መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

23/05/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “ካህናቶችዋም ሕጌን በድለዋል ቅድሳቴንም አርክሰዋል፤ ቅዱስ በሆነና ቅዱስ ባልሆነ መካከልም አልለዩም፥ በንጹሕና በርኩስ መካከል ያለውን ልዩነት አላስታወቁም፤ ዓይናቸውንም ከሰንበታቴ ሰወሩ።” (ሕዝቅ/22/26) ተብሎ የተጻፈውን አስተውሉ! ካሕናት ማለት የሌዊ ዘር የኾኑ ሌዋውያን ናቸው፡፡ የዘወትር ተግባራቸው እግዚአብሔርን ማመስገን ሕዝብን በቅድስና መንገድ መምራት ነበር፡፡ ነገር ግን በዚህ ዘመን ያሉ ብዙዎቹ ካሕናት ነን የሚሉቱ የሥላሴን ሕግ ትተው የዓለምን ሕግ ያስከብራሉ፤ በንዋየ ቅድሳቱ ያመሰግኑ ዘንድ ሲገባቸው ንዋየ ቅድሳቱን ከመቅደሱ አውጥተው ይሸጣሉ ይለውጣሉ፤ ቅዱስ የኾነውን ቅዱስ፡ ማለት ቅዱስ ያልኾነውን ደግሞ ርኩስ ይሉ ዘንድ ልባቸው ሳይፈራ በአንድነት ያከናውኑታል፡ በቀኝ እጃቸው መስቀል በግራ እጃቸው የጋኔን መጎተቻ ይይዛሉ፤ በቅድስና መንገድ እንመራዋለን የሚሉትን ሕዝብ ንጹህ እና ርኩስ የኾነውን ለይቶ ያውቅ ዘንድ አላስታወቁትም፡ ይልቁንም ሕዝብ ንጹሁን ለይቶ ቢያውቅ ለሥጋቸው የሚመቸውን ያሳጣናል ብለው ይሠጋሉና መግለጽ የሚገባቸውን ሠውረው በአሕዛብ መንገድ ይጓዛሉ፡፡

🔯 ስለዚህ፡ እግዚአብሔር በተዋሕዶ መንገድ የመራህ የአባቶችህን ክብር የሰጠህ ሕዝበ እትዮጵያ ሆይከእነዚህ የበግ ለምድ ለባሾች ርቀህ በአባቶችህ የቅድስና መንገድ ትመላለስ ዘንድ በጭካኔ እንመክርሀለን።

🔯 ባለፈው ሳምንት ካቆምንበት እንቀጥል ዘንድ ወድደናል፦ ያለመታዘዝ ምን ትመስላለች፡ ዋጋዋስ ምንድነው!!! ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ተናገረ፡ “እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና። (ኢሳ/1/19—20)

🔯 በእውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው፡ እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ መታዘዝ ከመሥዋዕት ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።” (ሳሙኤል ቀ/15/22)

🔯 ራሳችሁን ለምታቀርቡለት ለርሱ ለምትታዘዙለት ባርያዎች እንደኾናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኀጢአት ባርያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባርያዎች ናችሁ። (ሮሜ 6/16)

🔯 መታዘዛችሁ በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ኹሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል። (2/ቆር/10/6)

🔯 “ከትእዛዛትህ የሳቱትን ትዕቢተኞችንና ርጉማንን ዘለፍህ።” በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም፤ እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል። እጆቼንም ወደ-ወደድኋቸው ወደ-ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላለሁ።” (መዝ/119/21፣ 45-48)
ኃጢአተኞች ጨዋታን ነገሩኝ፥ አቤቱ፥ እንደ-ሕግህ ግን አይደለም። ትእዛዛትህ ሁሉ እውነት ናቸው፤ በዓመፅ አሳድደውኛል፤ እርዳኝ። ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም። እንደ-ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፤ የአፍህንም ምስክር እጠብቃለሁ። አቤቱ፥ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል። እውነትህ ለልጅ ልጅ ናት፤ ምድርን መሠረትሃት እርስዋም ትኖራለች። ሁሉም ባሪያዎችህ ናቸውና ቀኑ በትእዛዝህ ይኖራል።” (መዝ/119/85-91)

🔯 “አቤቱ፥ ሕግህን እንደ-ምን እጅግ ወደድሁ ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው። ለዘላለም ለእኔ ነውና ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ። ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ። ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ። ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ። አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም። ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ። ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው። የጽድቅህን ፍርድ እጠብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸናሁም።” (መዝ/119/97-105)

🔯 እንግዲህ ለሚያስተውል መታዘዝ ማለት እንደ-አብርሃም ያለች መታዘዝ ጸጋም በረከትም ማስተዋልንም ሰጥታ እድሜንም እንደ-እርሱ እንደ-አባታችን አብርሀም እስከ 962 ዓመት የምትሰጥ ወይም እንደ-ኤልያስ እንደ-መልከጼዴቅ፡ እንደ-ሔኖክ ወይም እንደ-ብዙኃን እትዮጵያውያን ቅዱሳን ዘለዓለማዊነትን የምታጎናጽፍ ናት፡፡

🔯 በሌላ አንጻር ያለመታዘዝ ማለት ግን አመጻ ማለት ነው፤ መታዘዝ እሺ ማለት ሲኾን፡ አለመታዘዝ ደግሞ እምቢ፡ ማለት ነው፡፡

🔯 ነቢዩ ሳሙኤል፡ ንጉሡን ሳኦልን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቀብቶ አነገሠው ነገር ግን ሕዝበ እስራኤልን ይዞ ከፍልስጤማውያን ጋር ለመዋጋት በወጣ ጊዜ ያገኘኸውን ሰውንም ከብትንም ኹሉ ግደል የሚል የእግዚአብሔር ትእዛዝ ደርሶት ሳለ፡ እንደ-ትእዛዙ ሰዎቹን ኹሉ በሰይፉ ካጠፋ በኋላ የሚያማምሩትን የፍልስጤማውያንን ከብቶችና አውራ በጎች ባየ ጊዜ ጎምዥቶ ሳይገድል ለመሥዋዕት አቀረባቸው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ከአውራ በግ ይልቅ በእግዚአብሔር የተወደደው መታዘዝ ነው፤ ከእንግዲህ ወዲህ ባለመታዘዝህ ጠንቅ እግዚአብሔር መንግሥትህን ከአንተ ወሰደው ለጎረቤትህም ሰጠው ተብሎ ተነገረበት፤ በዚያም ዘመን ከፍልስጤማውያን ጋር ሲዋጋ በጦር ተገድሎ ሲሞት በቤቱ ያደገው ቅዱስ ዳዊት ንግሥናውን ወሰደ፡፡

🔯 አለመታዘዝ ቃየንን ትመስላለች፤ አቤል ለእግዚአብሔር ንጹህ መሥዋዕትን ሲያቀርብ ቃየን ግን ግብስብስ መሥዋዕት በማቅረቡ ተቅበዝባዥ ደስታ የሌለው ኾነ፡ ዘሩም በአጋንንት እጅ ወድቀው ከአጋንንት ጋር እየተዳቀሉ እስከ-ዛሬ ከርኩሰት ጋር አሉ፡ ፍጻሜአቸውም በገሀነም ይኾናል፡፡

🔯 አለመታዘዝ የአስቆሮቱን ይሁዳን ትመስላለች፡ ይሁዳ ኀዋርያው አድርጎ የሾመውን አምላኩን መታዘዝ ትቶ ሥጋ ለባሾችን ተከትሎ ለሮማውያንና ለፈሪሳውያን ትእዛዝ ባርያ ኾኖ አምላኩን ለገዳዮቹ አሳልፎ ሰጥቶ ባደረገው ክፋት ጸጸት በዛፍ ላይ አንጠልጥላ ገደለችው፡ ብልጠቱም ከሲኦል መግባት አላስጣለችውም፡፡

🔯 አለመታዘዝ የናቡ ከደነጾርን ባለሟሎች ትመስላለች፤ ሚሳቅ፡ ሲድራቅና አብደናጎ የተባሉ አይሁዳውያን የንጉሥ ናቡ ከደነጾርን ጣኦት መታዘዝ ትተው የአይሁድን አምላክ እግዚአብሔርን ይታዘዛሉ ብለው ከሰዋቸው ንጉሡ በታላቅ እቶን እሳት ውስጥ ይጣሉ ዘንድ ትእዛዝ ሰጥቶ ከእነ-ሰናፌላቸው ወደ-ነበልባሉ በተጣሉበት ጊዜ፡ ሰለስቱ ደቂቅን በእሳት ለመጨመር ሲሉ ወደ-እሳቱ የተጠጉት ከሳሾቻቸው በእሳቱ ወላፈን ተቃጥለው ሲሞቱ የሥላሴን ሕግና ትእዛዝ አምልኮም አንተውም ያሉት ሲድራቅ፡ ሚሳቅና አብደናጎ በእሳቱ መሀል ከመላእክት ጋር ሲዘምሩ ያየው ንጉሥ ከሳሾቻቸውን በሰይፍ ገድሎ ራሱ ንጉሡ ከአመጻ ተለይቶ የእነ-ዳንኤልን አምላክ አመለከ፡፡

🔯 አለመታዘዝ ዲያብሎስን ትመስላለች፤ እግዚአብሔር አምላክ ዲያብሎስን የነገደ መላእክት አለቃ አድርጎ ሾሞት ከፍ ከፍ አድርጎት ሳለ፡ እርሱ ግን ለእግዚአብሔር አልታዘዝም ብሎ ከእነ ነገዱ ከሰማይ ወደ-ጥልቁ የሥቃይ ስፍራ ተጣለ፤ እነሆ ዝርያውም እስከ-ዛሬ ድረስ ሰዎችን እያሳተ ልባቸውንም ባለመታዘዝ በአመጻ እየሞላ የዘለዓለም ሞትን ሞቶ እናየዋለን፡፡

🔯 ስለዚህም፡ መታዘዝ መጨከንን ትፈልጋለች፡ መንገዷ ቅን ኾና የሚቃወሟት ብዙዎች ናቸውና፤ አመጻ ግን መንገዷ ሰፊ ነው ዓለማውያን በሥጋ ነጻ ፈቃድ በሥጋዊነት ሲኖሩ በአጭር እድሜ ውስጥ ብዙ የሚያጠፉባት ናትና፡፡

🔯 ስለዚህም እኛ የልብን ጭካኔ የምትሻ ፍጻሜዋ ዘለዓለማዊነት ሕያውነት የኾነችውን አዋጅ እንገልጽላችኋለን፡፡ እውነተኛ እምነት አንዲት ብቻ ናት፤ እርሷም ርትዕት ዘለዓለማዊት ተዋሕዶ ናት፡፡ ሰንበት አንዲት ናት፤ እርሷም አምላክ ሥራውን በ6 ቀናት ፈጽሞ ያረፈባት ቅዳሜ ሰንበት ብቻ ናት፡፡ ሕይወት እና የሕያዋን ዕረፍት አንዲት ናት፤ እርሷም ዘለዓለማዊነት የሚሰጠንን ሥጋዋን እና ደሟን ከልጇ ከእግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ የምትመግበን ቤዛዊተ ዓለም ድንግል ማርያም ናት፡፡ አምላክ አንድ ነው፤ እርሱም አንድ ሲኾን፡ ሶስት፡ ሶስትም ሲኾን አንድ የኾነ ስሉሥ ቅዱስ ኀያል አጋዕዝት ሥላሴ መለኮት አሐዱ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ይህ አዋጅ የቅዱሳን እትዮጵያውያን አዋጅ የፍጻሜው ምስጢር እና የፍጻሜው ቁርጥ ፍርድ ነው፡፡ የሚታዘዝ የሚተገብረው ይድንበታል፡ አመጸኛው የሚቧልት ግን የፍጻሜውን የአመጻውን ፍሬ ይበላል፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

16/05/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፥ በሰንበትም ቀን ሸክም አትሸከሙ፥ በእየሩሳሌምም በሮች አታግቡ፥ ከቤቶቻችሁም በሰንበት ቀን ሸክምን አታውጡ፥ ሥራንም ሁሉ አትሥሩበት፤ አባቶቻችሁንም እንዳዘዝሁ የሰንበትን ቀን ቀድሱ። እነርሱ ግን አልሰሙም ጆሮአቸውን አላዘነበሉም፥ እንዳይሰሙና እንዳይገሠጹም አንገታቸውን አደነደኑ።” (ኤር/17-21-23) ተብሎ እንደተጻፈ፡ የሰው ልጅ እግዚአብሔር ያከበራትን ሰንበትን ማክበር አልሻም ብሎ በአመጸኝነት በዕለተ ሰንበት/ቅዳሜ ሸክም ሲጠገረር፡ መከራንም በዚያው ልክ ሲሸከም፣ ሥራን ሲሠራ፡ ሥላሴ ደግሞ ያለመታዘዙን ዋጋ ሲከፍለው ይኖራል፡፡ ቅዱስ ሰሎሞን እንዳለው ““የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው” ምሳሌ 9/10) ብሎ እንደተናገረ የሚያስተውል ሰንበትንም የሚያከብር አምላኩን የሚታዘዝ እርሱ ጠቢብ ይባላል፡፡

🔯 በዚህ ድንቅ የፍጻሜ ዘመን እጅግ አስገራሚ ሰዎችን ዓየን! አስገራሚ የመቅሠፍት ድምጻቸውን በሰማን ጊዜም የመለኮትን ሥራ እፁብ አልን፡፡

✡ 1. ሰዎች፡ “እኔ ደግ ነኝ” ይላሉ፤ የደግነታቸው መገለጫ ግን ሰውን መግደል ባልንጀራቸውን ማሳደድ ኾኖ ዐየን፡፡

✡ 2. ሰው “እኔ እትዮጵያዊ ነኝ” ይላል ቀጥሎ በለበሰው ለምድ ውስጥ እትዮጵያን የሚያደማውን የሚያርድበትን ሰይፍ ስሎ አስልቶ በሀገራችን አንገት ላይ ይጭናል፤

✡ 3. ሰው፡ “የመዳን ቀን ዛሬ ነው ጌታን ተቀበሉ” ይላል ዘወር ብሎ ወንድሙን ሲገድል እህቱን ለመከራ ሲሸጥ ጎረቤቱን በእንባ ሲሞላ ቤቱን በርሱ ላይ በሚያዝኑበት የለቅሶ ድምጽ እየሞላ ራሱም ሳይድን ዕናየዋለን፡፡

✡ 4. ሰው “በቀል የእግዚአብሔር ነው፤ አትበቀል” ይላል እርሱ ራሱ ግን ያልበደሉትን ክፉም ያላደረጉበትን ክፋት እየተበቀለ ራሱን ከሚናገረው ቃል በላይ ዕናየዋለን፡፡:

✡ 5. ሰው፡ “አትፍረድ ይፈረድብሀል” ይላል፤ እርሱ ግን ከቅን ፍርድ ርቆ መበለቲቱን ሲሞግት በድሀው ላይ በግፍ ሲበይን፤ ለሀብታሙ በመድልዎ ሲፈርድ እጅ መንሻ የሌላቸውን በድህነት መቀመቅ ውስጥ ሲያወርድ ዕናየዋለን፡፡

✡ 6. ሰው፡ “ድንግል ማርያም እመቤቴ መድኃኔዓለምም ሕይወቴ ነው” ይላል፤ ነገር ግን የቤቱን እመቤት ሚስቱን በመከራ ሲዋጃት አንደበቱን ሳይኖርበት ክፋት ከአንደበቱ የተለየ አለቃ ኾኖበት የድንግል ማርያምን ስም ተሸሽጎ በእባብነቱ ይናደፋል፤ ይህም ድንግል ማርያም በፀሓይ ላይ እንደተሰጣ ብቅል እስከምትገልጽበት ጊዜ ድረስ ብቻ ይኾናል፡፡

✡ 7. ሰው፡ “እግዚአብሔር ፍቅር ነው” ይላል እርሱ ራሱ ግን እንጥፍጣፊ ፍቅር የለውምና ፍቅር አይሰጥም፡፡

🔯 ስለዚህም፡ እግዚአብሔር በሚታመኑትና በሚታዘዙት ደስ ይሰኛል እንጂ፡ ስሙን በከንቱ እየጠሩ የእርጉማን ሥራ በሚሠሩት አይደሰትም፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ “በእግዚአብሔር የሚታመን እግዚአብሔርም እምነት የኾነለት ቡሩክ ነው” እንዳለ የሚድኑ ከበጎች የኾኑ የሥሉስ ቅዱስ ኀያል እግዚአብሔርን አባታዊ ትእዛዝ ተቀብለው በቃሉ ከሞት ይድናሉ፡፡

🔯 መታመን ምንድነው!; መታዘዝስ እንዴት ነው!
“መታመን” ማለት በስሉሥ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ፡ በስሉሥ ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፡ በስሉሥ ቅዱስ እግዚአብሔር መንፈስ አሐዱ አምላክ፣ በምስጢረ ተዋሕዶ ወምስጢረ ቁርባን ድንግል ማርያም በተዋሕዶ ፍፁም እውነት አምኖ የእግዚአብሔርን አዳኝነት፣ የእትዮጵያን አምላክ ከሐሊነት፣ የድንግል ማርያምን ታዳጊነት አምኖ በፍጹም መመካት ያለ-ፍርሐት መኖር ማለት ነው፡፡ “መታመን” ማለት፡ ከክፉ ኹሉ የሚታደግህን መለኮትን አምነህ ሞትን፣ ጭንቅን፣ መከራን፣ ረኀብን፣ ስደትን፣ ጦርነትን፣ ድህነትን፣ ሥቃይን፣ እስርን፣ መገለልን፣ ይሉኝታን፣ ስድብን፣ መራቆትን፣ መታረዝን፣ ማጣትን አለመፍራት ማለት ነው፡፡

🔯 “መታዘዝ” ምንድር ናት!!! መታዘዝን ብዙ ሰው በቃሉ ይናገራታል በተግባሩ ግን አይፈጽማትም፡፡ “መታዘዝ” ማለት አንተ የምትወደውን ነገር ትተህ እግዚአብሔር የሚወደውን ማድረግ ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔር ከምትወዳት ሚስትህ ከምትሳሳላቸውም ልጆችህ ተለይተህ ገንዘብን በእጅህ ሳታደርግ ከቤትህ ውጣ! ቢልህ ይህን ማድረግ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ “ሰንበትን እንደ-ትእዛዜ አክብር” ሲልህ ማክበር ማለት ነው፡፡ “መታዘዝ” ማለት የአንተን ፍላጎት ትተህ የአምላክህን ፍላጎት መፈጸም ማለት ነው፡፡ አስተውሉ ባለጸጋው መድኃኔዓለምን እንዲህ አለው “ከአንተ ጋር እኖር ዘንድ ምን ላድርግ አለው” ወልድ ዋሕድም ባልንጀራህን እንደ-ራስህ ውደድ በፍጹም ልብህ በፍጹም አእምሮህም እግዚአብሔርን አምልክ” አለው፤ ባለ-ጸጋውም ይህንንስ ፈጽሜዋለሁ አለው፡፡ ወልድ ዋሕድም “እውነትህ ነው አንድ ነገር ብቻ ቀረህ ኹሉን ትተህ ተከተለኝ” አለው፤ በዚህን ጊዜ የባለጸጋው ፊት ጠቆረ ብዙ ሀብት ነበረውና ያንን ትቶ ወልድ ዋሕድን መከተል ከብዶታልና፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር አምላካችን “ሀብታም መንግሥተ ሰማያትን ከሚወርስ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይሻላል” ያለው፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ-ኤልያስ ነው፤ ኤልያስ ከብላቴናነቱ ጀምሮ እናቱንና አባቱን ትቶ ለእግዚአብሔር ተለይቶ የታዘዘ ፍፁም እንደ-አምላኩ ከሐሊ የኾነ ነቢይ ነውና፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ-ኤልሳእ ነው፤ ኤልያስ ኤልሳእን ተከተለኝ ባለው ጊዜ የሚያርስባቸውን ከብቶቹን ቀንበር ፈትቶ አርዶ ለሕዝብ መግበቦ እስከመጨረሻው እግዚአብሔርን ተከትሏልና፡፡ መታዘዝ እንደ-አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና እንደ-አቡነ ተክለ ኀይማኖት ነው፤ እነርሱ የዓለምን ፍላጎት ትተው ከሚወዷቸው ቤተሰቦቻቸው ተለይተው ለእግዚአብሔር ሐሳብ ታዝዘዋልና፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ-ጸጋ ዘአብ እና እግዚእ ሐረያ ነው፤ እነርሱ በዓለም ትእዛዝ በሥጋ ፍላጎት ሳይኾን በመለኮት ትእዛዝ ኖረው ኹሉን አሸንፈዋልና፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ ሔኖክ ነው፤ እርሱ የአምላኩን ትእዛዝ ፈጽሞ ዘለዓለማዊ ሥውር ኾኗልና፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ-ኖህ ነው፤ ኖሕ አምላኩን በመታዘዙ ራሱን ከእነ-ቤተሰቡ ከጥፋት ታድጎ ከዘሩ እኛ ተወወልደናልና፡፡

🔯 መታዘዝ እንደ-አቤል ነው፤ አቤል አምላኩ የሚወደውን ንጹህ መሥዋዕት አቅርቦ አምላኩን ደስ አሰኝቷልና፡፡

🔯 “ያለ-መታዘዝስ ምን ትመስላለች!!! በቀጣዩ ሳምንት በጥቂቱ እንገልጻታለን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔርን የሚያምን ትእዛዙን አክብሮ ከፍፁም ሞት ይድናል፡፡ አምላኩን የታዘዘ የአምላኩ የምስጢር ባለሟል ይኾናልና እውነቱን ከሐሰት ይለይ ዘንድ አይጨነቅም፡፡

🔯 ይህ የፍጻሜ ዘመን የፍጻሜውን የቁጣ መቅሠፍት በላዩ እንዳያወርድበት የሚፈልግ እርሱ ይታዘዝ! ሕግንም ነቢያትንም ይጠብቅ፤ አሐቲ ሰንበትን ያክብር በተዋሕዶ እምነት ይኑር፤ ፍፁም እትዮጵያዊ ይኹን፤ በድንግል ማርያም እቅፍ በጽዮን ጉያ ይኑር፤ እንዲህ ከኾነ እርሱ እንደ-አምላኩ ሕያውና ዘለዓለማዊ ይኾናል፤ የሚያስፈራውም አይኖርም፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡

🔯 በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

✡️  ✡️  ✡️  ✡️  ✡️  ✡️  ✡️ !ኤልያስ በማስፈራት ተነሳ!https://youtu.be/0wCOhgOFETwመንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ #ሰንበት  #ተዋሕዶ  #እትዮጵያ        ...
11/05/2026

✡️ ✡️ ✡️ ✡️ ✡️ ✡️ ✡️
!

ኤልያስ በማስፈራት ተነሳ!

https://youtu.be/0wCOhgOFETw

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ #አርማጌዶን

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

Nyd de videoer og den musik, du holder af, upload originalt indhold, og del det hele med venner, familie og verden på YouTube.

09/05/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ቀስተ ደመና ብርሂት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “ወደ-እግዚአብሔር የሚጠጉትን… እንዳያረክሱት ሰንበትን የሚጠብቁትን ቃል ኪዳኔንም የሚይዙትን ሁሉ፥ ወደ-ተቀደሰ ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፥ በቤተ መቅደሴም ደስ አሰኛቸዋለሁ።” (ኢሳ/56/6-7) በሚል ስለ ሰንበት የተሰጠውን ቃል ኪዳን አስቡ፡፡

🔯 አስቀድሞ በነቢይ እንደተነገረው 7ተኛዋን ዕለት ሰንበትን የሚጠብቅ የሚያከብራት በትእዛዘ መለኮት መሠረት ሥርዓቷን የሚፈጽም ሰው ተከታዩ ቃል-ኪዳን ተሰጥቶታል፡-
🟢 1. እግዚአብሔር ብጹዕ እና ቅዱስ ያደርገዋል፤
🟠 2. እግዚአብሔር በቤቱና በቅጥሩ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ ለዘለዓለም የማይጠፋ መታሰቢያና ስም ይሰጠዋል፤
🔴 3. እግዚአብሔር ወደ-ተቀደሰ ተራራው ወደ-ጽዮን ተራራ ያወጣዋል፤
🔵 4. እግዚአብሔር በቤተ መቅደሱ ደስ ያሰኘዋል፤
🔴 5. የሚቃጠለውን መሥዋዕቱን ሌላ መሥዋዕቱን (ምስጋናውን፡ ቁርባኑን፡ መባውን ልመናውን ኹሉ) በመሠዊያው ላይ ይቀበለዋል፤
🟠 6. ከእስራኤል የተበተኑትን የሚሰበስብ ጌታ እግዚአብሔር። ሌሎችን ቤተሰቡን ወደ-ተሰበሰቡት ዘንድ ይሰበስብለታል፤
🟢 7. ሰንበትን ባከበረ በዚያን ጊዜ ብርሃኑ እንደ-ንጋት ይበራል፥ ፈውሱም ፈጥኖ ይበቅላል፥ ጽድቁ በፊቱ ይሄዳል፥ የእግዚአብሔርም ክብር በኋላው ሆኖ ይጠብቀዋል፤
🔵 8. ሰንበትን ባከበረ በዚያን ጊዜ ይጣራል እግዚአብሔርም ይሰማዋል፤ ይጮሀል፡ እርሱም። እነሆኝ ይላል፤
🟢 9. ሰንበትን ባከበረ በዚያን ጊዜ ብርሃኑ በጨለማ ይወጣል ጨለማውም እንደ-ቀትር ይሆናል።
🟠 10. ሰንበትን ባከበረ ጊዜ፡ እግዚአብሔር ሁልጊዜ ይመራዋል፤ ነፍስህንም በመልካም ነገር ያጠግበዋል አጥንቱንም ያጠናል፤ እርሱም እንደሚጠጣ ገነት፥ ውኃውም እንደማያቋርጥ ምንጭ ይኾናል፤
🔴 11. ከአንተ መታዘዝ የተነሳ፡ ከዱሮ ዘመን የፈረሱት ስፍራዎች ይሠራሉ፥ የብዙ ትውልድም መሠረት ይታነጻል፤ አንተም። ሰባራውን ጠጋኝ፥ የመኖሪያ መንገድን አዳሽ ትባላለህ፤
🔵 12. ሰንበትን ባከበርህ በዚያን ጊዜ በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፥ በምድርም ከፍታዎች ላይ ያወጣሀል የአባትህንም የያዕቆብን ርስት ያበላሀል፡፡ ኢሳ/56/1-8) እና ኢሳ ም/58/8-14)

🔯 ስለዚህም ኹላችንም አሐቲ ሰንበትን በማክበር የስሉሥ ቅዱስ ኀያል አጋዕዝት ሥላሴ ቃል ኪዳን ተካፋዮች መኾን ይኖርብናል፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ የሰው ልጅ ጦርነት ሲያይል እግዚአብሔር መጣ ሲል፡ ቀዝቀዝ ሲል ደግሞ ጊዜው ገና ነው የምጥ ሰሞን ነው እያለ ውሀ እያሳሳቀ እንደሚወስድ እንዲሁ እንደ-ዘመነ ኖሕ የተታለሉት እንደተታለሉ ወዳልፈለጓት ሲኦል ይሸኛሉ፡፡ እትዮጵያውያን የኾናችሁ ኹላችሁ ግን ዘወትር ንቁ ሌባ በምን ሰዓት እንዲመጣ እንደማያውቅ ጌታ በድንገት እንዳይደርስባችሁ ተብሎ የተጻፈ ቢኾንም፡ እኛ ግን ልባቸውን ለከፈቱ የምጽአቱንአዋጅና ምስጢራት የገለጽንላችሁ በመኾኑ ሥጋና ነፍሳችሁን በንስሐ አጽድታችሁ የመለኮትን ፍርድ ተከታተሉ፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

02/05/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ርትዕት ተዋሕዶ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “የተቀደሰውን ሰንበትህን አስታወቅካቸው ትእዛዝ እና ሥርዓትህን ሕግህንም በባሪያህ በሙሴ እጅ አዘዝካቸው” (ነህ.9/14) ተብሎ የተጻፈውን አስተውሉ! የተቀደሰችው ሰንበት አንዲት እርሷም ወልድ ዋሕድ ከሥራው ኹሉ ዐርፎ የባረካትና የቀደሳት ሰባተኛዋ ዕለት ሰንበት መኾኗን ከቃሉ እንረዳለን፡፡:

🔯 ካለፉት ኹለት ሳምንታት ወዲህ በጽሑፋችን ላይ የቤልሆር ሰልፍ ኾኖ ለማወክ ጥረት በማድረጉ የጠበቃችሁትን ያህል አዋጅ እንዳላወጅን ይሰማናል፡፡ የኾነው ኾኖ፡ ዲያብሎስ ቢያጓራ ጋኔን ቢያሽቃጥር የሚሰማው የለምና እኛስ በእርጋታ በጽዮን መንገድ እንጓዛለን፡፡ ነገር ግን ሐሳባችንን በቀጣዩ ግጥም ለቀጣይ ሳምንት ቀጠሮ እንይዝ ዘንድ ወደናል፡-

የቤልሆር በኩር ልጅ የናምሩድ ወታደር፣
…ሰማይን ሊወጋ የወረወረው ጦር፤
ሰማይን ሳይወጋ ጦሩ ተመልሶ፣
ልጆቹን ፈጀና አወጀበት ለቅሶ፡፡
ልቡ እብሪት ተሞልቶ ነፍሱም በአመጻ፣
ሥጋው ሥጋት ልትሆን እጁም ጦርን ቀርጻ፣
እርሱ በትእቢቱ ከሰማይ ላይ ወርዶ፣
ከክፋቱ መዝገብ ተንኮልን አቅዶ፤
ሰማያውያኑን ምድራውያን ሊያደርግ፣
ሰንበትን አስክዶ በጭቃ እሾህ ሊመርግ፤
ተዋሕዶን ወግቶ ከሰማይ ላይ ሊጥል፣
ደንጊያ ግንብ ሳይቀር ፎቅን ሲቀጣጥል፤
ሰማይን ላያየው በሰማይ ላይ ላይደርስ፣
ጦር መስበቅ ጦር ማሾል እርሱ ራሱ ሊፈርስ፣
ሰማይ ይወጋ ዘንድ ከንቱ የተመኘው፣
የገዛ ራሱ ጦር ቤቱን ቢጎበኘው፤
ሥጋው ነፍሱን ይዞ በሲኦል አገኘው፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ የሰው ልጅ ጦርነት ሲያይል እግዚአብሔር መጣ ሲል፡ ቀዝቀዝ ሲል ደግሞ ጊዜው ገና ነው የምጥ ሰሞን ነው እያለ ውሀ እያሳሳቀ እንደሚወስድ እንዲሁ የተታለሉት እንደተታለሉ ወዳልፈለጓት ሲኦል ይሸኛሉ፡፡

🔯 እትዮጵያውያን የኾናችሁ ኹላችሁ ግን ዘወትር ንቁ ሌባ በምን ሰዓት እንዲመጣ እንደማያውቅ ጌታ በድንገት እንዳይደርስባችሁ ተብሎ የተጻፈ ቢኾንም፡ እኛ ግን ልባቸውን ለከፈቱ የምጽአቱን አዋጅና ምስጢራት የገለጽንላችሁ በመኾኑ ሥጋና ነፍሳችሁን በንስሐ አጽድታችሁ የመለኮትን ፍርድ ተከታተሉ፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
Share:
Forward:
Add members
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
only every Sunday
ዘወትር እሑድ ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

25/04/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 ”አምላክህ እንዳዘዘህ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ ጠብቅ።” (ዘዳግም 5/12) ይህ ቃል እግዚአብሔር መለኮት በጽላተ እግዚአብሔር ላይ “ከእኔ ሌላ አምላክ አይኹንልህ”፣ “በከንቱ በስሜ አትማል” ከሚለው ቀጥሎ የጻፈው ሶስተኛው ትእዛዝ ነው፡፡ ይህ መለኮታዊ ትእዛዝ ለሚተገብረው ሕይወት ሲኾን፤ ለማይታዘዝ ደግሞ ያለመታዘዙን ፍሬ ሰይፍን የሚበላበት የፍርድ ቃል ነው፡፡ የሰንበትን ዕለት ታመሰግናት ዘንድ ትጋ የምትለዋ ትእዛዝ በሰንበት የተመሰሉት እርሱ አጋዕዝት ሥላሴ እና ቤዛዊተ ዓለም እግዝእትነ ማርያም በመኾናቸው አምላክህን እግዚአብሔርን እናትህን መለኮት የተዋሐዳትን መለኮታዊት እግዝእትነ ማርያም ድንግልን አመስግንባት ማለት ነው፡፡

🔯 በመሠረቱ እግዚአብሔር የማይመሰገንባቸው ቀናት፣ ሳምንታት፣ ወራት፣ ዓመታት እና ሱባኤያት የሉም፡፡ ነገር ግን ሰባተኛዋ ዕለት የእግዚአብሔር የመንግሥቱ ቀን ናትና ከዕለታት ኹሉ ለይቶ ያከበራት በእስራኤልና በገባሬ ኩሉ ዓለማት መለኮት መካከል ምልክት አድርጎ የሠየማት ልዩ ዕለት በመኾኗ እግዚአብሔር አምላክ በልዩ ኹኔታ ይመሰገንባት ዘንድ፡ ፍጥረት ኹሉ ሥራን ከመሥራት ታቅቦ በዚህች ቅድስት ዕለት ሥጋውንና ነፍሱን ለፈጠረው፡ ጤና ለሰጠው፡ ጸጋንና በረከትን ላደለው እድሜውን ለሰፈረለት አምላክ ለእግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ እና ንጽህት፣ ክብርት፣ ርኅርኅት፣ ብጽዕት፣ ጽርህይት ወቅድስት ለኾነችው ቤዛ አማልክት ድንግል ማርያም ምስጋና እና ቁርባን የሚቀርብባት ፍጽምት ልዩ ዕለት ናት፡፡

🔯 ማንም ሰው ቢኾን ሰባተኛይቱን ዕለት በዕረፍት ኾኖ ሰንበትን በማክበሩ የእግዚአብሔርን ከፍታ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ የሚችል ወይም የድንግል ማርያምን ክብር ከፍ ከፍ ወይም ዝቅ ሊያደርግ አይቻለውም፤ እነርሱ ለዘለዓለም ከፍ ከፍ ያሉ ለዘለዓለምም የከበሩ ናቸውና፡፡ ይልቁንም በዚህች ክብርት ዕለት አምላኩን ያመሰገነ እርሱ ራሱ ከፍ ከፍ ይላል፤ ሰንበትን ባያከብር ደግሞ እርሱ ራሱ በተጠመደበት ኀጢአት ተይዞ ይወድቅባታል፤ ይዋረድባታል እንጂ ሌላውን ሰው ለማዋረድ አይችልም፡፡ ስለዚህም፡ መከበርን ማግኘት የሚወድድ ሰንበትን ያክብር፤ ጸጋና በረከት ማግኘት የሚፈልግ ሰንበትን ያክብር፤ መመስገን ከፍ ከፍማለት የሚሻ አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴንና ማርያም ድንግልን ያመስግን፤ የሥጋና የነፍስ ዕረፍት የሚፈልግ በሰንበት ዕረፍት ያድርግ፡፡

🔯 እትዮጵያውያን እትዮጵያዊቷን ሰንበት (ቅዳሜን) ያከብራሉ፤ እትዮጵያውያን ያልኾኑ ደግሞ ከእግዚአብሔር ሰንበት ተለይተው ሰንበት ያልኾኑ ቀናትን ሰንበት እያሉ ከእግዚአብሔር ለተለየ ወገን ይገዛሉ፡፡ እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ እንደ-ትእዛዙ ፍርዱን፣ ሕጉን፣ ትእዛዛቱንና ሰንበታቱን የሚጠብቅ በረከት ሲያገኝ ከዚህ ፈቀቅ ያለ ደግሞ በበረከት ፋንታ መቅሠፍትን ይቀበላል፤ እንዲህ ተጽፏልና፡- መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን። አንሄድባትም አሉ። እኔም። የመለከቱን ድምፅ አድምጡ ብዬ ጠባቆችን ሾምሁባችሁ፤ እነርሱ ግን። አናደምጥም አሉ። አሕዛብ ሆይ፥ ስለዚህ ስሙ፤ ማኅበር ሆይ፥ እነዚያ የሚያገኛቸውን እወቁ። ምድር ሆይ፥ ስሚ፤ እነሆ፥ ቃሌን ስላልሰሙ ሕጌንም ስለ ጣሉ በዚህ ሕዝብ ላይ የአሳባቸውን ፍሬ ክፉን ነገር አመጣባቸዋለሁ።” ኤር 6/17-19)
ስለዚህም የዚህ የፍጻሜ ዘመን ሰው በመልካሚቱ መንገድ በተዋሕዶ እምነት እና በመልካሚቱ ዕረፍት በሰንበት ለመመላለስ ባለመፍቀዱ የሐሳቡን ክፉ ፍሬ እየተመገበ ይገኛል፡፡ ለነፍሳችሁ ዕረፍት የምትኾነውን ሰንበትን እንደ-ትእዛዘ እግዚአብሔር በማክበር መክበር ይገባል እንጂ ባለመታዘዝ ጠንቅ ዕረፍት ማጣት መልካም አይደለም፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ የሰንበትን ዕረፍት ዋጋ እየሰጠ መቅሠፍቱንም ባልታዘዙት ላይ በድንቅ እያወረደ ይገኛልና እትዮጵያውያን በእትዮጵያዊ ልቦና ተገኝታችሁ ከቁጣው መዓት ትድኑ ዘንድ ጠርተናችኋል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
Share:
Forward:
Add members
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
only every Sunday
ዘወትር እሑድ ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

18/04/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሚያዝያ 10ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

✡ “ሰዱሰ፡ ዕለተ፡ ትገብር፡ ግብረከ፡ ወበሳብዕት፡ ዕለት፡ ሰንበት፡ ይእቲ፡ ወዕረፍት፡ ቅድስተ፡ ተሰምየት፡ ለእግዚአብሔር፡ ኵሎ፡ ግብረ፡ ኢትግበሩ፡ እስመ፡ ሰንበቱ፡ ለእግዚአብሔር፡ ውእቱ፡ በኵሉ፡ በሐውርቲክሙ።” (ዘሌ/23/3) በሚል በነቢያት የተጻፈውን አስተውሉ! በተለይም “ኵሎ፡ ግብረ፡ ኢትግበሩ፡ እስመ፡ ሰንበቱ፡ ለእግዚአብሔር፡” (የእግዚአብሔር ሰንበቱ ናትና ሥራን ኹሉ አትሥሩባት) የምትለዋ ሐረግ በእጅጉ አካልን እና ነፍስን የምትሞላ ናት፡፡ ከዚህ ሐረግ የምንረዳው ሰባተኛዋ ዕለት “የእግዚአብሔር ሰንበት” መኾኗን ሲኾን፤ እሑድ ደግሞ ሰው ለራሱ ዓለማዊ ዓላማ ሰው የሰው ሰንበት ብሎ የሠየማት መኾኗን መረዳት አያዳግትም፡፡

✡ ባለፈው ሳምንት የፈሪሳውያን ልጆች “ሰንበት ሥዑር” ወይም በገጠሪቱ እትዮጵያ “ቅዳሜ ሹር” እያሉ የሚጠሯት የፋሲካ ሰንበት ነበረች፡፡ በዚያች ዕለት እኛ ለብዙዎች መመለሻ ለአመጸኞች ደግሞ ፍርድ የኾነ ቃል አስተላልፈን ነበር፡፡ ታድያ፡ በአቅራቢያችን ላለች አንዲት ሴት “አክፍሎት ከረቡዕ ለኀሙስ አጥቢያ ማታ ተበልቶ ዐርብ አልፎ ሰንበት ሲጀምር መመገብ ተገቢ መኾኑን፤ እና በሰንበት እንደማይጾም” አውጀንላት ነበር፡፡ እርሷም ከእባብ በለሰለሰ አንደበቷ “አይደል!!!” እያለች የገባት መስላ መቀበሏን ገለጸች፡፡ እኛም ከልቧ እንዳልኾነ መንፈሳችን በመረዳቱ ተግባሯን ተከታተልን፡፡ እርሷም ዐርብ ማታ ራቷን ግጥም አድርጋ በልታ በፋሲካ ሰንበት ጾመኛ ኾና ተገኘች፤ የምትቀበለው በቴሌቪዥንና በቤተ ክርስቲያን የሚነገረውን የስህተት አስተምህሮ ነውና፡፡

✡ በልጅነታችን ዘመን፡ አባቶቻችን በስምንተኛው ሺህ ካሕን ይጠፋል ሲሉን “በእውኑ የክሕነት ትምሕርት የሚማር ስለማይኖር” ወይም “ካሕናት ኹሉ ተገድለው ስለሚያልቁ” ነውን? እያልን በውስጣችን እናመላልስ ነበር፡፡ አሁን ሲገባን ከቅዱሳን አባቶች ስንረዳ ሲገባን ለካስ ካሕናቱም እግዚአብሔርን ክደው የአምልኮ መልክ ይዘው “ሀገራቸው እና እምነታቸው ሆዳቸው፤” ኾኖላቸው ስለተገኙ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የብዙኃን ካሕናት አምልኮ ሆድ እና ገንዘብ ነው፤ ለእነርሱ እትዮጵያ ማለት ሆዳቸው ነው፤ ለእነርሱ ተዋሕዶ ማለት ሆዳቸው ነው፤ ለእነርሱ ሰንበት ማለት ሆዳቸው ነው፤ ለእነርሱ እግዚአብሔር ማለት ሆዳቸው ነው፤ ለእነርሱ ድንግል ማርያም ማለት ሆዳቸው ነው፡፡ ስለዚህም ሆዳቸው እንዳይጎድልባቸው ሲሉ ማንኛውንም ሕገ-ወጥ ነገር ይፈጽማሉ፤ የስህተት ትምህርት ማረም አይፈልጉም፤ ምክንያቱም፡ ሕዝቡ ለካስ ሲዋሹን ኖረዋል ብሎ በእነርሱ ላይ እምነት አጥቶ ለሆዳቸው የሚሰጣቸውን ገንዘብ እንዳይከለክላቸው ነው፡፡

✡ ስለእነዚህ ሆዳም የበዓል ካሕናት ነቢያት አስቀድመው እንዲህ ጽፈዋል፡-
“እናንተ ካህናት ሆይ፥ ይህ ትእዛዝ ለእናንተ ነው። 2ለስሜ ክብር ትሰጡ ዘንድ ባትሰሙ፥ በልባችሁም ባታደርጉት፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ እርግማን እሰድድባችኋለሁ፥ በረከታችሁንም እረግማታለሁ፤ አሁንም በልባችሁ አላደረጋችሁትምና እኔ ረግሜአታለሁ። እነሆ፥ ክንዳችሁን እገሥጻለሁ፥ የመሥዋዕታችሁንም ፋንድያ በፊታችሁ ላይ እበትናለሁ፤ ከእርሱም ጋር በአንድነት ትወሰዳላችሁ። እናንተ ከመንገዱ ፈቀቅ ብላችኋል፤ በሕግም ብዙ ሰዎችን አሰናክላችኋል፤ የሌዊንም ቃል ኪዳን አስነውራችኋል፥… ስለዚህ መንገዴን እንዳልጠበቃችሁ፥ በሕግም ለሰው ፊት እንዳዳላችሁ መጠን፥ እኔ ደግሞ በሕዝብ ሁሉ ፊት የተናቃችሁና የተዋረዳችሁ አድርጌአችኋለሁ።” (ሚልኪያስ 2/1-9)
በዱሮ ጊዜም በዚህ ዘመን ያሉቱን ብዙሃኑን ካሕናት የመሰሉ የዳጎን ካህናት የሚባሉ ነበሩ፤ (ቀ/ሳሙኤል 5/5) ያገለግሉ የነበሩት የፍልስጤማውያንን ጣኦት ዳጎንን ነበር፡፡ በእዮርበአምም ዘመን በኮረብታዎች ላይ የጣኦት መስገጃ ተዘጋጅቶላቸው ዲያብሎስን ያገለግሉ የነበሩ ካህናተ ጣኦት ነበሩ፡፡ በኤልያስም ዘመን የጃዛቤልና የአክአብ የበዓል ጣኦት አምላኪዎች የነበሩ ሲኾን፤ ነቢዩ ኤልያስ በቀርሜሎስ ተራራ ላይ መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ ከእነ-ነቢያቶቻቸው በቂሶን ወንዝ ዳርቻ እንዳሳረዳቸው በመጽሐፈ ነገሥት ላይ ተጽፎ እናገኛለን፡፡

✡ እግዚአብሔር መለኮት በዚህም ዘመን ባሉት ካሕናት ላይ እንዲህ ትንቢት ተናግሯል፡-“እጄን በይሑዳ ላይ በእየሩሳሌምም በሚኖሩት ኹሉ ላይ እዘረጋለሁ፡ ከዚህም ስፍራ የበዓልን ቅሬታና የጣኦታቱን ካህናት ስም አጠፋለሁ (ሶፎ/1/14) ተብሎ የተጻፈውን ልብ በሉ፡፡ ለነገሩማ “እነሆ ወደ-እየሩሳሌም እንወጣለን የሰው ልጅም ለካህናት አለቃዎችና ለጸሐፊዎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል” (ማቴ/20/18) ብሎ አምላካችን የተናገረ አይደለምን; በዚህም ዘመን ያሉት ብዙሃን ካህናት የቀደመውን አባቶቻቸውን ነውር ተግባር በማድረግ አምላክን በመካድ ሆዳቸውን በማምለክ የሚያስንቁ እንጂ የሚያንሱ አይደሉም፡፡
እጅግ የገረመን ግን ብዙኃኑ ሕዝብ አምላኩን እግዚአብሔርን ትቶ ካሕናቱን አምላኩ ማድረጉ ነው፡፡ ከላይ የነገርናችሁ ሴት የዚህ ዘመን ካህናት በቴሌቪዥንና በአካል ሰንበት ተሽራለች፡ በፋሲካ ሰንበት ሥራ ካልሠራሽ አትጸድቂም ብለዋት በሰንበት ዕለት ጉሮሮዋን ዘግታ ዋለች፡፡ የዚህች ሴት አምላኮቿ የበዓል ካህናት እንጂ እግዚአብሔር እንዳልኾነ ከተግባሯ መረዳት ይቻላል፡፡ ለነገሩማ ከእናንተም መካከል የምታነብቡ ነገር ግን በተግባር የምትቃረኑ፤ የምትሰሙ ነገር ግን በተግባር የማታዳምጡ ትኖራላችሁ፡፡
ነገር ግን እናንተ “እግዚአብሔር የሾማቸው ካሕናት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ” (ዳን/3/83) እንደተባለ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑትን እና ሰውን የሚያመሰግኑትን ካህናትና ካህናት መሰል ሰዎች ለይታችሁ የቅዱሳንን መለኮታዊ ቃል ብቻ ተከተሉ፡፡

✡ እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ የበዓል ካህናቱን ወደ-ጥልቁ እየወረወረ ተከታዮቻቸውንም ተወርዋሪዎቹን ይከተሉ ዘንድ እያስከተታቸው ይገኛል፡፡

✡ በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
Share:
Forward:
Add members
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
only every Sunday
ዘወትር እሑድ ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

11/04/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት መቅደሰ ጽዮን ወእየሩሳሌም አደረሰን አደረሳችሁ!!!

✡ ሰንበት ስዑር ስላለመኾኗ 10 መለኮታዊ ማስረጃዎች፣
በየዓመቱ በፋሲካ ጊዜ የምትገኘውን ሰንበት ቅዳሜ ስዑር ወይም ቅዳሜ ሹር እያላችሁ በሕገ እግዚአብሔር እና በትእዛዛቱ ላይ ስታምጹ ኖራችኋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በኋላ ሰንበት ራሷን ታስከብር ዘንድ ምድሪቱን በድንቅ የቁጣዋ መቅሠፍት እየጎበኘች ነውና ይድን ዘንድ የወደደ ይህን አንብቦ፣ ሰምቶ እና አድምጦ ወደ-እግዚአብሔር ይመለስ፡፡

✡ 1ኛ. እግዚአብሔር የሠራውን ሥራ ኹሉ በሰባተኛይቱ ዕለት ፈጽሞ በርሷ ስላረፈ የባረካትና የቀደሳት ዕለት መኾኗ፤ (ዘፍጥረት 2/2-3)
እርሱ ራሱ ከሚረክስ በቀር እግዚአብሔር የባረከውን ማንም ማርከስ አይችልም፡፡ ሰንበትን የሚያከብር ሲከብር፡ ሰንበትን የማያከብር ደግሞ ራሱ ይዋረዳል፡፡ ሰዎች ግን የሰውን ሰንበት ያከብራሉ፤ እግዚአብሔር እሑድን ባረካት ቀደሳትም ዐረፈባትም ተብሎ ሳይጻፍ፡ ሰዎች በገዛ ፈቃዳቸው ሥላሴን ለመቃረን ሲሉ የሰንበት አቻ አድርገው እሑድን ሰንበታችን ብለው ለማክበር ተነሱ፡፡ ነገር ግን ይህ የውድቀታቸው መጀመሪያና መጨረሻ በመኾኑ እነሆ በዚህ ዘመን መላ ምድሪቱ በሰንበት ላይ ከተፈጸመው አመጻ የተነሳ በመቅሠፍት እየተጎበኘች መኾኑን ዕናያለን፡፡

✡ 2ኛ. ሰንበት ሰባት ሰባት ተደርጎ የእግዚአብሔር የአምልኮቱ እና የሕጉ የዘመናት አከፋፈል ሱባኤ የሚቆጠርባት የሕግና የዘመን መሠረት መኾኗ፤ (ኩፋሌ 1/1 እና 2/1)
እግዚአብሔር መለኮት ለሙሴ ትእዛዛቱ የተጻፈበባቸው ኹለት የእንቁ ጽላቶች የሰጠው ሲኾን፤ ከእነዚህ ትእዛዛት መካከል አንዷ ሰንበትን እንዳረፍኩባት ዕረፉባት የምትል ትእዛዝ ናት፡፡ ይህች ሰንበት ሰባተኛ ዕለት ስትኾን ዘመናት ኹሉ ከርሷ በመነሳት ይቆጠራሉ፡፡ ለምሳሌ፡- አንድ ሳምንት ከእሑድ ጀምሮ እስከ ሰባተኛዋ ዕለት ቅዳሜ (ሰንበት) አንድ ሱባኤ፤ እንዲህ እያላችሁ 7 7 ስትደምሩ ኹለተኛና ሶስተኛ ሱባኤ እያለ ይቀጥላል፡፡ ከዚያም በሰባት ዓመታት ተቆጥሮ 7 ጊዜ 7 49 ዓመታት ተቆጥረው 50ኛው ዓመት ኢዮቤልዩ ይባላል፡፡ ስለዚህ በእንቁ ጽላቶቹ ላይ የዘመናት አከፋፈል የተጻፈው ከሰንበት ሱባኤ ተነስቶ ሲኾን፤ ትውልድም እንዲሁ የመጀመሪያው ትውልድ ኹለተኛው ትውልድ እየተባለ በሱባኤ አቆጣጠር ይቆጠራል፡፡ ለምሳሌ ኖሕ የነበረው በስንተኛው ሱባኤ እንደነበረ፡ ሔኖክም፡ መልከ-ጼዴቅም፡ አብርሀምም ይስሀቅም፡ ያዕቆብም፡ እንዲሁ የኖሩበት ዘመን በሰንበት ሱባኤ ይቆጠራል፡፡ ይህም ማለት፡ ኹለት ሰንበት የምትሉ ከኾነ ግን የሰንበት ሱባኤ አቆጣጠር ይፋለሳል፡፡ ለምን ቢሉ፡ መጀመሪያ ከየትኛው ቀን ሱባኤ እንደምትጀምሩ ግራ ትጋባላችሁ፤ በመቀጠልም ከጾም በኋላ በሰባተኛዋ ዕለት መመገብ ሲኖርባችሁ እናንተ ግን ቅዳሜንም እሑድንም ሰንበት የምትሉ ኹለት ቀን ስለምትመገቡ እግዚአብሔር በ6 ቀናት ሥራውን ፈጽሞ በ7ተኛዋ ዕለት ዕረፍት ማድረጉን የሚመሰክረውን ሱባኤያችሁን ማከናወን አትችሉም፡፡

✡ 3ኛ. የእግዚአብሔርን የመሐላውን ሥርዓት ሰንበትን የሚተዉ ሰዎች በጠላቶቻቸው እጅ ወድቀው በመከራ ተይዘው የሚጠፉ ስለመኾናቸው፤ (ኩፋሌ 1/9)
ሰንበትን የማያከብሩ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት የተጠሉ በሰይጣን የተወደዱ ይኾናሉና የሚወድዳቸው ክፉው ጠላት አሳልፎ ለመከራ ይሰጣቸዋል፡፡ በዘሌዋውያን ም/26 ላይ እንደተመለከተው እግዚአብሔር በሰይፍ ለሚገድሏቸው አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ሰንበትን አለማክበርን ቢቀጥሉ ቢያምጹም 7 እጥፍ መቅሠፍትን እንደሚያወርድባቸው በመለኮታዊ የመሐላ ቃሉ ተናግሯል፡፡ ስለዚህም ነው፡ የሰው ልጅ መቅሠፍት እየወረደበት እግዚአብሔር ስለምን ተወን ይላል፤ እርሱ በሰንበት ላይ ያደረገው አመጻ ግን ለርሱ ትክክል ነው፡፡ ማንም ቢኾን በሰንበት ላይ በማመጹ እግዚአብሔር ለሚያሳድደው አሳልፎ ሲሰጠው ኦነግ ሸኔ ገደለን፣ ካሕናት ታረዱ እነ-እገሊት ተነወሩ፣ ፓኪስታን በሚሳኤል መታችን፣ ዐረቦች ጨረሱን፣ ሺፍቶች ገደሉን፣ አውሬ ሠለጠነብን ወዘተ… ማለት በራስ ላይ እንደ-መቀለድ መኾኑን ማስተዋል ይገባል፡፡

✡ 4ኛ. ሰንበት እግዚአብሔር በ6 ቀናት ሰማይንና ምድርን በውስጣቸውም ያሉትን ከፈጠረ በኋላ ለፈጠረው ፍጥረት የከበረ በዓል ይደረግባት ዘንድ የሰጣት ዕለት በመኾኗ የሚሠራባትም የሚሽራትም ሰው ለዘለዓለም ሞትን ይሙት ተብሎ መለኮታዊ እርግማን የተላለፈባት ዕለት መኾኗ፤ (ኩፋሌ 3/11-13 ም34/11-19))
እናንተ በየዓመቱ በፋሲካ ጊዜ ያለችው ሰንበት ሥራ ይሠራባት፡ ያልሻራት፡ አጥር ያላጠረባት፡ ቁፋሮ ያልቆፈረባት፡ ምንጥር ያልመነጠረባት፡ ያልነገደ እና ሥራ የተባለውን ኹሉ ያልሠራባት የተረገመ ይኹን ትላላችሁ፡፡ ነገር ግን ይህ እርግማን የሰቃሊያነ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ የፈሪሳውያንና የሮማውያን ቅሪቶች ወይም ልጆች እርግማን እንጂ የእግዚአብሔር እርግማን አይደለምና ሰንበትን በሚያከብሩት ላይ የሚያስከትለው ክፉ ነገር የለም፡፡
ነገር ግን፡ የእግዚአብሔር እርግማን እንዲህ ይላል፡- በሰንበት ጾምን የሚጾም፣ በሰንበት የሚሸጥና የሚለውጥ ገበያም የሚያደርግባት፣ በሰንበት ስለ-ሥራ ነገር የሚነጋገርባት፣ በሰንበት ዓሳ የሚያጠምድባት፣ አደን የሚያድንባት፣ ወፍንም እንስሳንም ማንኛውንም ፍጥረት መትቶ የሚገድልባት፣ በሰባተኛዋ ዕለት/ቅዳሜ ዕረፍትን የማያደርግ ሰንበትን የሚሽር ሰው ኹሉ ለዘለዓለም ሞትን ይሙት ተብሎ ተጽፏል፡፡
ስለዚህም፡ በፋሲካ ሰንበት ሥራን እንሠራለን የምትሉት መድኃኔዓለምን የሰቀሉትን ትእዛዝ ትጠብቁ ዘንድ አላችሁ እንጂ በመለኮት ትእዛዝ ውስጥ የሌላችሁ አመጸኞች ናችሁ፡፡
የአክፍሎት ጾምን በተመለከተ፡ አክፍሎት የሚከፈለው ረቡዕ ለኀሙስ አጥቢያ ማታ የጌታ ራት ጉልባን ከተበላ በኋላ እስከ ሶስተኛው ቀን ዐርብ ድረስ ተጾሞ ዐርብ አልፎ ቅዳሜ ሲጀምር ከ12 ሰዓት በኋላ መብላት ይገባል፡፡ ነገር ግን ኀሙስ ለዐርብ አጥቢያ ማታ በልቶ ሰንበትንም ጾሞ እሑድ ሌሊት መብላት በሰንበት አትጹሙ የተባለውን እናመልከዋለን የምትሉትን አምላክ ትእዛዝ መተላለፍ ነውና ታደርጉት ዘንድ ተቆጠቡ፡፡

✡ 5ኛ. ሰንበትን የሚጠብቅ፡ ከሥራም የሚያርፍባት ሰው በዘመኑ ኹሉ እንደ-አምላኩ እንደ-ሥላሴ የተቀደሰና የተባረከ (ቅዱስ) መኾኑ፤ (ኩፋሌ 3/14፣ ኢሳይያስ 56/2-3))
አንድ ሰው ቅዱስ ወይም ብፁዕ ከሚያሰኙት ምግባራት መካከል የመጀመሪያው ሰንበትን ማክበሩ ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ “ሰንበትን የሚያከብር እጁንም ከክፉ የሚጠብቅ ብጹዕ ነው” ይላል፡፡ በሌላ አንጻር ነቢዩ ኩፋሌ እንደጻፈው ደግሞ አጋዕዝት ሥላሴ ሰባተኛዋን ዕለት ሰንበትን የሚያከብራት ከእኛ ጋር አብሮ ያርፋልና እንደ-እኛ የተባረከ የተቀደሰ ይኾናል በማለት ጽፏል፡፡
ስለዚህ በዚህ ዘመን ሰንበትን ሳያከብሩ ብጹዕ ወቅዱስ አባ እገሌ የሚባሉት ኹሉ ፍፁም በእግዚአብሔር ፊት ቅድስና የሌላቸው መኾናቸውን ከዚህ መለኮታዊ ቃል ለመረዳት እንችላለን፡፡ በተዋሕዶ እምነት መገኘት፣ ሕግንም ነቢያትንም መጠበቅ እና ሰንበትን እንደ-ትእዛዙ ማክበር እንደ-ሥላሴ አንድም ሶስትም አድርገን የምናምንባቸው ናቸው፡፡ በዚህ የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል “እንደ-እኛ የተቀደሰ ይኾናል” በሚለው ሐረግ ውስጥ “እኛ” የተባለው ሥላሴ ሲኾን፤ ሰንበትን የሚሚያከብር ሰው ቅዱስ መኾኑን ያስረዳናል፡፡

✡ 6ኛ. ሰንበት የእስራኤል ሕዝብ (እትዮጵያውያን) ብቻ ዕረፍት እንድናደርግባት የተሰጠች ዕለት እንጂ ለአሕዛበ ምድር ያልተሰጠች መኾኗ፤ (ኩፋሌ 3/18 እና እብራውያን 4/9)
ያልተጻፈው የመለኮት ቃል እንደተጠበቀ ኾኖ፡ በቀደሙ መልእክቶቻችን እና አዋጆቻችን እስራኤል ማለት ቅድስት ምድር እትዮጵያ እስራኤላውያን ማለትም የእትዮጵያ ሕዝብ መኾኑን ከበቂ ማስረጃ ጋር ገልጸንላችኋል፡፡
ሰንበትን እንደ-ፈቃደ ሥላሴ የሚያከብሯት በተዋሕዶ እምነት የጸኑና ከገንዘብ ይልቅ እግዚአብሔርን የመረጡ፤ ሰውን በፈንጂ በኒውክሌር፣ በድሮን፣ በጀት፣ በሚሳኤል፣ ከመርከብ በሚወረወር አረር፣ በመርዛማ ኬሚካል፣ በጩቤና በሽጉጥ በግፍ የሚገድሉት ሳይኾኑ፡ ይልቁኑም ሕግን እና ነቢያትን የሚጠብቁ፤ ሰባተኛዋን ዕለት በፍፁም እርጋታ የሚያከብሩ የእግዚአብሔር ሕዝብ እትዮጵያውያን ናቸው፡፡ ይህም ማለት፡ በዕብራውያን ም/4/9 “የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል” በማለት በገሃድ የሚገልጽ ሲኾን፣ ኩፋሌ ደግሞ “ሰንበት ከእስራኤል በቀር ለአሕዛብ አልተሰጠችም” በማለት ጽፏል፡፡
ስለዚህም የእግዚአብሔር ያልኾነን ሕዝብ ሰንበትን አክብር ብትሉት ያከብር ዘንድ አይቻለውም፤ ሰንበት ለርሱ አልተሰጠችውምና፡፡ በመኾኑም፡ እትዮጵያውያን ኹላችን የተሰጠችንን የእግዚአብሔር ዕረፍት አብረን ከአምላካችን ጋር ማክበር ይገባናል፤ ይህን የማያደርግ ቢኖር፡ እኔ የእግዚአብሔር ልጅ እትዮጵያዊይም አይደለሁም ማለቱን ማስተዋል ይገባል፡፡

✡ 7ኛ. ሰንበት የከበረች የእግዚአብሔር መንግሥት ዕለት መኾኗ፤ (ኩፋሌ 34/15)
ሰንበት የምስጋና፣ የመከበር እና የበረከት ዕለት እንዲሁም የአጋዕዝት ዓለም ሥላሴ የመንግሥቱ ቀን መኾኗን ኩፋሌ ቁልጭ አድርጎ ጽፎልናል፡፡ በሰንበት ማድረግ የሚገባውን እና የማይገባውን ኹሉ በኩፋሌ ም/34 ላይ የተመለከተ ሲኾን፤ ሰንበትን የሚያከብር በመንግሥተ ሥላሴ ውስጥ ከአምላኩ ጋር ዕያረፈ መኾኑን በአዋጃችን መግለጽ እንወዳለን፡፡

✡ 8ኛ. በሰንበት የሚያርፉት በእውነት እግዚአብሔርን የሚያምኑ ስለመኾናቸውና የሰንበት ዕረፍት የምሥራች የተሰበከላቸው ሰንበትን ካላከበሩ ባለመታዘዝ ጠንቅ ወደ-እግዚአብሔር የዘለዓለም ዕረፍት የማይገቡ ስለመኾናቸው፤ (እብራውያን 4/3-6)
እግዚአብሔርን የሚያምን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ይጠብቃል፤ እግዚአብሔርን የሚክድ ትእዛዛቱን ይሸሻል፡፡ ስለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሰንበትን ለማክበር ልባችሁን እልኸኛ አታድርጉ ይላል፡፡ አማን በአማን ሰንበትን የማያከብር ሰው ባለመታዘዝ ጠንቅ በመንግሥተ ሰማያት አይገባም፡፡ ስለዚህ በሰንበት ከሸቀጥ ጋር መዋል ማደራችሁን ትታችሁ በመታዘዝ ሰንበትን አክብራችሁ ከመቅሠፍት ይልቅ በረከትን አግኙ፡፡

✡ 9ኛ. ሐዋርያት/ደቀ-መዛሙርት እና እነ-መግደላዊት ማርያም ከሥቅለተ ወልድ ዋሕድ በኋላ ሰንበትን በዕረፍት ያሳለፉ ስለመኾኑ፤ (ሉቃስ 23/53-56)
ብዙዎች ሰዎች ቀዳሚት ሰንበት የኦሪት ናት፡ እሑድ ደግሞ የሀዲስ ኪዳን ሰንበት ሰንበተ ክርስቲያን ቆስጠንጢኖስ ያከበራት ቀን ናት ይላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ሰውን ይከተላሉ እንጂ እግዚአብሔርን አይከተሉም፡፡ ምክንያቱም፡ በሀዲስ ኪዳንም ቢኾን ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን ም/4 ላይ ሰባተኛዋን ዕለት ሰንበትን ካላከበራችሁ ባለመታዘዝ ጠንቅ ትወድቃላችሁ ብሎ ይናገራል፡፡ በመቀጠልም፡ በሉቃስ ወንጌል ም/27/53-56 ባለው እነ-መግደላዊት ማርያም እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድን በመዘጋጀት ቀን ሲሰቅሉት እና ከመስቀል አውርደው ሲቀብሩት ስፍራውን ልብ ብለው ሲያዩ መቆየታቸውን፤ ሰንበትን እንደ-ትእዛዘ-መድኃኔዓለም ማረፋቸውን፤ ሰንበት ካለፈ በኋላ ሽቱ እና ቅባት ገዝተው እሑድ ማለዳ ወደ-መቃብር ስፍራ መሄዳቸውን፤ ይናገራል፡፡ በተጨማሪም በማቴዎስ ም/28/1-2፣ በማርቆስ ወንጌል ም16 እና ዮሐንስ ወንጌል ላይ እነ-መግደላዊት ማርያም ሰንበት ሲያልፍ ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን እሑድ ወደ-መቃብር ስፍራ መሄዳቸውን ፍንትው አድርገው ጽፈዋል፡፡ ጠማሞች አጣምመው የጻፉት የበረዙት መጽሐፍ ካልኾነ በቀር በቅዱስ መጽሐፍ ላይ በአንድም ስፍራ እሑድ ሰንበት ናት የሚል የለም፡፡ ነገር ግን በአብያተ መቅደሳቶቻችን ሲያዝዙ የነበሩት ግብጻውያን ጳጳሳት መጻሕፍቶቻችንን ኹሉ በርዘው ሱባኤያችንን አፋልሰው በጽሑፍ ቀርጸውብን በመሄዳቸው ብዙዎች በውዳሴ ማርያምና በሌሎች ቅዱሳት መጽሐፍት ላይ እሑድን “ውዳሴሃ ለእግዝእትነ ማርያም ዘይትነበብ በዕለተ እሑድ ሰንበት” ተብሎ የተጻፈውን እያነበቡ ማስተዋላቸው ተወስዶባቸው እናያለን፡፡
ስለዚህ ይህች ስዑር ናት ወይም ቅዳሜ ሹር እያላችሁ እንሻራት ሥራ እንሥራባት እንጹምባትም የምትሏት ሰንበት ማለት እነ-መግደላዊት ማርያምና ደቀ-መዛሙርቱ ያረፉባት እንጂ የሻሯት ዕለት አይደለችም፡፡ ማንን መከተል እንደሚገባችሁ እናንተው ምረጡ፡፡

✡ 10ኛ. ሰንበትን የሻሩት ሰቃሊያነ ወልድ ዋሕድ የካሕናት አለቆችና ፈሪሳውያን ስለመኾናቸው፤ (ማቴዎስ 27/62-66)
ቅዱስ ማቴዎስ ቅድመ ስቅለተ ወልድ የተከናወኑትን የተንኮል ቅድመ ዝግጅቶች፣ ሥርዓተ ስቅለተ ወልድ ዋሕድን እና ከስቅለቱ በኋላ የኾነውን ነገር ተንትኖ ጽፏል፡፡ በዚህ ወንጌል ላይ ጲላጦስ እንኳን “ይህ ሰው ጻድቅ ነው ምንም ጥፋት አላገኘሁበትምና ከደሙ ንጹህ ነኝ” ሲላቸው የካሕናት አለቆችና ፈሪሳውያን ግን “ግዴለም ደሙ በእኛና በልጆቻችን ይኹን” ብለው የሰማይንና የምድርን በውስጣቸውም ያሉትን ፍጥረታት ፈጣሪ በመስቀል ላይ ሰቀሉት፡፡ ይህም አልበቃቸውም፤ እነርሱ ወልድ ዋሕድን ሲከሱት የነበረው በምኩራብ መልካም ነገር እያደረገ ቅዳሜን/ሰንበትን ይሽራል በማለት ሲኾን፤ የካሕናት አለቆችና ፈሪሳውያን ግን አክብረን እናስከብራታለን የሚሏትን ሰንበት ሽረው ከቤታቸው ወጥተው ተሰባስበው እናንተ ቅዳሜ ስዑር በምትሏት ቀን ወደ-ጲላጦስ ሄደዋል፡፡ ሄደውም ጲላጦስን እንዲህ አሉት፡- “ያ አሳች በሕይወት ሳለ፡ በሶስተኛው ቀን እነሳለሁ ብሏልና ደቀ መዛሙርቱ በሌሊት መቃብሩን ቆፍረው አውጥተው ከሙታን ተነሳ እንዳይሉ መቃብሩን የሚጠብቁ ወታደሮች ስጠን” አሉት፡፡ ጲላጦስም ወታደሮች ሰጥቷቸው ወደ-መቃብር ስፍራ ሄደው በሰንበት መቃብር ሲጠብቁና ሲያስጠብቁ መዋል ማደራቸውን ከወንጌለ ማቴዎስ እንረዳለን፡፡
ስለዚህም ቅዳሜን/ሰንበትን የሻሩት ሰቃሊያነ ወልድ ዋሕድ ፈሪሳውያን ናቸው እንጂ ሐዋርያቱ እና በጠቅላላው 120 ቤተሰብ አልነበረም፡፡ ቅዳሜ ስዑር ወይም ቅዳሜ ሹር የተባለችው ሰቃሊያኑ ሰንበትን በማይገባ ሻሩ ለማለት እንጂ እግዚአብሔርና ልጆቹ ሻሯት ለማለት አይደለም፡፡ የዛሬዎቹ የሰቃሊያነ ወልድ ዋሕድ ልጆች ግን ሰንበት በፋሲካ ጊዜ በዓመት አንድ ጊዜ የተሻረች ነች እያሉ አባቶቻቸውን ፈሪሳውያንን ማስታወሻ አድርገዋታል፡፡ ስለዚህ እናንተ ግን መቶ ሀያው ቤተሰብ በሰንበት እንዳረፈ ዕረፉ እንጂ እንደ-ሰቃሊያኑ በሰንበት አትክለፍለፉ፤ መቅሠፍትን ትቀበላላችሁና፡፡

✡ በዚህ የፍጻሜ ዘመን ደግሞ በሰባተኛው ኪዳን ጊዜ ምስጢራትን እንዲገልጽ ሥልጣን የተሰጠው ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ ለቅዱሳን አባቶች እንዲህ ብሏል፡- “የምትሻር የፋሲካ ሰንበት የለችም፤ እንዴውም በዓመት አንድ ጊዜ በፋሲካ ጊዜ የምትገኘው ሰንበት መቅደሰ ጽዮን ወእየሩሳሌም ተብላ ልዩ መለኮታዊ ሥያሜ ተሰጥቷታል እንጂ የተሻረች አይደለችም” ማለቱን ከከበሩ ልዑላን ቅዱሳን እትዮጵያውያን ተረድተናል፡፡
ስለዚህ ማናችሁም እትዮጵያውያን ሕዝበ እስራኤል የኾናችሁ በተዋሕዶ እምነት ያላችሁ፣ ሕግን እና ነቢያትን የምትጠብቁ ኹላችሁ እግዚአብሔር ለእናንተ የሰጣትን የዕረፍታችን የድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችውን ሰባተኛዋን ዕለት አክብራችሁ ክበሩ፤ አትጹሙባት ይልቁንም ዕድሜንና በረከትን የሰጣችሁን አምላክ አመስግኑባት፣ አትሥሩባት፡ ይልቁንም ከአምላካችሁ ጋር ዕረፉባት፡፡ ይህን የስሉሥ ቅዱስ ኀያል አጋዕዝት ሥላሴ ትእዛዝ ተቀብሎ የማይተገብር ልቡን አመጸኛ አድርጎ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ይልቅ በይሉኝታ የሰውን ፈቃድ የሚቀበል ከቤልሆር ጋር የተባበረ በመኾኑ የሲኦል ልጅነቱን እንደተቀበለ መረዳት ይገባል፡፡ እኛ ይህን ኹሉ አዋጅ የምናውጅላችሁ ከእናንተ እጅ መንሻ ወይም የድኅረ ገጽ ገንዘብ ለማግኘት አይደለም፤ ይልቁንም ዕረፍት ያጣች የምትቅበዘበዝ አንዲት እትዮጵያዊት ነፍስ እንኳን ብናገኝ ብለን እንጂ፡፡

✡ እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ በሰንበት ላይ እየተፈጸመ ባለው አመጻ ምክንያት ደግሞ መቅሠፍቱን በአመፀኞች ላይ እያዘነመ ይገኛል፡፡

✡ በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
Share:
Forward:
Add members
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
only every Sunday
ዘወትር እሑድ ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251927616937

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias:

Share