Alebachew Worku

Alebachew Worku This page is about the Ethiopian Orthodox Tewahido Church Doctrine and other spiritual wisd

"ሦስት ነገሮች ያስደንቁኛል!አባቱ የማይቀድመው ልጅ፤እናቱን የፈጠረ ሕፃን፤ፈጣሪዋን የወለደች እናት"ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት...
07/01/2026

"ሦስት ነገሮች ያስደንቁኛል!
አባቱ የማይቀድመው ልጅ፤
እናቱን የፈጠረ ሕፃን፤
ፈጣሪዋን የወለደች እናት"
ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ አደረሳችሁ!

   የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ነው። በዚህ መጽሐፍ የተቀመጡት የግርጌ ማስታወሻዎች መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ የተጻፈበትን አውድ ለመረዳት መንገድ ጠራጊ ናቸው።አጠቃላይ የገጽ ...
17/06/2025



የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ነው። በዚህ መጽሐፍ የተቀመጡት የግርጌ ማስታወሻዎች መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ የተጻፈበትን አውድ ለመረዳት መንገድ ጠራጊ ናቸው።

አጠቃላይ የገጽ ብዛት 1,868 ሲሆን በኢትዮጵያ ገበያ ላይ ይገኛል (ዋጋው ውድ ቢሆንም)።

መጽሐፉን ለማግኘት https://t.me/MekaneTibeb1/1200
ይጎብኙ፤ ቤተሰብ ይሁኑ!

📖 መጽሐፍ ቅዱስ "ዲያብሎስም ረዥም ወደ ሆነ ተራራ አውጥቶ የዓለምን መንግሥታት ሁሉ  #በቅጽበት አሳየው" ሉቃስ 4:5 በማለት ዲያቢሎስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮን...
27/05/2025

📖 መጽሐፍ ቅዱስ "ዲያብሎስም ረዥም ወደ ሆነ ተራራ አውጥቶ የዓለምን መንግሥታት ሁሉ #በቅጽበት አሳየው" ሉቃስ 4:5 በማለት ዲያቢሎስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንጦስ ሲፈትነው እንዲህ እንዳደረገና ቀጥሎ ጥዠየማሰናከያ ጥያቄውን እንደጠየቀው ያስረዳናል።

✍️ በዚህ ምንባብ ላይ ትኩረት ላደርግ የፈለኩት #በቅጽበት #አሳየው የሚሉትን ቃላት ነው። ያው መጽሐፍ ላይ ስለተጻፈ ብቻ ጴ*ን*ጤውም ተሐ*ድሶውም ሳያቅማማ አሜን ብሎ ይቀበለዋል። ነገር ግን ስለ ቅዱሳን መላእክት ምልጃ ኦርቶዶክሳውያን ስናስተምር "እንዴት አንድ መልአክ በአንዴ ሁሉም ቦታ ይገኛል" በማለት ትችታቸውን ይዘረጋሉ። በእርግጥ ፍጡራን ስለሆኑ ውስንነት እንዳለባቸው ይታወቃል። ነገር ግን እግዚአብሔር በሰጣቸው ጸጋ መገኘት ባለባቸው ቦታ ሁሉ በቅጽበት ለመገኘት የሚከለክላቸው ነገር እንደሌለ በዚህ የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል እንመለከታለን።

✝️ ታዲያ ዲያቢሎስ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ #በቅጽበት የዓለምን ነገስታት አሳየው የሚለውን (ያውም ለዓለሙ ሁሉ አስገኝ አምላክ) አሜን ብሎ ተቀብሎ፤ ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ሲባል መቃወም የጤና ይሆን?🤔🤔 ነው ቅዱሳን መላእክት ከዲያብሎስ ያነሱ ናቸው ብለው ነው የሚያስቡት?

https://t.me/MekaneTibeb1

📖 ሥዕለ ሥሉስ ቅዱስን በተመለከ አንዳንድ ሰዎች "መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም" ዮሐ 1:18 የሚለውን በማንሳት እግዚአብሔርን ማን አይቶት ሥላሴን ሳላችሁ የሚሉ አሉ ...
03/05/2025

📖 ሥዕለ ሥሉስ ቅዱስን በተመለከ አንዳንድ ሰዎች "መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም" ዮሐ 1:18 የሚለውን በማንሳት እግዚአብሔርን ማን አይቶት ሥላሴን ሳላችሁ የሚሉ አሉ (ምንም እንኳ እግዚአብሔር ለሰወች የተገለጠበት ጊዜ ቢኖርም)።

✍️ በአጠቃላይ ቅዱሳት ሥዕላትን በተመለከተና የኢትዮጵያውያን አሳሳልን በተመለከተ ከዚህ በፊት አስተማሪ የሆኑ ስራወችን የሰራልን መምህራችን ዲ/ን ሄኖክ ወልደ ኃይሌ በዚህ ቪዲዮ ደግሞ ሥዕለ ሥሉስ ቅዱስን በተመለከ ከበቂ ማብራሪያ ጋር አቅርቦልናል።

📖✍️ ማየት ከመጀመራችን በፊት ማስታወሻ ብንይዝ እንጠቀምበታለን።

የቅድስት ሥላሴ ሥዕል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ውስጥ ማእከላዊ ቦታ ይሠጠዋል:: ይህ ትምህርት የዚህን ሥዕል የትመጣ ከዓለም አቀፋዊ ቅኝት ጋር የሚዳስስ ት.....

በሊቀ ሊቃውንት Simur Alamrew 'Alexia'ጸጋ የበዛለት ወንድማችን፦ ቤዛነትን ተነተነው፤አተነነው፡፡ ዱሮም ስብከት እንጂ ትምህርት አይኾንለት ነበር፡፡ እውነት!ይኽን የማያምን ሰው ካ...
30/04/2025

በሊቀ ሊቃውንት Simur Alamrew

'Alexia'

ጸጋ የበዛለት ወንድማችን፦ ቤዛነትን ተነተነው፤አተነነው፡፡ ዱሮም ስብከት እንጂ ትምህርት አይኾንለት ነበር፡፡ እውነት!

ይኽን የማያምን ሰው ካለ ስለ ክርስቶስ ፈራጅነት እሰብካለኹ ብሎ ኤርምያስ 7:25ን ያብራራበትን ትምህርት መስማት ይችላል፡፡ እዚኽ ምዕራፍ ላይ "በእየዕለቱ እየማለድሁ ባሪያዎቼን ነቢያትን ሁሉ ልኬባችሁ ነበር" ይላል ቃሉ፡፡ ታዲያ ይኽ ወንድማችን 'እየማለድሁ' የሚለውን ቃል እያማለድኩ ብሎ ነው የተረዳው፡፡ ቃሉ ግን ከማማለድ ጋር አይገናኝም፡፡ ልክ እንደዚኽ እንደቤዛነት ትምህርት ከኪሱ እያወጣ ቃሉን ለሚያብራራ ሰው ግን ይገናኛል😉

አኹን ደግሞ ከቤታችን የተቀበለውን ኳስ ይዞ እንዲኽ አለ፦
"ቤዛዊተ ዐለም ለመባል መስቀል ላይ መሞት አለባት"፡፡ ኧረ ቀስ! መስቀል ላይ ሳይሰቀሉ ቤዛ/መድኀኒት የተባሉ ሰዎች አሉ፡፡
ከእነዚኽ ሰዎችም አንዱ Joshua ነው፡፡ በግእዝ ኢያሱ። በመጀመሪው ቋንቋ ኢያሱና ኢየሱስ ተመሳሳይ ስም ነው ያላቸው፡፡ ኹለቱም ጆሹዋ ይባላሉ፡፡ የስሙም ትርጓሜ መድኀኒት ማለት ነው፡፡ ይኽ በኢየሱስ ስም የተጠራው ኢያሱ ተሰቅሎ ነበር ወይ?? ኧረ ተዉ! ሳይሰቀሉ አርጅተው የሞቱ ቤዛዎች አሉ፡፡

እኔ ግን ይኽ ነገር በሽታ ይመስለኛል፡፡ እያነበቡ የሚያነቡትን እንዳይረዱ የሚያደርግ በሽታ አለ፡፡ Alexia ይባላል፡፡
ይኽ በሽታ መሰለኝ የአለማወቅ ጸጋ የሚያበዛ፡፡

https://t.me/MekaneTibeb1

  የአባቶቻችን ጉባኤ በኒቂያ፣ በቆስጠንጢኒያ፣ በኤፌሶን ተገኝቶ በየባረከ የቅዱሳን አምላክ በዚህ ጉባኤ ተገኝቶ ጉባኤውን ይባርክልን፤ ይጠብቀንም!https://t.me/MekaneTibeb1
26/04/2025



የአባቶቻችን ጉባኤ በኒቂያ፣ በቆስጠንጢኒያ፣ በኤፌሶን ተገኝቶ በየባረከ የቅዱሳን አምላክ በዚህ ጉባኤ ተገኝቶ ጉባኤውን ይባርክልን፤ ይጠብቀንም!

https://t.me/MekaneTibeb1

ካህን አባት ማነው? አሁን ምን አጋጠመን?ሊቀ ልሳናት Fantahun Wakie ========✍️ የሊቀ ካህን የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ሥልጣን የሆነች ክህነት በጸጋ ለሰው ልጆች ለዘላለም እ...
25/04/2025

ካህን አባት ማነው? አሁን ምን አጋጠመን?

ሊቀ ልሳናት Fantahun Wakie
========

✍️ የሊቀ ካህን የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ሥልጣን የሆነች ክህነት በጸጋ ለሰው ልጆች ለዘላለም እየታደለች ሰዎች እንዲድኑባት የተደረገበት መንገድ ቀኖናዊ፣ ሰንሰለታዊ፣ እምነታዊ፣ ሥርዓታዊ መንገዱ አንድ ብቻና ብቻ ነው። እርሱም ቀኖና ሐርያትን፣ ፫ቱን ዓለም አቀፍ የአበው ጉባኤአትን፣ በተቀደሰ ትውፊታዊ ቅብብሎሽ ቤተክርስቲያን የኖረችበትን ሥርዓት ያለመቆነጻጸልና በተቃራኒ መንገድ ባለ መውሰድ ነው።

✍️ ይህ መንገድ በሐዋርያት እጅ መጫን ብቻ የሚተላለፍ፣ ሐዋርያዊ ቅብብሎሽ በጸጋ የሚታደለውና በእግዚአብሔር ተቀባይነት ያለው ክህነት ኮኖ ለሰው ልጆች መዳን የሚያገለግለው ሿሚና ተሿሚው የማይነጣጠሉ ምሥጢራት የሚፈጸሙባት እና ትእዛዛት በትግባር የሚተረጎሙባቸውን የሚከተሉትን ሐዋርያዊ ትውፊትና ቀነኖናት መከበራቸውን በሚያረጋግጡ አኗኗሮች ተሟልተው ሲገኙ ነው:-

፩) ያመነ፣ የተጠመቀ፣ በሜሮን የታተመ፣ የቆረበ፣ በክርስቲያናዊ ስነ ምግባር የጸና ሿሚና ተሿሚ ሲገናኙ፤

፪) የዚህን ዓለም ከንቱ ኢክርስቲያናዊ አስተምህሮዎችን፣ አሕዛባዊ አኗኗሮችን፣ ባዕድ አምልኮን እና የሰው ልጆችን ክብር የሚያበላልጡ ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ዝንባሌዎችን በአፍ፣ በመጽሐፍና በተግባራዊ ሕይወቱ እየተዋጋ ለቤተክርስቲያን መንጋ የሚያበዛ፣ የሚጠብቅ፣ ለሰማእትነት የተዘጋጀ ሿሚና ተሿሚ ሲገናኙ፤

፫) የአበውን ትምህርት፣ ትውፊታዊ ቅብብሎሽ፣ ሥርዓተ አምልኮና አርአያ ክህነቱን በሁሉ ቦታና ሁኔታ ውስጥ የሚጠብቅ ሿሚና ተሿሚ ሲገናኙ፤

፬) ቅድስናን ከሚቃረኑ ከዝሙት፣ ከሀሰተኝነት፣ ከስግብግብነት፣ ከዘረኝነት፣ ከኑፋቄ፣ ከትዕቢት፣ ከከፋፋይነት እጅግ የተጠነቀቁ ሿሚናንተሿሚ ሲሆኑ፤

፭) ሲመተ ክህነትን በምልጃ፣ በእጅ መንሻ፣ በጎሣና በብሔረሰብ ድርሻ አስደግፈው ያልተሾሙ፣ ያልሾሙ፣ ሥልጣኑን ለምድራዊ ዓላማ የማይጠቀሙ አባቶች ሲሾሙና ሲሾ'ሙ ነው።

* በዚህ ዘመን በእኛ ያጋጠመን ምንድነው?
* በገንዘብና በፖለቲካው ትልቅ ገብነት ስንቱ ተሾመ?
* እንደየዘመኑ የዘር ፖለቲካ ፍላጎት በጎሣ ድርሻ ተሰብስበው የክርስቶስን የጸጋው ማደያ ክህነትን ለኑሮአቸው ማደያደያ የተጠቀሙ ስንቶቹ ናቸው?
* ልጆቻቸው በኑፋቄ፣ በዘረኛ ፖለቲካዊ ትርክት ሲጠፉ እንደ መከላከል በተቃራኒው መለያየትን የሚመሩ አባቶች አልተፈጠሩም?

* ለመፍትሄው በዚህ ዘመን ከዚህ ውድቀት የተረፉት ከከካህናትና ክከምእመናን ወገን የሆኑ ክርስቲያኖች ድርሻ ምን ይሁን?
የሁሉም የውይይት ነጥብ ሆኖ በመፍትሄው ላይ ቀኖና ሐዋርያትን ሳያፋልስ መደረግ የሚገባውን በማጋራት እንሳተፍ።

https://t.me/MekaneTibeb1

"የተናገርኸውን ትምህርት አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው"ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መላከ ✍️ ብቻህን ማሰብ ስትጀምር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የብቻችን የሆነ ትምህርት ...
23/04/2025

"የተናገርኸውን ትምህርት አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው"

ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መላከ

✍️ ብቻህን ማሰብ ስትጀምር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የብቻችን የሆነ ትምህርት የለም። በማኅበር እንማራለን ፤ በማኅበር እንጸልያለን ፤ አንድ ሆነን የተዘጋጀልንን ማዕድ ቅዱስ ቊርባን እንቀበላለን ፤ በመጨረሻም የተዘጋጀልንን የተስፋ አገር እንቀበላለን።

✍️ ክርስቶስ ያስተማረ በጉባኤ ነው ፤ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ምንጊዜም ጉባኤአዊት ሆና ትቀጥላለች እንጅ ማንም ምንም ቢሆን የራሱን ትምህርት አምጥቶ ሊያስተምር የሚችልበት ዕድል የለውም።

የብቻው የሆነ ክርስቶስ ስለሌለው የብቻው የሆነ ትምህርትም ሊኖረው አይችልም።

✍️ ብቻህን ማሰብ ከጀመርህ ከጉባኤው የተለየ አስተምህሮ ማምጣትህ ስለማይቀር “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኵሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” የሚለውን የሃይማኖት መግለጫ አስቀድመን እንድናውቅ መደረጉ ስለዚህ ነው።

✍️ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖር ማንም ቢሆን ቤተ ክርስቲያን ካስተማረችው ትምህርት የወጣ እንደሆነ መዐርጉ ፣ የዕውቀት ደረጃው ፣ የወገኑ የሀብቱ ብዛት ሊያድነው አይችልም። በመጀመሪያ ከቃሉ የሰሙ ሰዎች “የተናገርኸውን ትምህርት አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ብለው ይመክሩታል። ምክራቸውን ሰምቶ በዚህ ካቆመ ይተዉታል፤ ምክራቸውን አልሰማ ብሎ ከቀጠለ ግን ወደ መምህራን ያደርሱታል፤ መምህራንንም አልሰማ ካለ ወደ ጉባኤ {ሲኖዶስ} ይቀርባል። ሲኖዶሱን ካልሰማ ተወግዞ ይለያል።

✍️ በሰሞኑ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የሰጡትን ትምህርት በቪዲዮ አንዲት ወዳጄ ልካልኝ ተመለከትሁት፤ ምናልባት ከባልንጀሮቻቸው ጋር ተማክረውበት ከበታቾቻቸውም ጋር ተከራክረውበት የነበረ ጉዳይ ከሆነ “አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ሊሏቸው ይገባ ነበር።

✍️ አሁን ግን በሹክሹክታ ሳይሆን በሰገነት ላይ የተሰበከ የስሕተት ስብከት ስለሆነ ጉዳዩ ከዚህ ያለፈ ይመስለኛል። ከረፈደም ቢሆን ባየሁት መረጃ መሠረት ብዙ ሊቃውንት ሀሳብ ሰጥተውበታል ፤ ይሄ ለብፁዕነታቸው መልካም ዕድል ነው ብየ አምናለሁ። ሀሳባቸውን የገለጹ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን በሊቅነታቸው የምታምንባቸው ሊቃውንት እንደመሆናቸው መጠን ምክሩን ይቀበሉታል ብየ ስለማምን ነው። ሀሳቡን ሳይንቁ በቶሎ በሰገነት ላይ ያጠፉትን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በሰገነት ላይ ወጥተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። “አትደንግጡ” ብለውናል እንዳንደነግጥ ያድርጉን።
ይህንን ትምህርት አባቶቻችን አልነገሩንም መጻሕፍቶቻችን ላይ ተጽፎ አላገኘነውም።

ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ መጻሕፍቶቻችንን አባቶቻችንን ተቃውመዋል። ዛሬ መልስ አልጽፍም፤ ምክንያቱም መልሱን ከብፁዕነትዎ ስለምጠብቅ ነው።

ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ

https://t.me/simakonem

23/04/2025
https://youtu.be/CaFjGIsLLIQ?si=6qzi_RjwYCqfpgkt
21/04/2025

https://youtu.be/CaFjGIsLLIQ?si=6qzi_RjwYCqfpgkt

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! በበዓለ ትንሣኤ እና በበዓለ ሃምሳ የሚዘመሩ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራት Ethiopian Orthodox Mezmur #ኦ....

መከራም ቢያጸኑበት አልተቀየማቸውም፤ ዕውነትን ለሚፈርድ ቸርነትን መለሰ እንጂ፤ በመቸንከሩም የሞት ችንካርን አጠፋልን። ሔዋን በእግሮቿ ወደ ዕፀ በለስ ስለ ተመላለሰች እጆቹንና እግሮቹን በመቸ...
17/04/2025

መከራም ቢያጸኑበት አልተቀየማቸውም፤ ዕውነትን ለሚፈርድ ቸርነትን መለሰ እንጂ፤ በመቸንከሩም የሞት ችንካርን አጠፋልን። ሔዋን በእግሮቿ ወደ ዕፀ በለስ ስለ ተመላለሰች እጆቹንና እግሮቹን በመቸንከር ከፍሏልና። በእጆቿም የበለስን ፍሬ ስለቆረጠች ፈንታ በእውነት የእግዚአብሔር ቃል በሥጋው ከመስቀል እንጨት ጋራ ተቸነከረ።
የሐሙስ ድርሳነ ማኅየዊ

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alebachew Worku posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Alebachew Worku:

Share