ዝክረ ወይብላ ማርያም

ዝክረ ወይብላ ማርያም ጥንታዊቷን እና ታሪካዊቷን ገዳም የወይብላ ደ/ም/ቅ/ድ/ማርያም ገዳምና ሌሎችንም አድባራትና ገዳማትን የምናስተዋውቅበት ገፅ ነው

27/09/2022

መስቀል አደባባይን የመስቀል አደባባይ ማድረግ አለብን - (ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

እንደሚታወቀው መስቀል የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ በዓልዋ መሆኑ የታመነ ነው፡፡ ሆኖም የመስቀል በዓል ከመንፈሳዊ በዓልነቱ ይልቅ ፌስቲቫላዊ ቅርፁ በጣም የሚያይል አከባበር ያለው በዓል ነው፡፡

እንደሚታወቀው በበዓሉ ዕለት ቤተ ክርስቲያን ከምትጠቀምበት ሰዓት ይልቅ የተለያዩ የፖለቲካ ሰዎችና ተጋባዥ እንግዶች ርዝመቱ የማይገመት ንግግር የሚያደርጉበት ሰዓት ይበዛል፡፡ የቤተ ክርስቲያንዋም አካላትም ከመንፈሳዊ ስብከት ይልቅ መንግሥትንና ተጋባዥ ዲፕሎማቶችን ማእከል ያደረገ ‘የተከበሩ አቶ እገሌ’ የሚበዛው ንግግር ሲያደርጉበት ይስተዋላል፡፡ በዓለ መስቀልም ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለመዳሰስ ሰበብ ሆኖ ያገለግላል እንጂ ወደ አደባባዩ መጥቶ ስለ ጌታችን መስቀል ምንም ዓይነት ነገር ሰምቶ የሚሔድ ምእመን የለም፡፡

በደርግ ዘመን እንኳን ከብዙ ችግር ጋር እነ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የሰበኩት ‘ዮም መስቀል ተሰብሐ’ የሚል ስብከት ተጠቃሽ ነበር፡፡ ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ግን መስቀል አደባባይ ላይ የሚተላለፉ መልእክቶች እንዴት በዓሉን ከወቅታዊ ትኩሳት ጋር እናስተሳስረው በሚለው ላይ ብቻ ያተኮሩ ናቸው፡፡ ከዚያ ውጪ መስቀል አደባባይ በአግባቡ ምሕላ እንኳን ደርሶበት አያውቅም፡፡ ሐቁን ለመናገር እንደ መስቀል በዓል አከባበርም መስቀሉን የሚቀብር ተራራ የለም፡፡

የምእመናን በዓል እንደመሆኑ ከውጪ የሚመጡ እንግዶች ሕዝቡ በዓሉን ሲያከብር መመልከት ሲገባቸው በመስቀል አደባባይ ግን ሕዝቡ የውጪ እንግዶች በዓሉን ሲያከብሩ ከሩቅ ሆኖ ይመለከታል፡፡ ነፋስ የሚያማታውን የስፒከር ድምፅ እየተከተለ ጭብጨባ ሲሰማ ያጨበጭባል፡፡ የአደባባዩ መርሐ ግብር አስተዋዋቂ አሁን እንዲህ እየተከናወነ ነው ሲል እየሰማ ሥፍራው ላይ ያለው ሕዝብ በቤቱ በቴሌቪዥን ከሚመለከተው ሰው ያነሰ መረጃ ኖሮት ተደናብሮ ይመለሳል፡፡ አንዳንዴም ደመራው ቶሎ አልበራ ሲለው በፉጨትና በጭብጨባ ፍጠኑ ይልና ሕዝቡ ራሱ ጧፍ በመለኮስ በዓሉን ያስጀምራል፡፡

አንድ ስብከት ሳይሰበክ ፣ አንድ መዝሙር በወጉ ሳይሰማ ሊቃውንቱ ፣ መዘምራኑ የኦሎምፒክ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት እንደሚታዩት አትሌቶች ምንም ሰዓት ሳያገኙ በጥድፊያ አልፈው እንዲያልፉ ይደረጋል፡፡ አብዛኛው የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣትና የማኅበራት መዘምራን መስቀል ሲመጣ እንደ ትልቅ አገልግሎት የሚያዩት ከበዓሉ ዕለት ይልቅ ለበዓሉ ሲዘጋጁ የሚያቀርቡትን ዝማሬና ወደ አደባባዩ እስከሚደርሱ ድረስ በመንገድ ላይ የሚዘምሩትን ዝማሬ ነው፡፡ የልዩ ልዩ ሚዲያ ጋዜጠኞችም መስቀሉን መቅበራቸው የተለመደ ነው፡፡ ‘የዘንድሮን የመስቀል በዓል ካለፈው ዓመት የተለየ የሚያደርገው ግድቡ በተገባደደበት ማግስት ላይ በመሆናችን ሲሆን’ የሚል ዘገባ ያቀርባሉ፡፡

አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ለቃለ መጠይቅ ያቀርቡና ‘መስቀል ከሃይማኖታዊነቱ ባሻገር ለሀገር የሚያበረክታቸው እሴቶች ምን ምን ናቸው?’ ‘የመስቀል በዓል በዩኔስኮ መመዝገቡ ያለው ጠቀሜታ ምንድን ነው?’ የሚሉ በየዓመቱ እንደ ችቦው የማይቀሩ ችክ ምንችክ ያሉ ጥያቄዎችን ያቀርባሉ፡፡ በማግስቱም የመንግሥት ሚዲያዎች ስለ ክትፎ አሠራርና ስለ ቆጮ አዘገጃጀት ቀኑን ሙሉ ሲያብራሩና ዘፈን ሲጋብዙ ይውላሉ፡፡ ታሪኩን የማያውቅ ሰው ንግሥት እሌኒን የጉራጌ ንግሥት ፣ መስቀሉም ከክትፎ ውስጥ ተቆፍሮ የተገኘ ሊመስለው ይችላል፡፡

ብቻ በአጭሩ መስቀልን ሲያስታውስ አንድ ነገር ጨበጥሁ የሚል ሰው ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ ደመራው የሚለኮስበት ውብ ሰዓት ላይ ብቻ ሕዝቡ በእልልታና በጧፍ እያጀበ ሰውነትን የሚነዝር ዝማሬ ያቀርባል፡፡ አሁን አሁን ቀረ እንጂ ደመራው የወደቀበትን አቅጣጫ እንደ ሀገሪቱ ፖለቲካ ኮምፓስ ቆጥሮ ወዴት ወደቀ ብሎ በጭንቀት የሚጠይቅም ብዙ ሰው አለ፡፡ ከዚያ በኋላ መስቀል አደባባይ ለሰዓታት ብቻ መስቀሉን አክብሮ አገልግሎቱ ያበቃል፡፡

ይህንን በማድረግ ፈንታ ቢያንስ ከዋዜማው ጀምሮ እንኳን ቤተ ክርስቲያን አደባባዩን መጠቀም መቻል አለባት፡፡ ዓለምን ያስደመሙት የኢትዮጵያ መስቀል ዓይነቶች ለሀገር ውስጥና ለውጪ ጎብኚዎች በዐውደ ርእይ የሚታዩበትና ለሽያጭ የሚቀርቡበት ፣ የኢትዮጵያ የመስቀል ዐውደ ጥናት የሚካሔድበትና በዘርፉ ላይ ጥናት የሠሩ ባለሙያዎች ጥናት የሚያቀርቡበት ፣ የቤተ ክርስቲያንዋ የያሬዳዊ ዜማ ሀብታት በአደባባይ የሚታዩበት ፣ በዕለቱ ተካልበው የሚያልፉት የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በዋዜማው ምሽት አደባባዩን ሞልተው ዋዜማውን በዝማሬ የሚያሳልፉበት ፣ በዕለቱ የሚቀርበውም ትርዒት የተመጥነና ለሕዝቡ ትደራሽ እንዲሆን በባለሙያዎች የታገዘ ቢሆን ፣ ቤተ ክርስቲያንዋ በበዓሉ ላይ ለሚገኘው ሕዝብ አንዳንድ የገቢ ማሰባሰቢያ ሥራዎችን የምትሠራበት ሁኔታ ቢመቻች መስቀል አደባባይ እውነትም መስቀል አደባባይ መሆን ይችላል፡፡

ስለመስቀል አደባባይ ከጻፈው የተወሰደ - ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነመስቀል ቤዛነመስቀል መድኀኒተ ነፍስነ አይሁድ ክሕዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ
26/09/2022

መስቀል ኃይልነ
መስቀል ጽንዕነ
መስቀል ቤዛነ
መስቀል መድኀኒተ ነፍስነ አይሁድ ክሕዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ

25/04/2022

እንኳን ለብርሃነ ትንሳአው በሰላም አደረሳችሁ ውድ የfb ቤተሰቦቻችን
ያው ብንዘገይም መዘግየት ከመቅረት ይሻላልና በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን

የሆሳዕና በአረያም
17/04/2022

የሆሳዕና በአረያም

ናፈቀኝ ደጅሽ ወይብላየ
01/02/2022

ናፈቀኝ ደጅሽ ወይብላየ

27/12/2021

"አይቀናችሁም"

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለኢሳቱ ጋዜጠኛ ከነገሩት መካከል አንደኛው "በጎቼን ትቼ ከሔድሁ እረኛ ልባል አልችልም" ለዚህ ነው ከሕዝቡ ጋር የቆየሁት ያሉት ልብ ውስጥ የሚቀመጥ ነው።

ሌላው ሕወሐቶች ከምኑም የሌሉበትን ሦስት ተማሪዎቼን መቱብኝ። ኹለቱ ሞቱ አንደኛው ለታሪክ ተርፏል። እኔም በድርጊታቸው አዝኜ "በዚህ ዓይነት ከኾነ አይቀናችሁም" ብዬ ተናግሬአቸዋለሁ ያሉት ይጠቀሳል።

እየከዱ ወደ ትግራይ ሲሔዱ የነበሩ የሕወሐት ወታደሮች ራበን ባሉ ጊዜ አብልተናቸዋል፣ መንገድም በጠየቁን ጊዜ ጠቁመናቸዋል።

ነገራቸውን እየሰማሁ በሔድሁ ቁጥር እየሳሳሁ መኾኔን ልደብቃችሁ አልችልም። ያሰንብትልን!

ብፁዕ አባታችን በገንዘብ ብቻ ፭.፱ (5.9) ሚሊየን ብር ዕዳ አለባቸው። በእህል ሰፍረው ከገበሬው የተቀበሉትም አለባቸው። ይህንን ብድር ለመመለስ በራሳቸውና በረዳታቸው የሚንቀሳቀሱ በሀገረ ስብከቱ ስም የተከፈቱ የባንክ ቋቶች እነሆ ፡ -

ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር: 1000448699297
Swift code: CBETETAA

አቢሲኒያ ባንክ ቁጥር ፡ 85590928
Swift Code: ABYSETAA
ዲ/ን ኢንጂነር ዓባይነህ ካሴ

https://youtu.be/jFheDULflPE

እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን አዲሱ አመት የሰላም የፍቅር የመተሳሰብና የአብሮነት ዘመን ይሁንልን ለሀገራችን ሰላምን ለህዝባችን ፍቅርን እግዚአብሔር ያድልልንመልካም በአል
10/09/2021

እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን አዲሱ አመት የሰላም የፍቅር የመተሳሰብና የአብሮነት ዘመን ይሁንልን ለሀገራችን ሰላምን ለህዝባችን ፍቅርን እግዚአብሔር ያድልልን
መልካም በአል

ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅን በአል በወይብላ ማርያም ገዳም ለማክበር ያሰባችሁ የእመብርሃን ልጆች ጉዞ እያዘጋጀን ስለሆነ መመዝገብ ትችላላችሁ0927432887 መታፈርያ ብላችሁ ተመዝገቡ እናታ...
25/04/2021

ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅን በአል በወይብላ ማርያም ገዳም ለማክበር ያሰባችሁ የእመብርሃን ልጆች ጉዞ እያዘጋጀን ስለሆነ መመዝገብ ትችላላችሁ
0927432887 መታፈርያ ብላችሁ ተመዝገቡ
እናታችን ቅድስት ድንግ ማርያም ለሀገራችን ሰላም ለህዝባችን ፍቅርና አንድነትን ታድልልን

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ወይብላ ማርያም      ወረኢሉ ወረዳ ውስጥ የምትገኘው ወይብላ ማርያም ግንቦት 21 በያመቱ እንደምትከብር ይታወቃል ዘንሮም በደጇ ተገኝተን እበረክ...
24/04/2021

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ወይብላ ማርያም
ወረኢሉ ወረዳ ውስጥ የምትገኘው ወይብላ ማርያም ግንቦት 21 በያመቱ እንደምትከብር ይታወቃል ዘንሮም በደጇ ተገኝተን እበረክ ዘንድ ሁላችንም ተጋበዘናል ። ከአዲስ አበባ ጉዞ እያመቻቸን ስለሆነ ከወዲሁ የቻልን እንመዝገብ ያልቻልን ለሌሎች እንዲደርሳቸው መልእክቱን ሸር እናድርግ
ስልክ ቁጥር 0927432887 መታፈርያ
እማምላክ ሀገራችንን ሰላም አድርጋ እደጇ ተረግጠን እንማፀናት ዘንድ ትፍቀድልን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዝክረ ወይብላ ማርያም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share