የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ Ircaa

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ Ircaa We work to be an excellent and united Inter –Religious Forum!!

1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ ይከበራል።*****************የ1447ኛው ዓ.ሒ (የ2018) የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ እንደሚከበር ...
22/05/2026

1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ ይከበራል።
*****************
የ1447ኛው ዓ.ሒ (የ2018) የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የፊታችን ረቡዕ እንደሚከበር የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አስታወቀ።

ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤቱ በዓሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፣ ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በመግለጫው፣ ዋናው የሐጅ ቀን (ውቅፍ ዓረፋ) ማክሰኞ ዙል ሒጃ 9 ቀን መሆኑን ጠቅሶ፣ ዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) ረቡዕ ዙል ሒጃ 10 (ግንቦት 19) ቀን ተከብሮ እንደሚውል አስታውቋል።

በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን #መልካም ምኞቱን የገለጸው የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት፣ ምዕመናን በዓሉን ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳት እንዲያከብሩት ጠይቋል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት...
21/05/2026

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብርን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመግለጫቸው፣ ሀገር አቀፍ የሰላምና የአብሮነት የጸሎት መርሃ ግብሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በጋራ የሚሳተፉበት ሲሆን በመርሐ ግብሩ የሰላም እና የአብሮነት መልዕክቶችን ማስተላለፍ፣ የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ፣ እንዲሁም በህዝቦች መካከል ሰላምና አብሮነትን ማጠናከርና ለሀገር መቆም ዋነኛ ትኩረቱ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ኅብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ በማግኘት በመርሐ ግብሩ ላይ እንዲሳተፍ የመገናኛ ብዙኃን ኋላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ግንቦት 16 ቀን 2018 ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄደው መርሐ ግበር የጋራ እሴቶችና አንድነትን የሚያጎሉ መልዕክቶች እንደሚተላለፉም የተጠቀሰ ሲሆን ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ ለሕዝቦች መተሳሰብ እና አብሮነት መጽናት በጋራ ጸሎት እንደሚካሄድም ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው ከዚህ ቀደምም በተለያዩ ወቅቶች መሰል ሀገር አቀፍ የጸሎት መርሐ ግብሮችን ሲያካሂድ መቆየቱን ያስታወሱ ሲሆን በዚህ መርሃ ግብር ላይ የሁሉም የጉባኤው አባል ቤተ-እምነት ተቋማት የሃይማኖት መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ጠቅሰዋል።

ምንጭ Ethiopian News Agency

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

11/05/2026

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ አመራሮች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጉብኝት።

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

🔴በመጨረሻ የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት
05/05/2026

🔴በመጨረሻ የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!! ➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe https://www.youtube.com/➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ https://t.me/IRCAA2020➽ ዌ...

🔴ክፍል 02 የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት
30/04/2026

🔴ክፍል 02 የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት

1 like. "🔴ክፍል 02 የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት"

የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት ክፍል 01
29/04/2026

የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት ክፍል 01

የጎዳና ላይ ስብከትና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌል አማኞች መሪዎች ጋር የተካሄደ ውይይት ክፍል 01

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ አመራሮች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ።መሪዎች በጉብኝታቸው ኢንስቲትዩቱ ያለዉን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ የሚያስቃኝ...
29/04/2026

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ አመራሮች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ።

መሪዎች በጉብኝታቸው ኢንስቲትዩቱ ያለዉን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ የሚያስቃኝ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ተቋሙ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዙ የፈጠራ ሥራዎችን በማበልጸግ በሀገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑም ተገልጿል።

ተቋሙ እያከናወነ ያለው ተግባር ሀገራችን ለእድገት እየሰራች ባለችባቸው ዘርፎች ለማገዝ በጤና፣ በግብርና፤ በትምህርት እና በሕክምና ጨምሮ በዲጂታል ዘርፍ በከፍተኛ ሁኔታ የማገዝ ስራ እያከናወነ መሆኑን ተገልጿል።

ኤ.አይ ለሁሉም የሚለው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሀገር ከኤ.አይ ቴክኖሎጂ የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ በመከናወን ላይ ያሉ ተግባራትን ለጉባኤያችን ቦርድ አመራሮች ገለጻ ተደርጎላቸዋል።

መሪዎች በበኩላቸው በተመለከቱት ነገር መደነቃቸውን ገለጸው ተቋሙ ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሚበለጽግበት እና ለትዉልድ የሚተላለፍ አቅም ያለበት ስፍራ መሆኑን ገለጸው እየተሰራ ያለውን ስራ አድንቀዋል።

መሪዎቹ የሮቦቲክስ ወርክሾፕ የምርት ማሳያ ክፍሎች እንዲሁም የኤ.አይ ስታርታፕ ማዕከልን ጎብኝተዋል።

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በተቋሙ ለተደረገልን አቀባበል እና መስተንግዶ ምስጋናውን ያቀርባል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

29/04/2026

የጎዳና ላይ ስብከት እና ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ከወንጌላውያን መሪዎች ጋር የተደረገ ዉይይት 🙏🙏

ሙሉዉን ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ https://youtu.be/qNwwLzl6JZE

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 4ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባ ተካሄደ።የጉባኤያችን ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ የ2018ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የስራ ሪፖርት እና ዝርዝር ተግባር ለ...
29/04/2026

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 4ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባ ተካሄደ።

የጉባኤያችን ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ የ2018ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የስራ ሪፖርት እና ዝርዝር ተግባር ለጉባኤው የቦርድ አመራሮች ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ የጉባኤያችን የቦርድ አመራሮች ዉይይት አካሂደው ውሳኔ አሳልፈዋል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

የጎዳና ላይ ስብከት ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ።የጎዳና ላይ ስብከት፤ ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እና የሚዲያ አጠቃቀምን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞ...
23/04/2026

የጎዳና ላይ ስብከት ግጭት ቀስቃሽ የሚዲያ መልዕክቶችን በተመለከተ ውይይት ተካሄደ።

የጎዳና ላይ ስብከት፤ ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እና የሚዲያ አጠቃቀምን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል አመራሮች ጋር ምክክር ተደረገ።

በምክክሩ የሚዲያ አጠቃቀም እና ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን በተመለከተ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሚገባ ተጠቅሷል።

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ የሚዲያ አጠቃቀም እና ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን፤ የጎዳና ላይ ስብከት እና የድምጽ ብክለትን በተመለከተ ያሉትን ተግዳሮቶች እና የስረዓተ አምልኮ ቦታ አጠቃቀምን በተመለከተ ሰፋ ያለ ጽሑፍ አቅርበዋል።

በጽሁፋቸው መዲናችን አዲስ አበባ የአለም አቀፍ 3ኛ የዲፕሎማቲክ ከተማና የአፍሪካ መዲና መሆኗን ጠቅሰው ለሀገራችንም ይሁን ለከተማችን ስንሰራ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ መረዳት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

መጋቢ ታምራት አክለው ሃይማኖቶች በትምህርት ፤ በጤናና በብሔራዊ ጥምቅን ጨምሮ የፕብሊክ ዲፕሎማሲ ስራ ፤ የሰላም እሴት ግንባታ ፤ የትውልድ ስነ-ምግባር፤ ማህበራዊ ስራዎችን በመስራት በሁለንተናዊ መንገድ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ አበርክቶ እንደነበራቸው በጽሁፋቸው አንስተዋል።

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከ2014 ጀምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ “ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ የግጭት መነሻ ምክንያቶች” በሚል ሃሳብ በሁሉም ክፍለ ከተማዎች የዳሰሳ ጥናት ማድረጉን እና በዚህም ችግሮቹን መለየቱን አንስተው ያሉ ክፍተቶች እንዲቀረፉ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ መጋቢ ታምራት አክለው ተናግረዋል።

በቀረበው ጽሁፍ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝደንት ቄስ ደረጄ ጀምበሩ በበኩላቸው ወንጌል አማኞች በሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ በርካታ ሚና እንደነበራቸው ጠቅሰው ካውንስሉ ይህንን በማጠናከር ረገድ የእስትራቴጂ እቅዱ አካል አድርጎ እንደሚሰራ በመጥቀስ የማጠቃለያ ሃሳብ ስተዋል።

ካውንስሉ ለሃገራችን ብሎም ለከተማችን ሰላም እሴት ከፍተኛ ስራ እየሰራ መሆኑን አንስተው ይህንን ለማጠናከር ከአባል ቤተዕምነቶች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ እና ለሀገራችን ብሎም ለከተማችን የሚያበረክተውን አስተዋጾኦ ከፍ እንደሚያደርግ የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ጌትነት ለማ (ዶ/ር) ናቸው።

በመድረኩ የተሳተፉ የካውንስሉ የስራ አስፈጻሚ አመራሮች በበኩላቸው የተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ለሀገራችን እና ለከተማችን ያላቸውን ፋይዳ ተመልክተው በጋራ ለመስራት እና ያሉ ክፍተቶችንም ለመቅረፍ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የወንጌል አማኞች ለሀገረ መንግስት ግንባታ የነበራቸው ሚና አሁንም አጠንክረውን እንደሚቀጥሉ የተነሳ ሲሆን ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላት መሰል ውይይቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም በመድረኩ ተገልጿል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች #ቤተሰብ ይሁኑ !!! መረጃዎችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ!!
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Subscribe
https://www.youtube.com/
➽የቴሌግራም ገጻችን Subscribe ያድርጉ
https://t.me/IRCAA2020
➽ ዌብ ሳይታችንን ይጎብኙ
https://ircaddisababa.org/

Address

Addis Abeba, Ethiopia AMBASSADOR
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ Ircaa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ Ircaa:

Share