10/09/2026
#የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የ2019 ዓ.ም የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት #መልዕክት
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አዲሱ ዓመት ለመላው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፣ ለመላው ኢትዮጵያውያን እና በዓለም ለሚትገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የፍቅር፣ የተስፋና የብልጽግና ዓመት እንዲሆንላችሁ ይመኛል።
አዲስ ዓመት አዲስ ዘመን ብቻ ሳይሆን፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ትብብርና የተሻለ ነገን በአዲስ መልክ ለመጀመር ዕድል የሚሰጠን ዓመት ነው። ስለዚህ በአዲሱ ዓመት ከፍርሃት ይልቅ ተስፋን፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን፣ ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን፣ ከግጭት ይልቅ ሰላምን እንድናስቀድም በጉባኤያችን ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን።
#ኢትዮጵያ በብዝሃነት ደምቃ የተለያዩ ሃይማኖቶች፣ ማህበረሰቦች ተከባብረው የሚኖሩባት የብዝሀ የማንነት ሀገር ናት። ይህ ብዝሃነት የመከፋፈል ምክንያት ሳይሆን የጋራ ጥንካሬያችን የሀገራችን መገለጫ እና የጋራ ሀብታችን እንዲሆን ሁላችንም እንደ ቀድሞ ሁሉ በአዲሱ ዓመትም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል።
የሃይማኖት ተቋማት እንደ ሁልጊዜው ሰላምን ለመገንባት፣ ማህበራዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የሰው ልጆች ክብር እንዲጠበቅ መስራት፣ ርህራሄንና መተሳሰብን ለማሳደግ እና ለሀገራዊ ሰላም፣ ልማትና ልዕልና ከመፀለይና ዱኣ ከማድረግ ባለፈ እንደ ቀድሞ ሁሉ በጋራ ለመስራት አጋርነታችንንና ቁርጠኝነታችንን የምናሳይበት ዓመት ሊሆን ይገባል።
በዚህ #አዲስ ዓመት ለወጣቶቻችን አዲስ ተስፋና ዕድል፣ እንዲሆንላቸው ለመላው ማህበረሰባችን ፍቅርና ሰላም፣ ለሀገራችን አንድነት መረጋጋት፣ ዕድገት ልማት እና የተሻለ ሰላማዊ ኑሮ እንዲሆንላቸው እንመኛለን።
ዓመቱ የሰላም ዓመት፣ የአንድነት ዓመት፣ የተስፋ ዓመት የመልካም ለውጥና ዕድገት ዓመት እንዲሆንልን እየተመኘን ፈጣሪ ለአዲስ አበባና ለመላው ኢትዮጵያዊያን ሰላሙን፣ ፍቅሩንና በረከቱን እንዲያበዛልን እንመኛለን።
በመጨረሻም አዲስ ዓመት ስንቀበል ለአቅመ ደካሞች ካለን በማካፈል በመደገፍ የታመሙትን በመጠየቅ የታረዙትን በማልበስ አምላክ ለሰው ልጆች ያሳየውን ፍቅር በማሳየት አዲሱን ዓመት እንድንቀበል በጉባኤያችን ስም ጥሪያችንን እናቀርባል።
በድጋሚ #እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሠላም በጤና አደረሳችሁ! እያልን አዲሱ ዓመት የሰላም የፍቅር የአብሮነት የመከባበር የዕድገትና የበረከት ዓመት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 2019ዓ.ም
ጳጉሜ 4/2019ዓ.ም
በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/