23/05/2026
🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡
በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አደረሳችሁ!!!
🔯 “ካህናቶችዋም ሕጌን በድለዋል ቅድሳቴንም አርክሰዋል፤ ቅዱስ በሆነና ቅዱስ ባልሆነ መካከልም አልለዩም፥ በንጹሕና በርኩስ መካከል ያለውን ልዩነት አላስታወቁም፤ ዓይናቸውንም ከሰንበታቴ ሰወሩ።” (ሕዝቅ/22/26) ተብሎ የተጻፈውን አስተውሉ! ካሕናት ማለት የሌዊ ዘር የኾኑ ሌዋውያን ናቸው፡፡ የዘወትር ተግባራቸው እግዚአብሔርን ማመስገን ሕዝብን በቅድስና መንገድ መምራት ነበር፡፡ ነገር ግን በዚህ ዘመን ያሉ ብዙዎቹ ካሕናት ነን የሚሉቱ የሥላሴን ሕግ ትተው የዓለምን ሕግ ያስከብራሉ፤ በንዋየ ቅድሳቱ ያመሰግኑ ዘንድ ሲገባቸው ንዋየ ቅድሳቱን ከመቅደሱ አውጥተው ይሸጣሉ ይለውጣሉ፤ ቅዱስ የኾነውን ቅዱስ፡ ማለት ቅዱስ ያልኾነውን ደግሞ ርኩስ ይሉ ዘንድ ልባቸው ሳይፈራ በአንድነት ያከናውኑታል፡ በቀኝ እጃቸው መስቀል በግራ እጃቸው የጋኔን መጎተቻ ይይዛሉ፤ በቅድስና መንገድ እንመራዋለን የሚሉትን ሕዝብ ንጹህ እና ርኩስ የኾነውን ለይቶ ያውቅ ዘንድ አላስታወቁትም፡ ይልቁንም ሕዝብ ንጹሁን ለይቶ ቢያውቅ ለሥጋቸው የሚመቸውን ያሳጣናል ብለው ይሠጋሉና መግለጽ የሚገባቸውን ሠውረው በአሕዛብ መንገድ ይጓዛሉ፡፡
🔯 ስለዚህ፡ እግዚአብሔር በተዋሕዶ መንገድ የመራህ የአባቶችህን ክብር የሰጠህ ሕዝበ እትዮጵያ ሆይከእነዚህ የበግ ለምድ ለባሾች ርቀህ በአባቶችህ የቅድስና መንገድ ትመላለስ ዘንድ በጭካኔ እንመክርሀለን።
🔯 ባለፈው ሳምንት ካቆምንበት እንቀጥል ዘንድ ወድደናል፦ ያለመታዘዝ ምን ትመስላለች፡ ዋጋዋስ ምንድነው!!! ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ተናገረ፡ “እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና። (ኢሳ/1/19—20)
🔯 በእውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው፡ እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ መታዘዝ ከመሥዋዕት ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።” (ሳሙኤል ቀ/15/22)
🔯 ራሳችሁን ለምታቀርቡለት ለርሱ ለምትታዘዙለት ባርያዎች እንደኾናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኀጢአት ባርያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባርያዎች ናችሁ። (ሮሜ 6/16)
🔯 መታዘዛችሁ በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ኹሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል። (2/ቆር/10/6)
🔯 “ከትእዛዛትህ የሳቱትን ትዕቢተኞችንና ርጉማንን ዘለፍህ።” በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም፤ እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል። እጆቼንም ወደ-ወደድኋቸው ወደ-ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላለሁ።” (መዝ/119/21፣ 45-48)
ኃጢአተኞች ጨዋታን ነገሩኝ፥ አቤቱ፥ እንደ-ሕግህ ግን አይደለም። ትእዛዛትህ ሁሉ እውነት ናቸው፤ በዓመፅ አሳድደውኛል፤ እርዳኝ። ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም። እንደ-ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፤ የአፍህንም ምስክር እጠብቃለሁ። አቤቱ፥ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል። እውነትህ ለልጅ ልጅ ናት፤ ምድርን መሠረትሃት እርስዋም ትኖራለች። ሁሉም ባሪያዎችህ ናቸውና ቀኑ በትእዛዝህ ይኖራል።” (መዝ/119/85-91)
🔯 “አቤቱ፥ ሕግህን እንደ-ምን እጅግ ወደድሁ ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው። ለዘላለም ለእኔ ነውና ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ። ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ። ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ። ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ። አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም። ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ። ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው። የጽድቅህን ፍርድ እጠብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸናሁም።” (መዝ/119/97-105)
🔯 እንግዲህ ለሚያስተውል መታዘዝ ማለት እንደ-አብርሃም ያለች መታዘዝ ጸጋም በረከትም ማስተዋልንም ሰጥታ እድሜንም እንደ-እርሱ እንደ-አባታችን አብርሀም እስከ 962 ዓመት የምትሰጥ ወይም እንደ-ኤልያስ እንደ-መልከጼዴቅ፡ እንደ-ሔኖክ ወይም እንደ-ብዙኃን እትዮጵያውያን ቅዱሳን ዘለዓለማዊነትን የምታጎናጽፍ ናት፡፡
🔯 በሌላ አንጻር ያለመታዘዝ ማለት ግን አመጻ ማለት ነው፤ መታዘዝ እሺ ማለት ሲኾን፡ አለመታዘዝ ደግሞ እምቢ፡ ማለት ነው፡፡
🔯 ነቢዩ ሳሙኤል፡ ንጉሡን ሳኦልን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቀብቶ አነገሠው ነገር ግን ሕዝበ እስራኤልን ይዞ ከፍልስጤማውያን ጋር ለመዋጋት በወጣ ጊዜ ያገኘኸውን ሰውንም ከብትንም ኹሉ ግደል የሚል የእግዚአብሔር ትእዛዝ ደርሶት ሳለ፡ እንደ-ትእዛዙ ሰዎቹን ኹሉ በሰይፉ ካጠፋ በኋላ የሚያማምሩትን የፍልስጤማውያንን ከብቶችና አውራ በጎች ባየ ጊዜ ጎምዥቶ ሳይገድል ለመሥዋዕት አቀረባቸው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ከአውራ በግ ይልቅ በእግዚአብሔር የተወደደው መታዘዝ ነው፤ ከእንግዲህ ወዲህ ባለመታዘዝህ ጠንቅ እግዚአብሔር መንግሥትህን ከአንተ ወሰደው ለጎረቤትህም ሰጠው ተብሎ ተነገረበት፤ በዚያም ዘመን ከፍልስጤማውያን ጋር ሲዋጋ በጦር ተገድሎ ሲሞት በቤቱ ያደገው ቅዱስ ዳዊት ንግሥናውን ወሰደ፡፡
🔯 አለመታዘዝ ቃየንን ትመስላለች፤ አቤል ለእግዚአብሔር ንጹህ መሥዋዕትን ሲያቀርብ ቃየን ግን ግብስብስ መሥዋዕት በማቅረቡ ተቅበዝባዥ ደስታ የሌለው ኾነ፡ ዘሩም በአጋንንት እጅ ወድቀው ከአጋንንት ጋር እየተዳቀሉ እስከ-ዛሬ ከርኩሰት ጋር አሉ፡ ፍጻሜአቸውም በገሀነም ይኾናል፡፡
🔯 አለመታዘዝ የአስቆሮቱን ይሁዳን ትመስላለች፡ ይሁዳ ኀዋርያው አድርጎ የሾመውን አምላኩን መታዘዝ ትቶ ሥጋ ለባሾችን ተከትሎ ለሮማውያንና ለፈሪሳውያን ትእዛዝ ባርያ ኾኖ አምላኩን ለገዳዮቹ አሳልፎ ሰጥቶ ባደረገው ክፋት ጸጸት በዛፍ ላይ አንጠልጥላ ገደለችው፡ ብልጠቱም ከሲኦል መግባት አላስጣለችውም፡፡
🔯 አለመታዘዝ የናቡ ከደነጾርን ባለሟሎች ትመስላለች፤ ሚሳቅ፡ ሲድራቅና አብደናጎ የተባሉ አይሁዳውያን የንጉሥ ናቡ ከደነጾርን ጣኦት መታዘዝ ትተው የአይሁድን አምላክ እግዚአብሔርን ይታዘዛሉ ብለው ከሰዋቸው ንጉሡ በታላቅ እቶን እሳት ውስጥ ይጣሉ ዘንድ ትእዛዝ ሰጥቶ ከእነ-ሰናፌላቸው ወደ-ነበልባሉ በተጣሉበት ጊዜ፡ ሰለስቱ ደቂቅን በእሳት ለመጨመር ሲሉ ወደ-እሳቱ የተጠጉት ከሳሾቻቸው በእሳቱ ወላፈን ተቃጥለው ሲሞቱ የሥላሴን ሕግና ትእዛዝ አምልኮም አንተውም ያሉት ሲድራቅ፡ ሚሳቅና አብደናጎ በእሳቱ መሀል ከመላእክት ጋር ሲዘምሩ ያየው ንጉሥ ከሳሾቻቸውን በሰይፍ ገድሎ ራሱ ንጉሡ ከአመጻ ተለይቶ የእነ-ዳንኤልን አምላክ አመለከ፡፡
🔯 አለመታዘዝ ዲያብሎስን ትመስላለች፤ እግዚአብሔር አምላክ ዲያብሎስን የነገደ መላእክት አለቃ አድርጎ ሾሞት ከፍ ከፍ አድርጎት ሳለ፡ እርሱ ግን ለእግዚአብሔር አልታዘዝም ብሎ ከእነ ነገዱ ከሰማይ ወደ-ጥልቁ የሥቃይ ስፍራ ተጣለ፤ እነሆ ዝርያውም እስከ-ዛሬ ድረስ ሰዎችን እያሳተ ልባቸውንም ባለመታዘዝ በአመጻ እየሞላ የዘለዓለም ሞትን ሞቶ እናየዋለን፡፡
🔯 ስለዚህም፡ መታዘዝ መጨከንን ትፈልጋለች፡ መንገዷ ቅን ኾና የሚቃወሟት ብዙዎች ናቸውና፤ አመጻ ግን መንገዷ ሰፊ ነው ዓለማውያን በሥጋ ነጻ ፈቃድ በሥጋዊነት ሲኖሩ በአጭር እድሜ ውስጥ ብዙ የሚያጠፉባት ናትና፡፡
🔯 ስለዚህም እኛ የልብን ጭካኔ የምትሻ ፍጻሜዋ ዘለዓለማዊነት ሕያውነት የኾነችውን አዋጅ እንገልጽላችኋለን፡፡ እውነተኛ እምነት አንዲት ብቻ ናት፤ እርሷም ርትዕት ዘለዓለማዊት ተዋሕዶ ናት፡፡ ሰንበት አንዲት ናት፤ እርሷም አምላክ ሥራውን በ6 ቀናት ፈጽሞ ያረፈባት ቅዳሜ ሰንበት ብቻ ናት፡፡ ሕይወት እና የሕያዋን ዕረፍት አንዲት ናት፤ እርሷም ዘለዓለማዊነት የሚሰጠንን ሥጋዋን እና ደሟን ከልጇ ከእግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ የምትመግበን ቤዛዊተ ዓለም ድንግል ማርያም ናት፡፡ አምላክ አንድ ነው፤ እርሱም አንድ ሲኾን፡ ሶስት፡ ሶስትም ሲኾን አንድ የኾነ ስሉሥ ቅዱስ ኀያል አጋዕዝት ሥላሴ መለኮት አሐዱ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ይህ አዋጅ የቅዱሳን እትዮጵያውያን አዋጅ የፍጻሜው ምስጢር እና የፍጻሜው ቁርጥ ፍርድ ነው፡፡ የሚታዘዝ የሚተገብረው ይድንበታል፡ አመጸኛው የሚቧልት ግን የፍጻሜውን የአመጻውን ፍሬ ይበላል፡፡
🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡
🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!
🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡
ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ
አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።
መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።
#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ
በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie
በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/
በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/
የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ