘ ደስታ ነው ...

እንደ መግቢያ

ደስ ያላት ልብ መልካም መድሀኒት ናት .... ደግ ትሰራለች..

ደስ ያላት ልብ...

A merry heart doeth good like a medicine

Proverbs 17 (KJV) - ምሳሌ
22: A merry heart doeth good like a medicine: but a broken spirit drieth the bones.

ደስ ያላት ልብ ልክ እንደ መድኃኒት ናት...

ምሳሌ 17 (Proverbs)
22፤ ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት፤ ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች።

ሲጀመር

የልብ ደስታ .. ሁልጊዜ እንደ ግብዣ ነው...

ደስ ያለው ልብ... ፊትን ያበራል

ደስ ያለው ልብ... ፊትን .. ፏ ! ያደርጋል

ምሳሌ 15 (Proverbs)
13፤ ደስ ያለው ልብ ፊትን ያበራል፤ በልብ ኀዘን ግን ነፍስ ትሰበራለች።
14፤ የአዋቂ ልብ እውቀትን ይፈልጋል፤ የሰነፎች አፍ ግን በስንፍና ይሰማራል።
15፤ ልቡ የሚያዝን ሰው ዘመኑ ሁሉ የከፋች ናት፤ የልብ ደስታ ግን ሁልጊዜ እንደ ግብዣ ነው።

Proverbs 15 (KJV) - ምሳሌ
13: A merry heart maketh a cheerful countenance: but by sorrow of the heart the spirit is broken.
14: The heart of him that hath understanding seeketh knowledge: but the mouth of fools feedeth on foolishness.
15: All the days of the afflicted are evil: but he that is of a merry heart hath a continual feast.

ወሳኝ ጥያቄ

ልብ እንዴት ትደሰት ?

ልብ እንዴት በደስታ ትሞላ ?

ዋው

አስተውላችህዋል

በቁሳቁስ ደስታም ህይወትም አይገኝም...

ጌታ ኢየሱስ ነው እኮ ያለው...

ቁሳቁስ (ንብረት)(ገንዘብ) ትርፉ ለቁራሌው ነው... [እኔ አልኩ]

ቅራቅንቦ ቢበዛ .... ህይወትን አይሆንም ።

ጌታ እንዲህ አለ...

የገንዘብ(የንብረት) ብዛት .... ህይወትን አይሰጥም...

ሉቃስ 12 (Luke)
15፤ የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፥ ከመጐምጀትም ሁሉ ተጠበቁ፡ አላቸው።

የንጉሥ ጀምስ ትርጉም

For a man's life consisteth not in the abundance of the things which he possesseth....

Luke 12 (KJV) - ሉቃስ
15: And he said unto them, Take heed, and beware of covetousness: for a man's life consisteth not in the abundance of the things which he possesseth.

ታዲያ

Happy ማነው ? happy እንዴትስ ይኮናል ?

ቁልፍ ጥያቄ ?

ልብ እንዴት ትደሰት ?

Psalms 144 (KJV) - መዝሙር
15: Happy is that people, that is in such a case: yea, happy is that people, whose God is the LORD.

እግዚአብሔር አምላኩ የሆነ ሕዝብ ደስተኛ ነው...

መዝሙር 144 (Psalms)
15፤ እንደዚህ የሚሆን ሕዝብ የተመሰገነ ነው፤ እግዚአብሔር አምላኩ የሆነ ሕዝብ ምስጉን ነው።

ሌላ ደስተኛ ... ይኸው

Psalms 146 (KJV) - መዝሙር
5: Happy is he that hath the God of Jacob for his help, whose hope is in the LORD his God:

አምላክ ረዳቱ የሆነ ተስፋውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ደስተኛ ነው...

መዝሙር 146 (Psalms)
5፤ የያዕቆብ አምላክ ረዳቱ የሆነ ተስፋውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምስጉን ነው፤

ደሞ ሌላ ደስተኛ እንካችሁ

Proverbs 3 (KJV) - ምሳሌ
13: Happy is the man that findeth wisdom, and the man that getteth understanding.

ጥበብን የሚያገኝ ሰው ደስተኛ ነው...
ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ ሰው ደስተኛ ነው ....

ምሳሌ 3 (Proverbs)
13፤ ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤

ታስታውሱ እንደሁ

የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ...

ስለዚህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ደስተኛ ነው ።

ተወዳጆች ሆይ

ድሀን የሚረዳ ... ደስታን ያገኛል

ለድሃ የሚራራ ደስተኛ ነው ...

Proverbs 14 (KJV) - ምሳሌ
21: He that despiseth his neighbour sinneth: but he that hath mercy on the poor, happy is he.

ምሳሌ 14 (Proverbs)
21፤ ባልንጀራውን የሚንቅ ይበድላል፡ ለድሀ ግን የሚራራ ምስጉን ነው።

ወዳጄ

ኧረ ሌላም ደስተኛ አለ...

Proverbs 16 (KJV) - ምሳሌ
20: He that handleth a matter wisely shall find good: and whoso trusteth in the LORD, happy is he.

በእግዚአብሔር የታመነ ደስተኛ ነው ...

ምሳሌ 16 (Proverbs)
20፤ ቃልን የሚያዳምጥ መልካም ነገርን ያገኛል፤ በእግዚአብሔር የታመነ ምስጉን ነው።

ተወዳጆች

እንካችሁ የመጨረሻ ደስተኛ ..

Proverbs 28 (KJV) - ምሳሌ
14: Happy is the man that feareth alway: but he that hardeneth his heart shall fall into mischief.

ሁልጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ሁልጊዜ በልቡ ደስተኛ ነው...

ምሳሌ 28 (Proverbs)
14፤ ሁልጊዜ የሚፈራ ሰው ምስጉን ነው፤ ልቡን የሚያጸና ግን በክፉ ላይ ይወድቃል።

ስንሰበስበው

የዛሬው መልዕክት ሲሰበሰብ እንዲህ ይመጣል

አማኝ ሆይ

ደስታህን ከልብ ... ከውስጥ የሚመነጭ አድርገው... የእግዚአብሔርን ደስታ ተቀብለህ ልብህን በደስታ ሙላ... ልብ ውስጥ ያለ ደስታ ... ሁልጊዜ የሚበላ ... የሁሌ ግብዣ ነው ። በየቀኑ የምትመገበው የደስታ ግብዣ ከልብህ አግኝ ...

ደስታን ውጭ ዓለም ላይ አትፈልግ... ትርፉ ድካም ነው ...የዓለም ደስታ ውጫዊ እና ጊዜያዊ ነው ...

ወዳጄ

የልብ ደስታ ነው ለሥጋህ መድሃኒት

የዓለም ደስታ ... የቁሳቁስ ደስታ ፣ የመጠጥ ደስታ ፣ የሃሺሽ ደስታ ፣ የአደንዛዥ ዕፅ ደስታ ፣ የዝሙት ደስታ ... የዝና ደስታ .... ከወዘተ የተገኘ ደስታ ... አይጠቅምህም... ለሥጋህ መድሃኒት አይሆንህም ... ተወው

ልብን የሚሞላውን ... ልብ ላይ የሚበቅለውን... የእግዚአብሔርን ደስታ ፈልግ...የልብ ደስታ ነው ፊትህን ሁሌ የሚያበራ ...ሥጋህን ሁሌ የሚፈውስ ...

አሁን ወሳኝ ጥያቄ የሚሆነው ....

ልብ እንዴት ትደሰት ? የሚለው ነው

ወዳጄ

ልብህ እንድትደሰት

ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር... ያኔ ደስታ ልብህን ይሞላል

ልብህም... መድሃኒት ትሆናለች ... ፊትህንም ታበራለች...

Proverbs 15 (KJV) - ምሳሌ
13: A merry heart maketh a cheerful countenance: but by sorrow of the heart the spirit is broken.

ምርቃት

ጭማሪ እንካ ...
ወዳጄ

ልባችንን ማስደሰት ያለብን ለምን መሰለክ ?

ይኸውልህ

በልብ ያለ ደስታ ...እንደ ሁልግዜ ግብዣ... ነው ... ሁሌ መዥረጥ እየተደረገ የሚበላ

Proverbs 15 (KJV) - ምሳሌ
15: All the days of the afflicted are evil: but he that is of a merry heart hath a continual feast.

ስንደመድመው

ደስታን የተሞላች ልብ
ልክ... እንደ መድሃኒት ናት ...

ደግ (መልካም) ትሰራለች ።

እንቀምረው ...FORMULA

ደስታ የተሞላች ልብ = መድሃኒት

Proverbs 17 (KJV) - ምሳሌ
22: A merry heart doeth good like a medicine: but a broken spirit drieth the bones.

ደስ ያላት ልብ
መልካም መድሃኒት ናት ...

ስለዚህ

ልብህን ደስታ ሙላት

መድሃኒት እንድትሆን

ምሳሌ 17 (Proverbs)
22፤ ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት፤ ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች።

ወገን

የልብ ደስታ ላይ እንስራ ።

ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት እንዋል ! ድሀን እንርዳ...በእግዚአብሔር እንታመን... እግዚአብሔርን አምላካችን እናድርግ... ጥበብን እናግኝ ... ማስተዋልን ገንዘባችን እናድርግ...

ብቻ

የልብ ደስተኛ ለመሆን ...

ተግተን...

መጽሐፍ ቅዱስ እናንብብ

በእግዚአብሔርም ሥርዓት እንመራ

የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፥ ልብንም ደስ ያሰኛል....

መዝሙር 19 (Psalms)
7፤ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤ ነፍስን ይመልሳል፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል።
8፤ የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፥ ልብንም ደስ ያሰኛል፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል።
9፤ የእግዚአብሔር ፍርሃት ንጹሕ ነው፤ ለዘላለም ይኖራል፤ የእግዚአብሔር ፍርድ እውነትና ቅንነት በአንድነት ነው።
10፤ ከወርቅና ከክቡር ዕንቍ ይልቅ ይወደዳል፤ ከማርና ከማር ወለላም ይጣፍጣል።
11፤ ባሪያህ ደግሞ ይጠብቀዋል፤ በመጠበቁም እጅግ ይጠቀማል።

አሜን ።

ወዳጃችሁ #አዳነነኝ
ከ ልዑል መጠጊያ
From the secret place of the most High
---------------------------------------------

ነፍስን ለማዳን እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ ! እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ ! ወገኖቼ ! በዚህ ዓለም እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ ... ነፍስን ከስጋዊ ምኞት ለማዳን እና ለማራቅ ...
20/05/2026

ነፍስን ለማዳን እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ !

እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ !

ወገኖቼ ! በዚህ ዓለም እንግዳና መፃተኛ መሆንን ማሰብ ... ነፍስን ከስጋዊ ምኞት ለማዳን እና ለማራቅ ይጠቅማል...እና እንደ እንግዳ ኑሩ ...

እንግዳ... ሰው ቤት እንግድነት ገብቶ... እንዴት እንደሚያድር ... እንዴት እንደሚውል አስቡ... እንግዳው...በሚያድርበት ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ... ምን ግድ ይሰጠዋል ? ምንም... ያገባዋል ? አያገባውም ... አድሮና ተጫውቶ ሲሄድ ሁሉን ጥሎ መሄድ አይደለ ድርሻው ? አዎን ይህንን ነው የሚያደርገው...

አንተም በዚህ ምድር ልክ እንደዚሁ ኑር ።

እንግዳ ነን ለዚህ ዓለም ብለህ አስበህ ... እንደ እንግዳ እና መፃተኛ ( እንደ ስደተኛ ) ኑር ።

ስደተኛ ከሆንክ ...የዛ ያስጠጋህ አገር ፖለቲካ ያገባሃል እንዴ ? አያገባህም... ባለቤት ነኝ ብለህ ትሳተፋለህ ? አትሳተፍም...

እንግዲህ አማኝ ከሆንክ ... ልክ እንዲሁ ....የዚህ ዓለም ጉዳይ አይመለከትህም... አሜን በል።

ወዳጄ ! በኢየሱስ አዳኝነት ካመነክ ... ልክ ጌታ ኢየሱስን ስትቀበል ....ዓለምን ክጃለሁ ብለህ ስትናዘዝ ... በልብህ ያመንከውን በአፍህ ስትናገር ... ከዓለም ድነሃልና.... ደስ ይበልህ ።

ወዳጄ እህቴ ! አስተውይ .... ከዚያች ...ከዳንሽባት ቀን ጀምሮ ... አንቺ ! ለዚች ዓለም...እንግዳና መፃተኛ ነሽ.... ።

1 ጴጥሮስ 2 (1 Peter)
11፤ ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤

አሜን ።

ተወዳጆች

ይሄውላችሁ

የእምነት አርበኞች ...እንግዶች እና መፃተኞች እንዲሆኑ ታመኑ...አንፈልጋትም አሉ ይህችን ምድር...

እንዲህ ብለው ተናዘዙ እዚህ ምድር ምንም የለንም አሉ ... እዚህ ምድር ምንም አንፈልግም ብለው ተናዘዙ ...በላይ ያለውን አሰቡ ... አባቶች የላይኛውን ናፈቁ።

ዕብራውያን 11 (Hebrews)
13፤ እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ።

Hebrews 11 (KJV) - ዕብራውያን
13: These all died in faith, not having received the promises, but having seen them afar off, and were persuaded of them, and embraced them, and confessed that they were strangers and pilgrims on the earth.

አሜን ።

አዎን

አባቶች ! በግልፅ ተናዘዙ ... ይህችን ዓለም ናቁ ... አንፈልጋትም ብለው ተናገሩ .... የምትመጣዋን ናፈቁ። በግልጽም ከላይ የምትመጣ... የምንጠብቃት አገር አለችን አሉ ።

14: For they that say such things declare plainly that they seek a country.

ስለዚህች ምድር... አስበው ቢሆን ኖሮ .... ስለወጡባት ምድር በነፍሳቸው ተጨንቀው ቢሆን ኖሮ ... ጉድ ይሆኑ ነበር።

15: And truly, if they had been mindful of that country from whence they came out, they might have had opportunity to have returned.

በላይ ያለውን ስለ አሹ ... ስለ ፈለጉ ...desire ስለ አደረጉ ። ተጠቀሙ።...ነፍሳቸውን ከስጋዊ ምኞት አራቁ....

ተወዳጆች እኛም ነፍሳችንን ለማዳን ከእነርሱ እንማር ?! በ'ላይ ..ያለውን ብቻ እናስብ።

16: But now they desire a better country, that is, an heavenly: wherefore God is not ashamed to be called their God: for he hath prepared for them a city.

መደምደሚያ

በዚህች ዓለም ... እንግዳና መፃተኛ እንደሆኑ ማሰብ ... በዚህች ምድር እንደ አልፎ ሂያጅ መኖር ... ጥቅም አለው

ምክንያቱም

ሥጋዊ ምኞት ...ነፍስ ላይ ... ከሚያደርሰው ...አደጋና ጉዳት .... ነፍስን ለማዳን እና ለማስመለጥ ያስችላል።

ጌታዬ ! እንዲህ ብሏል....

ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ ብሏል ...

ይሄው ምስክር

ማቴዎስ 6 (Matthew)
19፤ ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤
20፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤
21፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና።

አሜን !

አማኞች ! ምን አለን እዚህ ?
እኔ ምንም ብዬአለሁ ።

ወዳጅ አንቺስ ምን አለሽ ? ምን ቀረሽ እዚ ?... ምንስ ትያለሽ ?

ወዳጅ ! አንተስ ምን ትናዘዛለህ ?

ተወዳጆች

አስተውሉ

አማኞች ሆይ ! በሰማይ ታላቅ ሕያው ተስፋ ቀርቶልናል ! እድለኞች ነን ።

ደስ ይበላችሁ !

ያመነ ብቻ ... እዚህ ምድር ...እንግዳ እና መፃተኛ ነኝ ይበል !

ልክ እንደኔ እንደ ወዳጃችሁ አዳነ ...

" እንግዳ እና መጻተኛ ነኝ "

ኢየሱስ ጌታ ነው !

እግዚአብሔር ፍቅር ነው!

ወዳችሁ አካፍሉ [ Like & Share ]

ወዳጃችሁ #አዳነነኝ
ከ ልዑል መጠጊያ
From the secret place of the most High
---------------------------------------

ለስጋው የሚዘራ that soweth to his flesh Galatians 6 (KJV) - ገላትያ8: For he that soweth to his flesh shall of the flesh reap co...
19/05/2026

ለስጋው የሚዘራ that soweth to his flesh

Galatians 6 (KJV) - ገላትያ
8: For he that soweth to his flesh shall of the flesh reap corruption; but he that soweth to the Spirit shall of the Spirit reap life everlasting.

በገዛ ስጋው ላይ የሚዘራ ... ከገዛ ስጋው ያፈራል...

አሁን ዋናው ጥያቄ

አንድ ሰው

ለስጋው ከዘራ...

ስጋው ምን እንዲያፈራ ያደርገዋል ? የሚለው ነው ።

ገላትያ 6 (Galatians)
8፤ በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።

ጳውሎስ

በስጋዬ ማለት በflesh ምንም በጎ ነገር የለም አለ...

Romans 7 (KJV) - ሮሜ
18: For I know that in me (that is, in my flesh,) dwelleth no good thing: for to will is present with me; but how to perform that which is good I find not.

ሮሜ 7 (Romans)
18፤ በእኔ ማለት በሥጋዬ በጎ ነገር እንዳይኖር አውቃለሁና፤ ፈቃድ አለኝና፥ መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም።

በሥጋህም ውስጥ ያለ ነገር ዝርዝር እንካ

ቆላስይስ 3 (Colossians)
5፤ እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው።

አየህ ...

በስጋህ ላይ ብትዘራ ... ሥጋህ በጎ ነገር ስለሌለው .... ያው የምታፈራው በጎ ያልሆነ ነገር ነው ማለት ነው ።

ነገር ግን

ወንድሜ

ለመንፈሰ

ወይም

በመንፈስ (Spirit) ላይ ብትዘራ ግን ከመንፈስ
መልካም እና ሕይወት የሆነ ነገር ሁሉን ታፈራለህ....

Galatians 6 (KJV) - ገላትያ
8: For he that soweth to his flesh shall of the flesh reap corruption; but he that soweth to the Spirit shall of the Spirit reap life everlasting.

ወዳጄ !

ምረጥ....

የስጋ ፍሬ እና የመንፈስ ፍሬ ይኸውልህ...

እንደዘራኸው የምታጭደው ?

በመጀመሪያ

የስጋ ፍሬ ይኸው...

ገላትያ 5 (Galatians)
19፤ የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥
20፤ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥
21፤ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።

በመቀጠል

የመንፈስ ፍሬ ይኸው...

22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

ወዳጆች

የእስከ አሁኑን ስንደመድመው

ምን ላይ እንዝራ ?

ወይም

ለየትኛው እንዝራ ?

Flesh ላይ ወይስ Spirit ላይ እንዝራ?

ለ~flesh ወይስ ለ~Spirit እንዝራ ?

ገላትያ 6 (Galatians)
9፤ ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።
10፤ እንግዲያስ ጊዜ ካገኘን ዘንድ ለሰው ሁሉ ይልቁንም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎች መልካም እናድርግ።

በአጠቃላይ

አማኞች ሆይ !

ቆላስይስ 3 (Colossians)
7፤ እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ።
8፤ አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ።
9፤ እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥
12፤ እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።
13፤ እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
14፤ በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።

አዎን ፍቅርን ልበሱት ...

ምክንያቱም

አንደኛ

1 Corinthians 13 አማ - 1ኛ ቆሮንቶስ
4: ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤
5: የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤
6: ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤
7: ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል።
8: ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል።

አሜን እያላችሁ

ሁለተኛ

ገላትያ 6 (Galatians)
7፤ አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤
Galatians 6 (KJV) - ገላትያ
7: Be not deceived; God is not mocked: for whatsoever a man soweth, that shall he also reap.

አሜን ።

ስለዚህ

ድምዳሜው

ምን ላይ እንደምትዘሩ ምረጡ ።

ለማን እንደምትዘሩ ምረጡ ።

የምትዘሩትንም ዘር ምረጡ ።

አሜን በሉ።

አሜን ጻፉ ።

ኢየሱስ ጌታ ነው !

እግዚአብሔር ፍቅር ነው!

ወዳችሁ አካፍሉ [ Like & Share ]

ወዳጃችሁ #አዳነነኝ
ከ ልዑል መጠጊያ
From the secret place of the most High
---------------------------------------

18/05/2026
የአዲስ ኪዳን አገልጋይ ማነው ?ለአገልግሎት ማን አበቃው ?2 Corinthians 3 (አማ) - 2 ቆሮንቶስ6: እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን...
18/05/2026

የአዲስ ኪዳን አገልጋይ ማነው ?
ለአገልግሎት ማን አበቃው ?

2 Corinthians 3 (አማ) - 2 ቆሮንቶስ
6: እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።

የደኽንነት ጥሪ እና ጸሎት ኢየሱስን ያመነ... ከኃጢአት  ባርነት:.. እና ከዘላለም  ከሞት አምልጧል... እንኳን ደስ አላችሁ ... ያመናችሁ.። ተወዳጆች ያመነ  ከእንግዲህ ወዲያ የምስራቹ...
17/05/2026

የደኽንነት ጥሪ እና ጸሎት

ኢየሱስን ያመነ... ከኃጢአት ባርነት:.. እና ከዘላለም ከሞት አምልጧል...

እንኳን ደስ አላችሁ ... ያመናችሁ.።

ተወዳጆች

ያመነ ከእንግዲህ ወዲያ የምስራቹን ቃል ( ወንጌሉን ) ይመስክር

በኢየሱስ ያላመነ ደግሞ ... አሁኑኑ በኢየሱስ ይመን ... እና የዘላለምን ህይወት ይቀበል ! ከዘላለም ሞት በኢየሱስ እምነት ያምልጥ !!!

አሜን በሉ ።

ወገኖቼ

አሁን ያመነ.... ወይም አሁን ለማመን የፈለገ ...

ይሄን ከታች ያለውን የንስሐ ፀሎት አብረን እንፀልይ

የንስሐ ፀሎት

ሰው ሆይ

ድምፅህን ከፍ አድርገህ ፀልይ:

ኢየሱስ ሆይ! እኔ ኃጢያተኛ ነኝ... ኃጢያቴን ደምስስልኝ... በደምህ እጠበኝ...

ከኃጢአቴም አንፃኝ!

በአንደበቴ

አንተ ጌታዬና አዳኜ መሆንህን እመሰክራለሁ! ኢየሱስ ሆይ! አንተን የግሌ አዳኜ እና ጌታዬ አድርጌ በዚህች ሰዓት እቀበላለሁ !

በልቤም

ስለኃጢያቴ እንደሞትክ! እግዚአብሔርም ከሞት እንዳስነሳህ አምናለሁ!

በሕያው ቃልህም በማመን ደህንነትን አሁን እቀበላለሁ !

ኢየሱስ ሆይ! ከኃጢያቴ ስላነፃኸኝ አመሰግንሃለሁ !

ልጅህ ስላደረግከኝ እና ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ ።

በኢየሱስ ስም ፀለይኩ ።

አሜን

ሰው ሆይ

የእግዚአብሔር ውድ ሆይ ❣️

ኢየሱስን አሁን የተቀበልክ ሆይ

እንኳን ደስ አለህ !

በዚህች ሰዓት በሰማይ መልዓክቶች ተደስተዋል... አንተ የንስሃ ፀሎት በማድረግህ በሰማይ እግዚአብሔር ባለበት ታላቅ ደስታ ሆኖአል👏🏽👏🏽👏🏽(ሉቃስ 15: 10)

ሕይወትህን ለኢየሱስ ክርስቶስ በመስጠትህ በዚህች ሰዓት የቃሉ እውነት በመንፈስህ ውስጥ ይፈፀማል!

አሁን ዳግም ተወልደሀል! በውስጥህም አዲስ ፍጥረት ሆነሃል (2ኛ ቆሮንቶስ 5:17)

የእግዚአብሔር ውድ ሆይ ❣️

በአካባቢህ

በሥራ ቦታህ
በመኖሪያ ሰፈርህ

ካሉ በኢየሱስ ከሚያምኑ ወገኖች ጋር ህብረት አድርግ ... አብር ።

ኢየሱስ ጌታ ነው!
ኢየሱስ ያድናል!

አሜን።

 #የምስራቹን  #ማብሰር !የገፃችን ወዳጆችና አባሎች.... ዛሬ በጌታ ፍቅር አንድ ትዕዛዝ እንሰጣችህዋለን ... አንድ ለየት ያለ ነገር እናደርጋለን ...  ያመነበት ብቻ ይሳተፍ ! እኔ አ...
16/05/2026

#የምስራቹን #ማብሰር !

የገፃችን ወዳጆችና አባሎች....

ዛሬ በጌታ ፍቅር አንድ ትዕዛዝ እንሰጣችህዋለን ... አንድ ለየት ያለ ነገር እናደርጋለን ...

ያመነበት ብቻ ይሳተፍ !

እኔ አለሁ ይበል !

ወዳጆች !

እስቲ ለምታገኙት አንድ ሰው ወንድ /ሴት [ለሁሉም ሰው ፣ ለማንኛውም ሰው ] በሥራ ቦታ ፣መንገድ ላይ ፣ ቤታችሁ ውስጥ ፣ መዝናኛ ሥፍራ ሊሆን ይችላል ....

ብቻ ለአንድ ሰው የሚከተሉትን ሚስጥሮች ንገሩ ...

1) ዛሬም በእግዚአብሔር ተወዳጅ መሆኑን !

2) ዛሬም እግዚአብሔር ምርጥ ነገሬ የሚለው እሱን / እሷን መሆኑን !

3) ዛሬም በጌታ የተወደደች መሆኗን !

4) ዛሬም እግዚአብሔር አንድ ልጄን እስከ መስጠት በሚደርስ ፍቅር እወደዋለሁ/ እወዳታለሁ እያለ መሆኑን!

5) ዛሬ በምንም ሁኔታ ውስጥ ይሁን ገና ጠላት እየሆነ እንኳን ... ከፍቅሩ የተነሳ... ለእሱ/ለእሷ ሲል ኢየሱስ .... ነፍሱን እንደሰጠ ንገሩ/ንገሯት ....

6) ብቻ "እንዲያው" ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እግዚአብሔር ይወደናል ብላችሁ ንገሩ ...
.. ንገሩ ፤ አውሩ ፤ መስክሩ ፤ በአጠቃላይ

ተወዳጆች !

የምስራቹን ለአንድ ሰው አብስሩ !

ዛሬም

እግዚአብሔር እንደሚወደው አስታውሱት !!!

እግዚአብሔር ፍቅር ነው!

ወዳችሁ አካፍሉ [ Like & Share ]

#ወዳጃችሁ #አዳነነኝ !

Address

Addis Ababa

Telephone

+251704444004

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adane Getachew Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Adane Getachew Ministry:

Share