መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አ...
22/08/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

✡ “ሰንበትን የሚጠብቃት፡ ሰው ኹሉ ከሥራም ኹሉ የሚያርፍባት በዘመኑ ኹሉ እንደ-ዕኛ የተቀደሰና የተባረከ ይኾናል፡፡” (ኩፋሌ 3/14) ከዚህ ሕያው ቃል የምናስተውለው አንዲቷን ሰባተኛዋን ዕለት ቀዳሚትና ደኀራዊት ሰንበትን ከሥራ ኹሉ ተከልክሎ በምስጋና እና በዕረፍት የሚያሳልፍ ከአምላኩ ጋር አብሮ እንደሚያርፍ ነው፡፡ ነገር ግን በሰንበት የማያርፍ የእግዚአብሔርንም ቃል የማይጠብቅ እርሱ ከእግዚአብሔር ጠላቶች ጋር አብሮ ይቅበዘበዛል፡፡

✡ ቅድስት ሀገር እትዮጵያ ሀገረ ሰንበት! ሀገረ እግዚአብሔር ሀገረ ማርያም ናት ስንላችሁ እንደ-ቀልድ በዋዛና በፈዛዛ ያያችሁት እንዴት ጊዜው እንዳለፈባችሁ አስተውሉ!!! እኛ የሚገርመን እትዮጵያ አምላኳ እግዚአብሔር፤ ባለቤቷ እግዚአብሔር፤ ቀኗንም ሌሊቷንም የሚያስተዳድረው እግዚአብሔር፤ ኾኖ እያለ ልክ ዘለዓለም ነዋሪዎች የሚመስሉ በማይመለከታቸው ገብተው እርስ በእርስ ሲፋጁ ሲጣሉ ከበረከት ሲርቁ ስናይ በእግዚአብሔር አደራረግ እንደነቃለን፡፡

✡ ነቢዩ ኢሳይያስ በቅድስት ምድር እትዮጵያ ስለሚመከር ክፉ ነገር እንዲህ ተናገረ፡- “ለዓመፀኞች ልጆች ወዮላቸው… ከእኔ ዘንድ ያልሆነን ምክር ይመክራሉ፥ ኃጢአትንም በኃጢአት ላይ ይጨምሩ ዘንድ ከመንፈሴ ዘንድ ያልሆነውን ቃል ኪዳን ያደርጋሉ። ከአፌም ነገርን ሳይጠይቁ በፈርዖን ኃይል ይጸኑ ዘንድ በግብጽም ጥላ ይታመኑ ዘንድ ወደ ግብጽ እንዲወርዱ ይሄዳሉ። (ኢሳይ/30/1-2)

✡ ነቢዩ ሕዝቅኤልም እንዲህ አለ፡- “ዋይ በሉ፥ ለቀኑ ወዮ ቀኑ ቅርብ ነው፥ የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፥ የደመና ቀን፥ የአሕዛብ ጊዜ ይሆናል። ሰይፍ በግብጽ ላይ ይመጣል፥ ሁከትም በኢትዮጵያ ይሆናል፤ የተገደሉትም በግብጽ ውስጥ ይወድቃሉ፥ ብዛትዋንም ይወስዳሉ፥ መሠረትዋም ይፈርሳል። ኢትዮጵያና ፉጥ ሉድም የተደባለቀም ሕዝብ ሁሉ ኩብም ቃል ኪዳንም የገባችው ምድር ልጆች ከእነርሱ ጋር በሰይፍ ይወድቃሉ። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ግብጽን የሚደግፉ ይወድቃሉ፥ የኃይልዋም ትዕቢት ይወርዳል፤ ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔ ድረስ በእርስዋ ውስጥ በሰይፍ ይወድቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። ባድማም በሆኑ አገሮች መካከል ባድማ ይሆናሉ፥ ከተሞችዋም በፈረሱ ከተሞች መካከል ይሆናሉ። እሳትንም በግብጽ ባነደድሁ ጊዜ ረዳቶችዋም ሁሉ በተሰበሩ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። በዚያ ቀን መልእክተኞች ተዘልለው የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንን ለማስፈራት ከፊቴ በመርከብ ይወጣሉ፤ እንደ ግብጽም ቀን ሁከት ይሆንባቸዋል፤ እነሆ፥ ይመጣልና።”
(ሕዝቅ/30/2-9)

✡ እነዚህ የነቢያት ትንቢቶች በዚህ ዘመን ስላሉ አመጸኞች የተነገሩ ናቸው፡፡ ቅድስት ሀገር እትዮጵያ የእግዚአብሔር ምድር የዐዳምና የሔዋን መፈጠሪያና መናገሻ የመለኮት መቅደስ የድንግል ማርያም የትውልድ ሀገር ናትና ባለቤት እንደሌላት መቀራመት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ስለዚህም እግዚአብሔር ሀገር ትመሩ ዘንድ የፈቀደላችሁ በቤተ ክህነትና በቤተ መንግሥት ያላችሁ እንዲሁም በቅድስት ሀገር በአራት ማእዘናት ያላችሁ ከእናንተም መካከል በትእቢትና በአመጽ ያላችሁ የእግዚአብሔር ቁጣ በእናንተ ላይ እንደ-ዝናብ ከመውረዱ አስቀድሞ በእጅጉ ወደ-ልቦናችሁ ተመለሱ፡፡ እኛ በቅድስት ምድር እትዮጵያ ላይ የሚመከር ክፉ ነገር ኹሉ እንዳይፈጸም ፈጽሞ እናምናለን፤ እናውቃለን። ነገር ግን ክፉ መካሪዎች ከክፋታቸው ተመልሰው በጽድቅ መንገድ ይሄዱ ዘንድ ዘርአ ዐዳም ወሔዋን ኹሉ በተዋሕዶ ከጥፋት ይድን ዘንድ የዘወትር ልመናችን ነውና ኹልጊዜ እናስጠነቅቃለን፡፡

✡ 7 ሰዎች በአንዲት ከተማ ውስጥ ሲኖሩ በፀሓይ ተጣሉ ይባላል፡፡ ሶስቱ ፀሓይ የኹላችንም ብርሃን ናትና አንዱ ሌላውን ይከለክለው ዘንድ አይቻልም ሲሉ፤ አራቱ ደግሞ ፀሓይ የእኛ ብቻ ናት፤ ከእናንተ ከሶስታችሁ ቀድመን የተወለድነው እኛ ነን፤ ስለዚህ በቀን ፀሓይ ልትሞቁ፣ እህል ልታሰጡ፣ ከብቶቻችሁን በብርሃን ልታሰማሩ አይገባም፤ እናንተ ሌሊት ሌሊት የወደዳችሁትን ከማድረግ በቀር በፀሓይ ጊዜ በቤታችሁ ተቀመጡ፤ በፀሓይ ጊዜ የወደድነውን እናደርጋለን ካላችሁ ስለ-ፀሓያችን ዋጋ ክፈሉን፤ ሳትከፍሉ የእኛን ፀሓይ ከሞቃችሁና ከተገለገላችሁባት እናጠፋችኋለን፤ አሏቸው፡፡ በዚህም የተነሳ ሰባቱ ሰዎች ጦር እና ቀስት መዘው ውጊያ ጀመሩ፡፡ ውጊያቸው በቀን ነበረና በውጊያቸው መካከል ፀሓይ በድንገት ብርሃኗን ከለከለች፤ ለሰባት ቀናትም ከተሠወረችበት አልወጣችም፡፡ ታድያ ከሚዋጉት መካከል ከኹለቱም ወገን አምስቱ ሞተው ከየወገኑ የተረፉት ኹለት ሰዎች ለካስ የምንጣላው የእኛ ባልኾነች ለጋራ በተሰጠችን ስንወድ ልናወጣት ሳንወድ ልናጠልቃት በማንችል በእግዚአብሔር ስጦታ ነው ብለው ተነጋግረው በይቅርታ ሲላቀሱ ፀሓይ እንደ-ገና ብርሃኗን ሰጠች።

✡ በእኛም ሀገር ቅድስት ምድር እትዮጵያ ሀገረ ማርያም፣ ሀገረ እግዚአብሔር ኾና ሳለ፡ ይህ ከተማ የእኛ ነው፤ ያኛው ክፍለ ሀገር የእነ-እገሌ ነው፤ የግእዝ ፊደል ይጥፋ የእትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ይወገድ፤ እኛ በዚህ እንበልጣለን እነገሌ በዚህ ያንሳሉ፤ በሚል በቅድስት እትዮጵያ የሚጣሉ ኹሉ እንዲሁ በፀሓይ እንደተጣሉት ሰዎች ናቸው፡፡እነርሱ በሰፊ አዳራሽ መከሩ፤ ነገር ግን የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ምክር አላወቁም፤ እነርሱ ፍቅርን እግዚአብሔርን ትተው በጸብ ተሞሉ፤ ነገር ግን የቅዱሳንን ሐሴትና ፍርድ አልተረዱም፤ እነርሱ ለነገ መከሩ፤ ነገር ግን ነገን አላወቁትም፡፡

✡ ስለዚህ ነቢዩ ሕዝቅኤል ቅድስት እትዮጵያን ለማስፈራራት የሚመጡ የግብጽ ደጋፊዎች ቅድስት እትዮጵያ ትጥፋ የሚሉ የስም አጠራሯንም አንስማ ያሉ እንደ-ግብጽ ቀን ሑከት እንደሚኾንባቸው የተነገረው ሕያው ቃል ይወድቅባቸው ዘንድ አለና ከክፉ ምክራቸውና ምግባራቸው ተጠብቀው በጽድቅ መንገድ እንዲመላለሱ እናሳስባለን፡፡

✡ እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” የምትለው ናት፤ መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

✡ በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላዳመጥኩም የሚል ያድምጥ፡

For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደረ...
15/08/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

✡ “ብዙ ሰዎች በመከራ ተይዘው ይጠፋሉ፡ በጠላቶቻቸውም እጅ ይወድቃሉ፤ ሥርዓቴን የመሐላዬንም በዓላት ሰንበታትንም በመካከላቸውም የለየሁትን ንዋየ ቅድሳቴን ስሜ በእርሱ ይጠራ ዘንድ ያድርበትም ዘንድ በምድር መካከል ያከበርኩትን ቤተ መቅደሴንና ድንኳኔን ትተዋልና ይጠፋሉ። (ኩፋሌ 1/9)

✡ ከዚህ ኀያል መለኮታዊ የቁጣ ቃል፡-
1. የእግዚአብሔርን እትዮጵያዊ የተዋሕዶ ሥርዓት፤
2. የእግዚአብሔርን የመሐላ በዓላት ሰንበታትን፤
3. ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ማቅረቢያነት የተለዩትን ንዋየ ቅድሳቱን፤
4. በምድር እግዚአብሔር መካከል ያከበራትን የእግዚአብሔርን የስሙን መጠሪያ እና ማደሪያውን ዘለዓለማዊት ቤተ መቅደሱን ቅድስት ሀገር እትዮጵያን፤ የተዉ ሰዎች፣ ቅድስት እትዮጵያን ያፈረሱና ሊያፈርሱ የተነሱ አሕዛብ፣ ቅድስት እትዮጵያን ያንጓጠጡ፣ ቅድስት እትዮጵያን የጠሉና የሚጠሉ፣ በቅድስት እትዮጵያ ላይ አንደበታቸውን የሚያላቅቁ ኹሉ፤ እውነት፡ እውነት፡ እውነት፡ ሳይዘገይ ለዘለዓለም ይጠፋሉ፡፡ ይህ ቃል በሰው ፍላጎት የተነገረ ወይም ከፍጡር አንደበት የወጣ ተግሳጽ ሳይኾን ይልቁንም መለኮታዊ ፍርድ ነውና ከመፈጸም የሚቀር አይደለም፡፡

✡ “ተዐውቀ ፡ እግዚአብሔር ፡ በይሁዳ ፤ ወዐቢይ፡ ስሙ፡ በእስራኤል። ወነበረ፡ በሳሌም፡ ብሔሩ፤ ወማኅደሩሂ፡ ውስተ፡ ጽዮን። ወበህየ፡ ሰበረ፡ ኀይለ፡ ቀስት፤ ወልታ፡ ወኲናተ፡ ወፀባኢተ። ወበህየ፡ ሰበረ፡ አቅርንተ።”
(እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ፥ ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው። ስፍራው በሳሌም፥ ማደሪያውም በጽዮን ነው። በዚያም የቀስትን ኃይል፥ ጋሻን ሰይፍን ሰልፍንም ሰበረ፤ በዚያም ቀንዶችን ሰበረ።) (መዝ/76/1-3)
ተብሎ የተጻፈውን አስተውሉ! ቅድስት ምድር እትዮጵያ የልዑል እግዚአብሔር ማደሪያ መኾኗን ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ፍንትው አድርጎ የተናገረላት ናት፡፡

✡ ታድያ ዘወትር የማድርባትን መቅደሴን ትታችኋልና ትጠፋላችሁ የተባሉት መቅደሰ መለኮትን ቅድስት እትዮጵያን ሲኆን፤ ጠላት ኾነውባት የሚገኙትንማ እንዴት እንደሚቀጣቸው ማሰብ ይዘገንናል፡፡

✡ “ሕጌን ኹሉ ትእዛዜንም ኹሉ ፍርዴንም ኹሉ ሥርዓቴንም ኹሉ ይዘነጋሉ፤ የወሩን መባቻና ሰንበትን በዓሉንና እዮቤልዩ ሥርዓቱንም ይዘነጋሉ።” (ኩፋሌ 1/13) ተብሎ እንደተጻፈ፡ በዚህ ዘመን ያሉ ካሕናት ነን የሚሉ ትክክለኛዋን እግዚአብሔር ከሥራ ኹሉ ያረፈባትን ሰንበትን ቅዳሜን ትተው ሰበብ አስባብ እየደረደሩ እሑድን ሰንበት አድርገው፡ ጭራሽ በዚህ ጊዜማ ቅዳሜ ሥራ ተሠርቶ እሑድ ሰንበት ይኹንልን እያሉ የእግዚአብሔርን ሰንበት በሰው ሰንበት ለመተካት እየጮሁ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ስለሕጉና ሥርዓቱ ስለመንግሥቱም ዕለት ስለሰንበት ቀንቷልና እሑድን እንደ-ሰንበት እንተክላታለን የሚሉትን በአናታቸው እየተከላቸው ይገኛል፡፡ በአናቱ የተተተከለ አይበቅልምና እነርሱም ለዘለዓለም አይጸድቁም።

✡ እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” የምትለው ናት፤ መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

✡ በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ቀስተ ደመና ብርሂት አደረሰን ...
08/08/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ቀስተ ደመና ብርሂት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “በሰንበት ቀን… ሸክም ባታገቡ፥ የሰንበትንም ቀን ብትቀድሱ ሥራንም ሁሉ ባትሠሩበት በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታትና መሳፍንት በሰረገሎችና በፈረሶች ላይ እየተቀመጡ በዚህች ከተማ በሮች ይገባሉ፤ እነርሱና መሳፍንቶቻቸው የይሁዳም ሰዎች በኢየሩሳሌምም የሚቀመጡ ይገባሉ፥ ይህችም ከተማ ለዘላለም የ”ሕዝብ” መኖሪያ ትሆናለች። የሚቃጠለው መሥዋዕትና ሌላ መሥዋዕትን የእህሉንም ቍርባን ዕጣኑንም የምስጋናውንም መሥዋዕት ይዘው ከይሁዳ ከተሞች ከእየሩሳሌምም ዙሪያ ከብንያምም አገር ከቈላውም ከደጋውም ከደቡብም ወደ እግዚአብሔር ቤት ይመጣሉ።” (ኤር/17/25-26)

🔯 ይህ የሰንበት የበረከት ትእዛዝ ነቢዩ ኤርምያስ ለሕዝቡ የገለጸው ሕይወት ነው፡፡ ይህ ሕይወት ደግሞ የኦሪት ወይም ያለፈበት ወይም ድኅረ ልደተ ወልድ የማይተገበር አይደለም፤ ዘለዓለማዊ እንጂ።

🔯 በዚሁ የኤርምያስ መጽሐፍ ክፍልና ምዕራፍ ላይ “ነገር ግን የሰንበትን ቀን እንድትቀድሱ፥ በሰንበት ቀን ሸክምን ተሸክማችሁ በእየሩሳሌም በሮች እንዳትገቡ የነገርኋችሁን ባትሰሙኝ፥ በበሮችዋ ላይ እሳትን አነድዳለሁ፥ የእየሩሳሌምንም አዳራሾች ትበላለች፥ አትጠፋም።” (ኤር/17/27) በማለት ሰንበትን ያለማክበር የሚያስከትለውን መዘዝ ይናገራል፡፡

🔯 በዚህም ዘመን የሰው ልጅ በጥንቱ አመጻው በመቀጠሉ የእግዚአብሔር ቁጣ በእያንዳንዱ ላይ ነደደ፤ እነሆ የእግዚአብሔር እሳት በምስራቅና በምዕራብ፣ በሰሜንና በደቡብ፣ በመሀልና በዳር እየተንበለበለ የአሕዛብ ዋይታ በየስፍራው ኾነኖ እናያለን፡፡ እዚህ ቦታ ይህን ያህል ሰው ታገተ፤ በዚያ ከተማ እንዲህ ተዘረፈ፤ በዚህ መንደር ሰዎች እንዲህ ተነወሩ፤ በእነ-እገሌ ክፍለ ሀገር ይህን ያህል ሰው አለቀ፤ በባቢሎን አውሎ ነፋስ በምዕራብ ሐገራትም ሰደድ እሳት ሰዎችን ገደለ አፈናቀለም፤ ርዕደ መሬት በጃፓንና ኢንዶኔዢያ እሳተ ገሞራም በጣሊያን ተራሮችን አቀለጠ፤ በዩክሬን የሚሳኤል እሳትና ዲን ዘነመ በፋርስ ሀገር በኢራንም ሕዝብ በአቶሚክ ቦምብ አለቀ፤ የሁርሙዝ ሰርጽ ተዘግቶ ነዳጅ ጠፍቶ በዐረብ ሀገራት ረኀብ ጸና፤ ከሞሮኮ የተሻገሩ ሺዎች ስደተኞች ስፔንን አጥለቀለቁ፤ በሱዳን ጦርነት ሰው ከዝንብ ያነሰ የረከሰ ሞትን ሞተ፤ ደቡብ አፍሪቃ ነጮች ባርያዎች አድርገው ይግዙን የሚሉ ጥቁሮችን መግደል ቀጠሉ፤ ሳውዲ ዐረቢያ 25 እትዮጵያውያንን በሞት ቀጣች፤ ወዘተ… የምንሰማቸው የመርገም ድምጾች ኹሉ የሰላም ባለቤት የእትዮጵያ አምላክ አጋዕዝት ሥላሴ ሰላሙን ከአሕዛብ ላይ ነጥቆ በመውሰዱ እና የፍጻሜ ፍርዱ በመገለጡ መታወክና ሞት ሰቆቃና ለቅሶ ታይቶም የማይታወቅ እንግዲህም የማይታይ መከራ ኾነ (ማቴ/24)፡፡

🔯 እኛ የቅዱሳን ዘሮች፡ የድንግል ማርያም ልጆች፡ የእግዚአብሔር ሀገር ተወላጆች እትዮጵያውያን በምድሪቱ ላይ ላሉት የአሕዛብ ነገሥታትና የሃይማኖት ድርጅት መሪዎች ኹሉ አስቀድመን የሚመጣውን አሁንም የመጣውን በገሃድ አወጅንላቸው እነርሱ ግን ገሚሶቹ አውቀናል ግን እንዋጋችኋለን አሉን፤ ሌሎቹ ሐሰት ነው ሲሉ ቀሪዎቹ ችላ ብለው አለፉት፡፡ በዚህ ጊዜ ግን እንደ-ደመራ እንጨት እሳት ሲነድባቸው እኒያ ኤልያሳውያን ትክክል ነበሩ ይላሉ፡፡

🔯 አሁንም ቢኾን ፈገግ እያልን የምናስገነዝባችሁ ጥቂት ቁም ነገሮች አሉን፡-

🟢 1. ቅድስት ምድር እትዮጵያ የቅዱሳን ሀገር እንጂ የርኩሳን ምድር አይደለችም፤ ለምን ቢሉ ቅዱስ እግዚአብሔር መቅደሱ ያደረጋት፣ ድንግል ማርያም የተወለደችባት የሀና እና የእያቄም ሀገር፣ ወልድ ዋሕድ የተወለደባት የቤተልሔም ምድር፣ ዐዳምና ሔዋን የተፈጠሩባትና በርሷ ውስጥ ነግሠው ምድሪቱን ያስተዳደሩባት፣ ኖሕ ከጥፋት ውሀ የዳነባትና ምድሪቱን በእጣ ለሶስቱ ልጆቹ ያከፋፈለባት፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ፡ የአባ ሕርያቆስ፣ የአቡነ ተክለ-ሃይማኖት፡ የጸጋ ዘአብና እግዚእ-ሀረያ፡ የመልከ-ጼዴቅ ንጉሠ ሳሌም፡ የዳግማዊ መልከ-ጼዴቅ የመምህር ያሬክ፣ የአእጋረ ፀሓይ፣ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ የላልይበላ፣ የነአኩቶ ለአብ፣ የራስ መኮንን፣ የኀይለ-ሥላሴ፣ የሚኒሊክ፣ የአብርሀ እና የአጽብሀ፡ የንግሥት አዜብ ወይም ማክዳ፡ የ12ቱ ሐዋርያትና የ72ቱ አርድዕት፡ የ36ቱ ቅዱሳት አንስት፡ የነቢዩ ኤርምያስና ሚኪያስ፡ የርእሰ ነቢያት ወነገሥት ቅዱስ ኤልያስ፡ የነቢያት፣ የመላእክትና የአማልክት ሀገር መኾኗን በሰማይና በምድር ባሉ መላእክት እና አማልክት ፊት እናረጋግጥላችኋለን፡፡ ይህን ስንል ባለ-ሐገሮቹ ቅዱሳን ሳሉ፡ አሕዛብ ባቢሎናውያን በቅድስት ምድር ባለ-ሀገር ሊኾኑ አይችሉም፤ እግዚአብሔር ተዋግቶ ድል ይነሳቸዋልና፡፡

🟠 2. በአሕዛብ ላይ የምትነደው እሳት እንደማትጠፋ ኹሉ ተዋሕዶን ለማጥፋት በተነሱና በሚነሱ ሞኞች ላይ የእግዚአብሔር እሳት በላያቸው ላይ ኾና አትጠፋም፡ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ከድንግል ማርያም በተዋሕዶ ተወለደ የምትለዋን እውነት ጠልቶ የሚያምኑትን እትዮጵያውያንን ለማጥፋት የተነሳና የሚነሳ ኹሉ በእርግጥ ከድንግል ማርያምና ከእግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ጋር በአካል ውጊያ ገጥሟል፡፡ለዚህም ነው ነቢዩ ኢሳይያስ “በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ለአሕዛብ ምልክት ሊሆን የቆመውን የእሴይን ሥር አሕዛብ ይፈልጉታል፤ ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።… የቀረውን የሕዝቡን ቅሬታ ከአሦርና ከግብጽ፥ ከጳትሮስና ከእትዮጵያ፥ ከኤላምና ከሰናዖር ከሐማትም፥ ከባሕርም ደሴቶች ይመልስ ዘንድ ጌታ እንደ ገና እጁን ይገልጣል። ለአሕዛብም ምልክትን ያቆማል፥ ከእስራኤልም የተጣሉትን ይሰበስባል፥ ከይሁዳም የተበተኑትን ከአራቱ የምድር ማዕዘኖች ያከማቻል። የኤፍሬምም ምቀኝነት ይርቃል፥ ይሁዳንም የሚያስጨንቁ ይጠፋሉ፤ ኤፍሬምም በይሁዳ አይቀናም፥ ይሁዳም ኤፍሬምን አያስጨንቅም።” (ኢሳ/11/10-13) ቀድሞ እንደተነገረ፡ እትዮጵያውያንን የይሁዳን ምድር የሚያስጨንቁትን ያጠፋቸዋል እንዳለ፡ እግዚአብሔር ተዋሕዶን የሚዋጉትን ይዋጋቸዋል፡ ያሸንፋቸዋልም፡፡

🔴 3. ሰንበትን የሚዋጉ ለዘለዓለም ይጠፋሉ፡፡

🔯 በሚቀጥለው ሰንበት ከሰነበታችሁ ቅዱስ መጽሐፋዊ ማስረጃዎችን እንገልጥላችኋለን፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” የምትለው ናት፤ መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ርትዕት ተዋሕዶ አደረሰን አደ...
01/08/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ርትዕት ተዋሕዶ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “እግዚአብሔር ለእስራኤል የሰጣት ታላቅ ክብር ናትና /ሰንበትን/ አክብሯት።” (ኩፋሌ 34/16)

🔯 ሶስት ሰዎች ዘወትር ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል ወደ-ቤተ መቅደስ እየተመላለሱ እባክህ አምላኬ ሀብት ስጠኝ እያሉ በእንባ ይማጸኑ ነበር፡፡ ከሶስቱ አንደኛው አምላኬ ሆይ ሀብት ስትሰጠኝ የምክድህ ከኾነ ግን ተወው የምትል ቅድስናን የተመላች ትሕትና ይጨምር ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የሶስቱንም ልመና ሰምቶ ሀብት እንዲሰጣችሁ ወዳዘዝኩት ልጄ ወደ-መርስኤ ሐዘን ሄዳችሁ በረከታችሁን ተቀበሉ አላቸው፡፡ እነርሱም ተጠራርተው በደስታ ተሞልተው ተያይዘው በስም ተጠቅሶ ወደተነገራቸው አባት ሄዱ፡፡ በዚያም ሲደርሱ እንደ-እትዮጵያውያን ሥርዓት የገዳሙ አባት እግራቸውን አጥበው የተቀደሰ ኅብስት ሰጥተዋቸው ከተመገቡ በኋላ እንዲህ አሏቸው፡፡ “ልጆቼ ብልህ ኹኑ፤ የልመናችሁን መልስ እወቁበት” አሏቸው፡፡ እነርሱ ግን አላስተዋሉም ነበርና ይልቁንስ ዐርፈው እግዚአብሔር የሰጠንን ገንዘብ አይሰጡንምን! እያሉ አጉረመረሙ። አባ መርስኤ ሐዘንም ጥቂት ማስተዋልን የሚፈልጉ ሐሳብና ምክር ከሰጧቸው በኋላ ወደ-በዐታቸው ገብተው ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ ሶስት ከበሮዎች ይዘውላቸው መጡ፡፡ ሰዎቹም አብረን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርብ ዘንድ ከበሮ ይዘው መጡ አሉና በደስታቸው ቀጠሉ፡፡ አባ መርስዔም ወደ-ሶስቱ ሰዎች ቀርበው ለእያንዳንዳቸው አንድ አንድ ከበሮ ከሰጧቸው በኋላ እግዚአብሔር እንድሰጣችሁ ያዘዘኝ ይህ ነው አሏቸው፡፡ ከሶስቱ ሰዎች ኹለቱ በእጅጉ ተከፉና አጉረመረሙ፤ ያ የምትሰጠኝ ሀብት አንተን የሚያሳጣኝ ከኾነ ሀብት አትስጠኝ ሲል የነበረው ግን በእጅጉ በደስታ ተሞልቶ “እግዚአብሔርን ማመስገኛ ከመሰጠት የበለጠ ምን ታላቅ ሀብት አለ”` ብሎ በደስታ ተናገረ፡፡ እነዚያም ኹለቱ ሰዎች አንተ ቅንጦተኛ ነህና የእኛንም ከበሮ እነሆ ሶስትና አራት እጅ ካለህ እየመታህ እግዚአብሔርን ታመሰግን ዘንድ ውሰደው ብለው ትተውለት እየተበሳጩ ወደ-ቤታቸው ተመለሱ፡፡ አባ መርስኤ ሐዘንም ቀሪውን ሰው አይዞህ ልጄ አንተ እንዳልከው እግዚአብሔርን ከማመስገን የበለጠ ሀብት የለም፤ በምስጋና ሌላው ትርፍ ነገር ኹሉ ይሰጥሀል አሉት፡፡ አባ መርስዔ ረዳቸውን ጠርተው እነሆ ሶስቱን ከበሮዎች በዚህ ሰው ቤት የሚያደርሱለት ሶስት ሰዎች እንዲያዝዝለት አድርገው ይዞ ሄደ፡፡ ያ ሰው ከበሮዎቹ በተሰጡት በሶስተኛው ዓመት አባ መርስኤ ሐዘን እንዲህ ላኩበት፡ “ልጄ ሆይ ከበሮዎቹ አርጅተዋል፤ አዲስ ቆዳ ገዝተህ ለብጣቸው በየከበሮዎቹ ውስጥ ያሉትን ጠጠሮች ግን ለአንተ ወስደህ እኔ የላኩልህን ጠጠር በውስጣቸው አድርገህ መልሰህ ለብጣቸው አሉት፡፡ እርሱም ሶስት ዓመት ሙሉ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር አምላኩን ሲያመሰግንባቸው የነበሩትን ከበሮዎች ፈትቶ ሲመለከት በከበሮዎቹ ውስጥ የነበሩትና እንደ-ጠጠር ተቀምጠው የነበሩት የእንቁ ጠጠሮች ነበሩ፡፡ በእያንዳንዱ ከበሮ ውስጥ ሶስት የእንቁ እንክብሎችን በጠቅላላው ዘጠኝ የእንቁ እንክብሎች አግኝቶ ከፊሎቹን ሸጦ እጅግ በሀብት የበለጸገ በምስጋናም የታተረ የእግዚአብሔር ልጅ ኾነ፡፡

🔯 እንዲሁ እንደ-ምሳሌው ሰንበት ለእስራኤል ብቻ የተሰጠች የከበረች የዕረፍት ዕለት ናት ሲባል፡ ሰዎች ነገሩን ያቃልሉታል፡፡ እነዚያ በምሳሌው የተነገሩት ሰዎች በከበሮዎቹ ውስጥ እንቁ መኖሩን ሳያውቁ ለሥጋቸው ብቻ አድረው ጥለው እንደሄዱ ኹሉ አሁንም የሰው ልጅ በተለይም ሰንበት/ቅዳሜ የተሰጠቻቸው ብዙዎች እትዮጵያውያን ነገሩን አቅልለው ዕያዩ ገደል ገቡ፤ ለበዛ ጥፋትና መከራም ተዳረጉ፡፡

🔯 ሰንበት የፍጻሜው ዘመን መዳኛ እና ዳኝነት የሚሰጥባት የፍርድ ዐለት ናት፡፡ ሰንበትን የማያከብር እግዚአብሔርን አያከብርም፤ በሰንበት የማያርፍ የዘለዓለም ዕረፍት የለውም፤ ሰንበትን ያላወቀ ድንግል ማርያምን አያውቃትም፡። አንድ የተዋሕዶ አማኝ በተዋሕዶ እምነት አለሁ ለማለት የተዋሕዶን መሠረት ዕረፍታችንን ድንግል ማርያምን እና የድንግል ማርያም የዕረፍትነት አምሳል የኾነችውን ሰንበትን ማክበር ይገባዋል፡፡ አንድ ሰንበትን የሚያከብር ሰው በሰንበት ሥራውን ኹሉ ትቶ መውጣትና መግባትን ታቅቦ በሰንበት ከሥጋ ፈቃዱ ኹሉ ተከልክሎ (ኢሳ/58/13) በምስጋና መዋል ይኖርበታል፡፡ አባ መርስዔ ሐዘን “ብልህ ኹኑ” እንዳሉት የተዋሕዶ ልጆች ብልህ ኹኑ፤ ከበሮዎቹን ንቀው እንደሄዱት ሥጋውያን ሰዎች አትኹኑ! ሰንበት እንቁ ናትና አክብሯት፤ ሰንበትን በማክበር ከመከራ ታመልጣላችሁ በመታዘዛችሁ ከዘለዓለማዊ ሞት ትተርፋላችሁ፡፡

🔯 ይህ ዓለም ገሚሱ በጦርነት፣ ሌላው በርዕደ መሬት፣ ከፊሉ በእሳት ሌላውም በበረድና በጎርፍ፣ የቀረው በዐውሎ ነፋስና በማዕበል ሌላውም በስደትና በረኀብ፡ በቸነፈርም በሰይፍም ታይቶ ያልታወቀ እንግዲህም ወደ-ፊትም የማይታይ መከራ እየወረደበት የሚገኘው ሰንበትን አላከብርም ብሎ በማመጹ የተነሳ ነው፡፡ ስለዚህም፡ እትዮጵያውያን ኹሉ የእግዚአብሔር ልጅነታችሁ ምልክት የኾነችውን ቀዳሚት ሰንበትን ከሥጋዊ ነገር ኹሉ ተከልክላችሁ አክብሩ፤ ፊታችሁን ወደ-እትዮጵያ አምላክ መልሱ፡ እርሱም ይመለሳል፡፡ ነገር ግን አንመለስም በአመጻችን እንቀጥላለን ብትሉ የአመጻችሁን ፍሬ ትበላላችሁ፡ የታዘዙት ሰንበትን የሚያከብሩት ጥቂቶቹ ምድሪቱን ይወርሳሉ፡ እናንተ ግን እንደ-እግዚአብሔር ቃል (ዘሌ/26) ትጠፋላችሁ፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” የምትለው ናት፤ መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አ...
25/07/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ክብርት እትዮጵያ አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 ቅዳሜ ቀን (በሰንበት) ጸብን የሚያነሳ ሰው ሥራን ኹሉ የሚሠራባት ይሙት። (ኩፋሌ 34/19)

🔯 ስለምንድር በዕለተ ሰንበት ጸብ የሚያነሳ ሰው ይሙት ተባለ? አባቶቻችን በብዙ ረቂቅ ምስጢር ተርጉመው ያስረዳሉ፡፡ ዕለተ ሰንበት የእግዚአብሔር የምስጋና ዕለት ናትና በሰንበት ጸብ የሚያነሳ ሰው ምስጋናውን አቋርጧል ማለት ነው፤ ሰንበት ቁርባን እና ብዙ አይነት መሥዋዕት የሚቀርብባት ዕለት ናትና በዕለተ ሰንበት ጸብ የሚያነሳ ሰው ለእግዚአብሔር የሚያቀርበውን የምስጋና መሥዋዕት ትቶ ለአጋንንት የጸብና ክርክር መሥዋዕት ያቀርባል ማለት ነው፤ ሰንበት አምላካችን ከሥራ ኹሉ ያረፈባት ቀን በመኾኗ ዕንደ-አምላክ ዕረፍት ማድረግ የሚገባባት ዕለት ናትና በዚህች ዕለት ጸብ ያነሳ ሰው በጸብ ስፍራ ተገኝቷልና እንደ-አምላኩ ዐላረፈም ማለት ነው፤ ሰንበት በምስጋናና በዝማሬ የምናርፍባት የደስታ ቀን ናትና በሰንበት ጸብ ያነሳ ሰው የዝማሬ አንደበቱ ተዘግቶ ከምስጋና ተለይቶ ደስታ የለውም ማለት ነው፤ ሰንበት የእግዚአብሔር የመንግሥቱ ዕለት ናትና በሰንበት ጸብ የሚያነሳ ሰው ከእግዚአብሔር መንግሥት ወጥቶ በሰይጣን አገዛዝ ተገኝቷል ማለት ነው፤ ሰንበት አማልክትና መላእክት ቅዱሳንም ወደ-አጋዕዝት ሥላሴ ልዩ መሥዋዕት የሚያሳርጉባት ዕለት ናትና በሰንበት ጸብ የሚያነሳ ሰው መሥዋዕቱ በመንግሥተ ሥላሴ አላረገለትም ማለት ነው፡፡

🔯 ስለዚህ ፍቅር ባለበት የእግዚአብሔር መንፈስ በዚያ ያለ ሲኾን፤ በተቃራኒው ጸብ ባለበት በዚያ ደግሞ ርኩስ መንፈስ አለ ማለት ነው፡፡ ስለዚህም የጻድቃን እንቁ የድንግል ማርያም ልጆች የደስታ ዕለት በኾነችው በዕለተ ሰንበት በሰላም፣ በፍቅር፣ ለአምላከ ሰንበት መሥዋዕት በማቅረብ፣ በዝማሬ፣ በማኅሌትና በዕረፍት ከስሉሥ ቅዱስ እግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርባት ልዩ ዕለት እንጂ ጸብ በመቀስቀስ ወይም አንዱ ሌላውን በማሳዘን የዲያብሎስን ግብር የሚገብርባት ዕለት አይደለችም፡፡

🔯 ይህን ስንላችሁ በቀሪዎቹ በስድስቱ ቀናት ተጣሉ፡ ተደባደቡ ወይም አምባጓሮና ክርክር አድርጉ እያልናችሁ አይደለም፡፡ ዳሩ ግን “ለሰው ጌጡስ ንጽህና፣ ጥበብ፣ እውቀት፣ ያለመቅናት፣ ያለ-ምቀኝነት፣ ያለ-መጠራጠር፣ ያለ-ጸብ፡ በሚገባ መዋደድ ነው” (መቃ/3-10/22) ተብሎ እንደ-ተጻፈ፡ የእግዚአብሔር ልጆች ከክፉ ነገር ኹሉ ርቀው በፍጹም መዋደድ መኖር ይገባቸዋል፡፡ ነገር ግን አልፎ አልፎ በመካከል ክፉ ጸባይ ያለው ቢገኝ ነገርን ኹሉ በትዕግስት በማሳለፍ ለራስና ለዚያ ሰው በመጸለይ ክፉ መንፈስ እንዲርቅ ማድረግ ይገባል፡፡

🔯 የዚህን ዘመን እውነታ ስንመረምር ግን፡ በሰባቱም ዕለታት ወንድም ወንድሙን ሲያርድባቸው፣ ሲዘርፍባቸው፣ ሲሰድብባቸው፣፡ ወንድም ሴትም ሕጻንም አዋቂ የተባሉትም እውቀታቸው ለዓለም የሚገለጽበት መንገድ ኀጢአትን መሥራት በኾነበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡፡ ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፡ ኀያልም በኀይሉ ብዛት አያመልጥም” (መዝ/32/16)፣ እንደተባለ ደግሞም “ጌታን በመሠዊያው አጠገብ ቆሞ ዐየሁት፡ እርሱም እንዲህ አለ መድረኮቹ ይናወጡ ዘንድ ጉልላቶቹን ምታ በራሳቸውም ኹሉ ላይ ሰባብራቸው፡ እኔም ከእነርሱ የቀሩትን በሰይፍ እገድላለሁ፤ የሚሸሽ አያመልጥም የሚያመልጥም አይድንም” (ት/አሞጽ/9/1) ተብሎ እንደተጻፈ፡ የዚህ ዘመን ኀያላን እና ጉልበተኞች ነን ባዮች በኀይልና በጉልበታቸው በሠራዊታቸውም ብዛት ደግሞም በጦር መሳርያቸው ረቂቅነት ከመለኮት ፍርድና ቅጣት የሚያመልጡ መስሏቸው በእጅጉ ራሳቸውን አታለሉ፡፡ በዚህ ሰሞን አንዲት አንስት “የአንድ ወገን ሕዝብና ሃይማኖት የሀገር ባለቤት ነኝ ሲል የቆየ ወገን በዚህ ዘመን ሌላ ወገንና ሕዝብ ተነስቶ እየቀጣው እየተበቀለው ይገኛል” በማለት የተናገረችው ጸያፍ ቃል በእጅጉ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ስለምን መቅሠፍትህን በላዬ ላይ ከማዝነብ ዘገየህ እንዳለች ተሰማን፡፡ በእውኑ ሀገርንና እውነተኛን እምነት መውደድ አንዱ በሌላው ላይ ለበቀል እንዲነሳ ያደርጋልን? እግዚአብሔር አምላክ ቅጣት የሚገባውን በሚገባው አይነት፡ በመቅጣት፣ ሰማዕት ኾኖ ማለፍ ያለበትን በወወደደው አይነት በሠማዕትነት፣ ለደጉም ኾነ ለአመጸኛው፡ ለየዋሑም ኾነ ለእብሪተኛው፣ ለሀገር ጠሉም ኾነ ለሀገር ወዳዱ፣ ለርኩሱም ኾነ ለቅዱሱ፣ ለጻድቁም ኾነ ለኀጥኡ፣ ለአሕዛብም ኾነ ለሕዝቡ በቀጠራት ቀን ፍርድን የሚሰጥባት ቀን አለች፡፡ “ትዕቢት ውድቀትን ትቀድማለች” እንዳለ ይህች ሴት ያማረባት ነገርንም ያሳመረች መስሏት ደግሞም ብርቱ የዝቅጠት መንፈስ ባቢሎናዊትነት ተሰምቷት በተናገረችው እነሆ ቃሏ ወደ-መንግሥተ እግዚአበብሔር ዐርጎ የጸሎቷን መልስ በቅርብ እንደምታገኝ ሥላሴን አንጠራጠረውም፡፡

🔯 እኛስ ዘረ ዐዳም ወሔዋን በቅድስት እትዮጵያ ደስ ብሎት አምላኩን ሲያመሰግን ክፉና ክፋት ተወግዶ የሀገራችን የፍቅር ብርሃን ተዋሕዶ ለመላ ምድሪቱ ስታበራ ዓለም ኹሉ የሚያይባት ቀን እጅግ ቅርብ መኾኗን እናውቃለን፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” የምትለው ናት፤ መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደ...
18/07/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ለሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ኮከብ ሥርግው ብርሃናዊት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “ሰንበትን የሚጠብቅ እጁንም ክፋት ከማድረግ የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።” (ኢሳ/56/2) ይህ መለኮታዊ ቃል ቢያንስ ሶስት መሠረታዊ ፍሬ ነገሮችን ያዛል፡- የመጀመሪያው ሰንበትን እንደትእዛዙ ማክበር፤ ኹለተኛው ሕግና ነቢያትን መጠበቅ (እጁን ክፋት ከማድረግ መከልከል) እና ሶስተኛው ሰንበትን ያከበረና ሕግንና ነቢያትን የጠበቀ እርሱ ብጹዕ በእግዚአብሔር ፊት ቅዱስ ነው የሚሉት ናቸው፡፡

🔯 እስቲ በእነዚህ መመዘኛዎች የዚህን ዘመን ጳጳሳትና ካሕናት፣ ቆሞሳትና ላእክ፣ መሪ ጌታና ተማሪ መዝናችሁ በልባችሁ የደረሳችሁበትን መደምደሚያ ለነፍሳችሁ ንገሯት፡፡

🔯 “ይህን ሕዝብ የሚመሩ ያስቷቸዋል፤ ተመሪዎቹም ይጠፋሉ። ሰው ሁሉ ዝንጉና ክፉ ሠሪ ነውና፥ አፍም ሁሉ ስንፍናን ይናገራልና ስለዚህ ጌታ በጕልማሶቻቸው ደስ አይለውም፥ ለድሀ አደጎቻቸውና ለመበለቶቻቸውም አይራራም።” ኢሳ/9/16-17) ተብሎ የተጻፈውን አስተውሉ! ፍጽምትና ዘለዓለማዊት እውነት የኾነች እምነት “ተዋሕዶ” ናት፡፡ ነገር ግን በዚህን ዘመን በውስጧ ያሉ ካሕናት ሳይኾኑ እንደ-ካሕን የጠመጠሙ፣ ሊቀ-ካሕን ሳይኾኑ እንደ-ሊቀ ካሕን አክሊል የደፉ፣ ቅዱስ ሳይኾኑ እንደ-ቅዱሳን የተጎናጸፉ፣ ሐዋርያ ሳይኾኑ እንደ-ሐዋርያት በሰናፌል ያጌጡ፣ በተዋሕዶ እውነት ሳይገኙ በተዋሕዶ መንገድ የሚመላለሱ የሚመስሉ የቅባትና የጸጋ፡ የካቶሊክና የጴንጤ የቡድሃ እና የኤቲስቶች ሐሳውያን እየመሩ ሲያጠፏችሁ ዛሬም እናንተ በእነርሱ በአጥፊዎቻችሁ እግር ስር ትገኛላችሁ፡፡

🔯 ነገር ግን አንዲት ታላቅ እውነት እናውጃለን፡- ጳጳሱ ተዋሕዶን ካደ ማለት ተዋህዶ እምነት እውነት አይደለችም ማለት አይደለም፤ ሐዋርያው ተዋሕዶን መካዱ እምነቷን ሐሰት አያደርግም፤ በተዋሕዶ መቅደስ እባቦችና ቀበሮዎች ገብተው አፏጩባትና አስካኩባት ማለት ተዋሕዶ ጠፋች እምነቷም ሐሰት ናት ማለት አይደለም፤ ጴንጤ የተዋሕዶን መስቀል ያዘ ማለት መስቀል የፕሮቴስታንት ነው ማለት አይደለም፤ ቀስተ ደመናን ግብረ-ሰዶማውያን ተጠቀሙበት ማለት ቀስተ ደመና የድንግል ማርያም መቀነት የሥላሴ ክብር መገለጫ አይደለም ማለት አይደለም፤ ተሀድሶዎች እንደ-ካሕን ጠመጠሙ ማለት ቀጸላ የተሀድሶ ነው ማለት አይደለም፤ አድቬንቲስቶች ሰንበትን/ቅዳሜን አከበሩ ማለት ሰንበት የተዋሕዶ አይደለችም ማለት አይደለም፤ ጴንጤ ከበሮና መሰንቆ፡ ዋሽንትና እንቢልታ ክራርና ጽናጽል ያዘ ማለት እኒህ ንዋየ ቅድሳት የተዋሕዶ ቅዱሳን መሥዋዕት ማቅረቢያዎች አይደሉም ማለት አይደለም፤ አሕዛብ በቤተ መቅደሰ ሥላሴ በእትዮጵያ ጨፈሩ ማለት የእትዮጵያ ምድር የተዋሕዶ አይደለችም ማለት አይደለም፤ ቢዮንሴ እና ተከታዮቿ ደግሞም ግብረ ሰዶማውያን በቅድስት እትዮጵያ ጽሕፈት ቤት ከፈቱ ማለት የተዋሕዶ ቤተ መቅደስ ተዘጋች ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ይህ ኹሉ ሕዝብ ወደ-ተዋሕዶ መሠረት ወደ መድኃኔዓለም አልመለስ በማለቱ እንዲሁም የሚመሩትን ክፉዎች ተከትሎ ድንግል ማርያምን በመተዉ የተነሳ ይህ ኹሉ ለመከራ መፈጸሚያ ኾነበት፡፡ ነገር ግን ለተገለጠለት ለእርሱ ተዋሕዶ ከፀሓይ 7*7 ጊዜ እጥፍ በምድር እያበራች ጠላቶቿን እየተበቀለች ትገኛለች፡፡

🔯 ነገር ግን ቅድስት እትዮጵያ “ዓለም ወደደም ጠላም፤ ቧለተም/አልቧለተም፤ ቀለደም/አልቀለደም”` በተዋሕዶ እምነት ዓለምን/መላ ምድሪቱን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፡፡ ይህን እውነት ሊረዳ የሚችለው የእግዚአብሔር/የቅዱሳን የምስጢር ባለሟል የኾነ ብቻ ነው፡፡ የዓለም ዓይኖች በሙሉ በቅድስት እትዮጵያ ላይ የወደቁበትን ምክንያት ባለ-ርሥት የኾናችሁት እትዮጵያውያን ማስተዋል አቅቷችሁ እነሆ በአውሬው መንጋጋ ውስጥ ወደቃችሁ፤ ተስፋችሁን ድንግል ማርያምን ማመን ትታችሁ በተስፋ መቁረጥ የስንፍና ንግግር ተናገራችሁ፡፡ ስለ-ቅድስት እትዮጰጵያ ነቢያት የዛሬውን አስቀድመው እንዲህ አዩላት፦ “ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፥ በታላቅም ምሕረት እሰበስብሻለሁ። በጥቂት ቍጣ ለቅጽበት ዓይን ፊቴን ከአንቺ ሰወርሁ፥ በዘላለምም ቸርነት እምርሻለሁ፥ ይላል ታዳጊሽ እግዚአብሔር። ይህ ለእኔ እንደ ኖኅ ውኃ ነው፤ የኖኅ ውኃ ደግሞ በምድር ላይ እንዳያልፍ እንደ ማልሁ፥ እንዲሁ አንቺን እንዳልቈጣ እንዳልዘልፍሽም ምያለሁ። ተራሮች ይፈልሳሉ፥ ኮረብቶችም ይወገዳሉ፤ ቸርነቴ ግን ከአንቺ ዘንድ አይፈልስም የሰላሜም ቃል ኪዳን አይወገድም፥ ይላል መሐሪሽ እግዚአብሔር። አንቺ የተቸገርሽ በዐውል ነፋስም የተናወጥሽ ያልተጽናናሽም፥ እነሆ፥ ድንጋዮችሽን ሸላልሜ እገነባለሁ፥ በሰንፔርም እመሠርትሻለሁ። የግንብሽንም ጕልላት በቀይ ዕንቍ፥ በሮችሽንም በሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ዳርቻሽንም ሁሉ በከበሩ ድንጋዮች እሠራለሁ። ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል። በጽድቅ ትታነጺያለሽ፤ ከግፍ ራቂ፥ አትፈሪምም፥ ድንጋጤም ወደ አንቺ አትቀርብም። እነሆ፥ ይሰበሰባሉ፥ ነገር ግን ከእኔ ዘንድ አይሆንም፤ በአንቺም ላይ የሚሰበሰቡ ሁሉ ከአንቺ የተነሣ ይወድቃሉ። እነሆ፥ ፍሙን በወናፍ የሚያናፋ ለሥራውም መሣሪያ የሚያወጣ ብረት ሠሪን እኔ ፈጥሬአለሁ፤ የሚያፈርሰውንም እንዲያጠፋ ፈጥሬአለሁ። በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም፤ በፍርድም በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ። የእግዚአብሔር ባሪያዎች ርስት ይህ ነው፥ ጽድቃቸውም ከእኔ ዘንድ ነው፥ ይላል እግዚአብሔር።” (ኢሳ/54/7-17)

🔯 እንግዲህ ከእግዚአብሔር የተማሩ ቅዱሳን ያሉባት ሀገር ቅድስት እትዮጵያ ናት፡፡ እስቲ ልባችሁ ለነጭ አእምሯችሁም ለፈረንጅ የስህተት ትምሕርት መገዛቱን ትቶ ጥቂት ያስተውል! በጂቡቲ ቻይና፣ ጃፓን፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ባቢሎን፣ ፈረንሳይ፣ ራሽያ ወዘተ ተሰባስበው የሚጠብቁት ማንን ይመስላችኋል! በሶማልያ ግብጽ፣ ባቢሎንና የተባበሩት መንግሥታት ጦር፣ በኬንያ እነ-እንግሊዝ፣ ባቢሎን፣ ግብጽ፣ ወዘተ፣ በቀይ ባሕር ከ40 ሀገራት የላቁ ማንን ከብበው ያሉ ይመስላችኋል! በሱዳንና በሌሎች ዐረብ ሀገራት ያሉ የአሕዛብ ነገሥታት ስለምን በቅድስት እትዮጵያ ላይ ያፈጠጡ ይመስላችኋል! በጎንደር ወይም በወሎ ወይም በጎጃም ወይም በሸዋ አንድ ሙስሊም ተገደለ ሲባል ስለምን ኢራንና ቱርክ መግለጫ ይሰጣሉ! ስለምን ሳይንቲስቶች የሰው ዘር መገኛ የዐዳምና የሔዋን መፈጠሪያ እትዮጵያ መኾኗን አመኑ! ስለምን ምዕራባውያንና እነ-ቻይና ባቢሎንም፣ ካናዳም፣ ራሽያም ዕብራውይቱ እስራኤልም ለሕዝባቸው የአማርኛን ቋንቋ ለማስተማር በየሥርዓተ ትምሕርተታቸው አካተቱ! ስለምን ወ/ሮ ጀርመን በአማርኛ ቋንቋ የዶክተሬት ዲግሪ ትሰጣለች! ስለምን በሌሎች ሀገራት ቋንቋዎች ትምሕርት አልተጉም! ሌላ የተሻለ ቋንቋ አጥተው ነውን? እንጃላችሁ! እናንተው መርምሩት፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ፡፡

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

  🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡  ✡  ✡በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ቀስተ ደመና ብርሂት አደረሰን አ...
11/07/2026



🕎 🕎 🕎 🟢 🟠 🔴 🔵 ✡ ✡ ✡

በምድርና በሰማያት አጽናፋት ያላችሁ ሠራዊተ እግዚአብሔር እትዮጵያውያን እንኳን ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ/ዘ ዕለተ ሰንበት ቀስተ ደመና ብርሂት አደረሰን አደረሳችሁ!!!

🔯 “በሰባተኛይቱ ቀን “በሰንበት” በደመና መካከል ኾኖ ሙሴን ጠራው የእግዚአብሔርም ብርሃን በተራራው ራስ ላይ እንደ-እሳት ሲነድድ ዐየ።” (ኩፋሌ 1/3)
ከዚህ በላይ የተጠቀሰው መለኮታዊ ቃል የሰንበትን ኀያልነት በእጅጉ የሚያስረዳን ነው፡፡ አጋዕዝት መለኮት ሙሴን የጠራው በሰባተኛዋ ዕለት በሰንበት መኾኑን አስተውሉ፤ እንዲሁ እኛም በሰንበት ዕረፍት እግዚአብሔርን ማመስገን ትተን ከቤታችን ወጥተን የምንቅበዘበዝ ቢኾን፡ እግዚአብሔር በሰንበት ሲጠራን በፊቱ አንገኝም ማለት ነው፡፡ ሰንበት ፍጥረታት ከአምላካቸው ጋር የሚገናኙባት ዕለት እንጂ ከሥራ እና ከዓለም ጋር የሚገናኙባት ዕለት አይደለችም፡፡
ሌላኛው ፍሬ ነገር፡ “ሙሴ በተራራው ራስ ላይ እግዚአብሔርን ዐየ” የሚለው ሲኾን፤ እንዲሁ እኛም በተጠራን ጊዜ፡ እግዚአብሔር አምላክ ሊያነጋግረን በወደደ ጊዜ፡ በሰንበት ዕረፍት ካልተገኘን እርሱን የተገዛንለትን አምላክ እናየው ዘንድ አይቻለንም፡፡ ለዚህም ነው፡ የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ጠራሁት አልሰማኝም፤ ለመንኩት አልሰጠኝም፤ ወዘተ… እያለ አምላኩን የሚያማርረው፡፡ አንድ ሰው ወደ-አምላኩ ከጮኸ በኋላ ልመናው የተሰማለት መኾኑን የሚያውቀው በሰንበት ዕረፍት በስፍራው ተገኝቶ እግዚአብሔር ሲመልስለት ነው፡፡

🔯 አንድ ምሳሌ እንንገራችሁ፡- ኹለት ሰዎች ከየሚኖሩበት ክፍለ ሀገር ተነስተው ለንግድ ወጥተው በመንገድ ተገናኝተው ጓደኛሞች ኾነው አብረው በመንገድ ሲጓዙ ሰባት ኪሎ ወርቅ አገኙ፡፡ ወርቁ ብዙ ስለነበርና ኹለቱም ሰዎች ትሑታን ስለነበሩ ተማምነው እየተፈራረቁ ተሸክመው በመሄድ ላይ ሳሉ እንዲህ ተነጋገሩ፡- “የሚያሳድደንና ወርቃችንን የሚቀማን ሰው ቢያጋጥመን ወርቁን የያዝነው አንዳችን ከወንበዴ ባመለጥን ጊዜ በዚህች ዋሻ ውስጥ እንገናኝ፣ ተባብለው ጥቂት ከተጓዙ በኋላ የገመቱት አልቀረም ሶስት ሽፍቶች ከእረኛ ፍየል ቀምተው አርደው በልተው ጠግበው እየተጫወቱ አገኟቸው፡፡ ሽፍቶቹም ጓደኛሞቹን ቁሙ ሲሏቸው ወርቁን ያልያዘው ሲቆም ወርቁን የያዘው ወርቁን በነጠላው ሸፍኖ ወደ-ኋላው ሸሸ፡፡ ሽፍቶቹም ወርቅ የያዘው ሰው ወርቅ ስለመያዙ አልተረዱም ነበርና ጥቂት አባረውት ተመልሰው በእጃቸው ያስገቡትን ነጋዴ በል የዚህችን ፍየል እግር ጠብሰህ አብላን ብለውት እሳት ሲቆሰቁስ ውሎ ወደ-ማታ ሲኾን ለቀቁት፡፡ ሽፍቶች የለቀቁት ይህ ሰው ከጓደኛው ጋር በተቀጣጠሩበት ዋሻ ሊጠብቀው ሲገባ፡ ባለ-ወርቁን ጓደኛውን ባልተቀጣጠረበት ስፍራ በየጫካው ሲፈልግ ይነጋና ይመሽ ነበር፡፡ ወደ-ባለ-ወርቁ ቤት እንዳይሄድ ከየት ሀገር እንደመጣ ገና በመነጋገር ላይ ሳሉ ነበር ወርቁን በማግኘታቸው ደስታ ተሞልተው ሳይጠያየቁ ስለወርቅ ሲያወሩ መንገዱን የፈጁት፡፡ ወርቁን የያዘው ሰው ግን በታማኝነት እንዲገናኙ በተቀጣጠሩባት ዋሻ ተገኝቶ ነበርና፡ እገሌ እያለ በአካባቢው ላይ ቢጣራም አላገኘውም፡፡ ባለወርቁም ለሰባት ቀናት ያህል የዛፍ ፍሬ እየበላ ከአውሬ ጋር እየታገለ ይመጣ እንደኾን ብሎ ቢጠብቀውም አልመጣም፡፡ በስተመጨረሻም፡ እንግዲህ ይህ ወርቅ የኹለታችን እንጂ የእኔ ብቻ አይደለምና ምናልባት አንድ ቀን ወደዚች ዋሻ ሊፈልገኝ ሲመጣ የድርሻውን ይወስድ ዘንድ ላስቀምጥለት ይገባል ብሎ ወርቁን እኩል ለኹለት ከፍሎ ሶስት ኪሎ ከግማሽ የሚኾነውን በዋሻዋ ውስጥ በስተጎን ቀብሮ በላዩ ላይ ቆፍረህ ድርሻህን ውሰድ ብሎ ጽፎበት ሄደ፡፡ ነገር ግን አንዲት እግሯ በመሰበሩ የወደዱትን ያህል ልታገለግላቸው ባለመቻሏ ዘመዶቿ የጠሏት እናትና አባቷ በልጅነቷ ሕይወታቸው አልፎ የሕይወት ዘመኗን ወደ-አምላኳ በመጮህ ታሳልፍ የነበረች የ24 ዓመት እድሜ የነበራት ወጣት ምርኩዝ ይዛ እግሯ ወደ-መራት ሀገር ለመሰደድ ቆርጣ በለቅሶ እየተጓዘች ሳለች ዝናብ ደርሶባት ወርቅ በተቀበረባት ዋሻ ተጠለለች፡፡ በዚያ ቁጭ ብላ የዋሻዋን አሠራር ስታደንቅ ዓይኖቿ ድንጋይ በተጫነባት ወረቀት ላይ ዐረፉ፡፡ እርሷም ደንጊያዩን አንስታ ወረቀቱን ስታነበው “ቆፍረህ ድርሻህን ውሰድ” ተብሎ ተጽፎበት ነበር፡፡ ዓይኖቿን ወረቀቱን ወዳገኘችበት ቦታ ላይ ስታማትር በቅርብ የተቆፈረ የሚመስል አፈር አየች፡፡ እርሷም በውስጡ ምን ይኖር ይኾን ብላ ስፍራውን በእንጨት ጫር ጫር ስታደርግ በቀላሉ ሲቆፈርላት በልቧ መልካም ነገር አገኛለሁ የሚል ተስፋ ባይኖርም፡ የወረቀቱን መልእክት ለማረጋገጥ ስትል መቆፈሯን ቀጠለች፡ ወጣቷ ጥቂት እንደቆፈረች የሚያብለጨልጭ ነገር ዐየች፤ በጉጉት ስትቆፍር ሶስት ኪሎ ከግማሽ የሚኾነውን ወርቅ አግኝታ እጅግ ደስ አላት፡፡ እርሷም እግዚአብሔር ለቅሶዬን ዐይቶ የሰጠኝ የእንባዬና የመገፋቴ መልስ ነው ብላ ወርቋን ይዛ ወደ-ሀገሯ ተመልሳ፡ ወርቁን ሸጣ በዝና የታወቀች ባለሀብት ኾነች ይባላል፡፡

🔯 ከዚህ ምሳሌ ላይ፡ እንደምንረዳው፡ ሽፍቶች የለቀቁት ሰው መገኘት በነበረበት ስፍራ ባለመገኘቱ ወርቁን አጣ፤ እንዲሁ በሰንበት ዕረፍት እንዲገኙ የታዘዙ በሰንበት ካላረፉ የሚፈልጉትን እግዚአብሔርን አያገኙትም፡፡ ሽፍቶች የለቀቁት ሰው ባልተቀጠረበት ስፍራ ባለ-ወርቁን ፍለጋ ሲቅበዘበዝ እንደ-ከረመ እንዲሁ በሰንበት የሚሠሩ አምላካቸውን ሲለምኑ ቢኖሩም፡ ነገር ግን ጩኸታቸው ሳይሰማ በከንቱ ልፋት ይኖራሉ፡፡ ዳሩ ግን የተገፋችውና በሰንበት ዕረፍት የበለጸገችው ወጣት በዋሻ በሰንበት ዕረፍት በማረፏ የልመናዋን መልስ አግኝታ የጠሏት እስኪያደንቋት ድረስ ባለ-ዝና ኾነች፡፡

🔯 ስለዚህ፡ ኹላችሁም በሕመም ላይ ያላችሁ፣ በሰልፍ ላይ ያላችሁ፣ በሐዘን ላይ ያላችሁ፣ በማጣት ችግር ላይ ያላችሁ፣ በስደት ላይ ያላችሁ፣ በግዞት ላይ ያላችሁ፣ በሥቃይ ላይ ያላችሁ፣ በብቸኝነት ላይ ያላችሁ፣ በምቾት ላይ ያላችሁ በድህነት ያላችሁ፣ በመራቆት ምሬት ላይ ያላችሁ ኹላችሁ መጀመሪያ እግዚአብሔር መልስ የሚሰጥባትን ድምጹን የምትሰሙባትን ዕለት ሰባተኛዋን የጽዮንን ሰንበት አክብሩ፡፡ የታዘዘ የመታዘዙን ፍሬ ሲበላ አመጸኛ ደግሞ የአመጹን ፍሬ ይበላል እንጂ መልካም ፍሬ አይመገብም (ኢሳ/1/19-20) ለእትዮጵያውያን የተሰጠችውን ዕለተ ሰንበትን በማክበር ከምጽአቱ መዓት ከፍርዱ ቁጣ ማምለጥ መዳን ይገባል፤ ይህን የማያደርግ ግን ባለመታዘዝ በራሱ ፈረደ እንጂ ሌላ ፈረደብኝ አይበል፡፡ የተዋሕዶን እምነት ከሰንበትና ከከበረች እትዮጵያዊነት ጋር አስተባብራችሁ ያዙ፡፡

🔯 እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር… አ…ጋ…ዕ…ዝ…ት… መ…ለ…ኮ…ት… አ…ሐ…ዱ… አ…ም…ላ…ክ… ከመላእክቱና ከቅዱሳኑ ጋር በገሃድ በቅድስት እትዮጵያ ተገልጾ የቅድስት እትዮጵያን ክብር እየገለጸ፤ ለቅዱሳኑ የሰንበትን የዕረፍት ዋጋ ሲከፍል በአሕዛብ ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን እያወረደ ይገኛል፡፡ በተተዋሕዶ እምነት በመታዘዝ ክበሩ፤ በመታዘዝ ዳኑ፤ በመታዘዝ የአጋዕዝት ሥላሴን ቃል በተግባር በመኖር ከፍጻሜው የቁጣ መቅሠፍት አምልጡ፡፡ ለሚያስተውሉ የተገለጸች ለማያስተውሉና ለማይታዘዙ የተሠወረች እውነት አለች፤ እርሷም “እትዮጵያ በተዋሕዶ ዓለምን አንድ አድርጋ እየገዛች ነው፤” መጨረሻው ሲገለጥ ለማያምኑትም ኹሉ ይታያል፡፡

🔯 በሰንበት የምታርፉ ዘርዐ ዐዳም ወሔዋን የርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር ኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ኾኖ ይብዛላችሁ፤ ሰንበትን በሰልፍ ላይ ኾናችሁ ለምታከብሩት ርእሰ ኀይላተ እግዚአብሔር ኤልያስ ሰልፋችሁን ይቁረጥላችሁ፤ ነገር ግን በሰንበት ዕረፍታችን በድንግል ማርያም ላይ በምትሳለቁት በቅድስት እትዮጵያ ጠላቶች ላይ ለፍርድ የተገለጸው ሙሽራ ነቢየ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኤልያስ ፍቅሩን ይግለጽባችሁ!!!

🕎 እትዮጵያ!!! ሀገረ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ማርያም እመ ኩሉ ፍጥረት ወላዲተ አምላክ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ጽዮን መቅደስ፡ ወዙፋነ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ኤልያስ ርእሰ ሠራዊተ እግዚአብሔር፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አድማኤል ኪሩብ/ዐዳም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሕያኤል/ሔዋን፤
🕎 እትዮጵያ ሰማያዊት እየሩሳሌም፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ሐዋርያተ መለኮት ወልድ ዋሕድ፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ ቅዱሳን፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ መላእክት፤
🕎 እትዮጵያ ሀገረ አማልክት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ አርባእቱ መዛግብት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ግእዝ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ተዋሕዶ፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ሰንበት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ገነት፤
🕎 እትዮጵያ ሰማየ ሰማያት፤
🕎 እትዮጵያ ምድረ ፍትሐ ፍጻሜ፡፡

ሞዓ አንበሳ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ በአካል ለፍጻሜ ፍርድ ተገልጾ ከነገሠባት መቅደሱ እም ሀገረ እግዚአብሔር ወማርያም ወምድረ ገነት ቅድስት እትዮጵያ

አልሰማሁም የሚል ይስማ
አላደመጥኩም የሚል ያድምጥ፡
For any elaboration or spiritual questions:
ጥያቄ/ማብራርያ ለምትሹ፤
Contact with 0910-12-72-72
Everyday from Monday to Friday mid-day 6:30-7:30, night time 1-3 and on Sunday at any time.
ዘወትር ሰኞ እስከ ዐርብ ከቀኑ 6፡30 እስከ 7፡30 ማታ ከምሽቱ 1-3 ሰዓት እና እሑድ ሙሉ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ ልታገኙን ትችላላችሁ።

መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሐቲ ጉባኤ ሰማያዊት።

#ሰንበት #ተዋሕዶ #እትዮጵያ

በፌስቡክ፦ https://facebook.com/mengesteselassie

በዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/

በቲክቶክ፦ https://tiktok.com/

የእትዮጵያ አምላክ እግዚአብሔር ለመጨረሻው ፍርድ በአካል እንደመጣና አሮጌው ሰማይና ምድር እያለፈ፥ አዲስ ሰማይና ምድርም እየተዘረጋ መሆኑን ለፍጥረት ሁሉ ማወጅ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251927616937

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to መንግሥተ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ Mengeste Selassie Ze Dekike Elias:

Shortcuts

Share