Evangelical MEDIA/Council

Evangelical MEDIA/Council የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
(1)

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ለሕዝብ ጤና ጥበቃ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ...
28/04/2026

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ለሕዝብ ጤና ጥበቃ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የተመራ የልዑካን ቡድን ከኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በሁለቱ ተቋማት የትብብር ሥራዎች ዙሪያ ፍሬያማ ምክክር አደረጉ።
በውይይታቸውም ቀደም ሲል በጋራ በመሥራት የኮቪድ-19 ወረርሽኝን እና የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ተገምግሟል።

ሀገራችን በራሷ አቅም የተሟላ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ለጀመረችው ጉዞ፣ የሃይማኖት ተቋማት ያላቸውን ተፅዕኖ በመጠቀም ግንዛቤ የመፍጠርና የማህበረሰብ ጤናን የመጠበቅ ሥራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተስማምተዋል።

የጤና ተቋማትን ከጉባኤው ቅርንጫፍ መዋቅሮች ጋር በማስተሳሰርና በቀጣዩ የበጀት ዓመት የሁለቱ ተቋማትን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራትን በመለየት በተደራጀ መልኩ ለመሥራት አቅጣጫ ተቀምጧል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የማህበረሰብን ጤና ለማስጠበቅ እና ወረርሽኞችን ፈጥኖ ለመቆጣጠር ከጤና ሚኒስቴር ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ ይቀጥላል።

ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ
የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት

27/04/2026

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የ100ኛ አመት በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራሮች የተገኙበት ግብረ ሃይሎችን የማቋቋም መርሃግብር በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጽሕፈት ቤት ዛሬ ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

በስፍራውም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቃላይ ጸሐፊ ፓስተር ጌትነት ለማ(ዶ/ር) እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ ተገኝተዋል።

በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ለስድስት ወራት ሲሰጥ የቆየው የተተኪ መሪዎች ስልጠና በጉለሌ ጰውሎስ አጥቢያ በድምቀት ተጠናቋል።የ...
27/04/2026

በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ለስድስት ወራት ሲሰጥ የቆየው የተተኪ መሪዎች ስልጠና በጉለሌ ጰውሎስ አጥቢያ በድምቀት ተጠናቋል።

የስልጠናው መጠናቀቂያ ዋና ዋና ኩነቶችን ሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም፡ የመጨረሻው ስልጠና በመጋቢ ኤርምያስ ገ/መድህን "የ21ኛው ክፍለ ዘመን የወጣቶች ተግዳሮት እና የወጣቱ ምላሽ" በሚል ርዕስ ተሰጥቷል።

ሚያዝያ 18/2018 ዓ.ም፡ በጉለሌ ጰውሎስ አጥቢያ ቤተክርስቲያን በተከናወነው የምረቃ ስነስርዓት የክልሉ ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰለሞን በንቲ እና የስአኮ ጸሐፊ መጋቢ ሽመልስ ደምሴ እንዲሁም የአጥቢያ መሪዎች ተገኝተዋል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰለሞን በንቲ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፡ "ተመራቂዎች ቤተክርስቲያናቸውን በመውደድ በታማኝነት፣ በጽናት እና የወንጌልን ተልዕኮ በድል እንዲወጡ" ጥሪ አቅርበዋል። እንዲሁም ወጣቶችን ለስልጠና የላኩ አጥቢያ መሪዎችን በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።
በመጨረሻም ለተመራቂዎች የእውቅና ሰርትፍኬት አበርክተው፣ የኬክ ቆረሳ ፕሮግራም በመከናወን እና ለተተኪ መሪዎች የጸሎት ፕሮግራም በማድረግ የምረቃው ስነስርዓት ተጠናቋል።

ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
መረጃውን ከቤተክርስቲያኑ ገፅ ላይ አገኘነው

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ

የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://youtube.com/
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ 0991827226 ላይ ያገኙናል

መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የመሐል ባህር ዳር አጥቢያ አዲሱን ህንጻ አስመረቀች።የመሐል ባህር ዳር መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በ30 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባችውን ዘመናዊ ህንጻ ...
27/04/2026

መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የመሐል ባህር ዳር አጥቢያ አዲሱን ህንጻ አስመረቀች።

የመሐል ባህር ዳር መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በ30 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባችውን ዘመናዊ ህንጻ በትላንትናው ዕለት አስመረቀች።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ፣ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት አዳራሹ ለእግዚአብሔር መንግስት አገልግሎት እንዲውል በይፋ ተመርቋል።

ይህ ዘመናዊ አዳራሽ ከ2,000 በላይ ምዕመናን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ እንደሚችል ተገልጿል።

ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
መረጃውን ከቤተእምነቱ ገፅ ላይ አገኘነው

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ

የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://youtube.com/
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ 0991827226 ላይ ያገኙናል

ዶ/ር ማሙሻ 11 ሚሊየን ብር ለቤተ ክርስቲያን ሰጠዶ/ር ማሙሻ ለኢትዮጵያ ሕይወት ብርሐን አጥቢያ 11 ሚሊየን ብር ለአገልግሎት ማእከል ግንባታ ከመጽሐፉ የተገኘዉን ገቢ ሰጠ! “መንፈሳዊ ብስ...
26/04/2026

ዶ/ር ማሙሻ 11 ሚሊየን ብር ለቤተ ክርስቲያን ሰጠ

ዶ/ር ማሙሻ ለኢትዮጵያ ሕይወት ብርሐን አጥቢያ 11 ሚሊየን ብር ለአገልግሎት ማእከል ግንባታ ከመጽሐፉ የተገኘዉን ገቢ ሰጠ!

“መንፈሳዊ ብስለት” ከተሰኘው መጽሐፍ የተገኘዉን 11 ሚሊዮን ብር ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ ላለፉት 25 ዓመታት በመሪነት ላገለገሏት በኢትዮዽያ ሕይወት ብርሃን ቤተ ክርስቲያን አዲስ ክርስቲያን ላይፍ አሰምብሊ አጥቢያ የአገልግሎት ማእከል ግንባታ በልግስና ሰጥቶል።

ትላንት ምሽት ቤተ ክርስቲያኒቱ ባዘጋጀችው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ዶ/ር ማሙሻ ቼኩን ሲያስረክቡ እንደገለጹት መጽሐፉ ለቤተክርስቲያን እንደተሰጠ ያወቁ ምመናን በብዙ ልግስና ከዋጋው በላይ በብዛት በመግዛታቸው ይህ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል። በዚሁም እነኚህን (የገዙትን) አማኞችና የራሳቸውን ቤተሰብ አመስግነዋል።

አሁንም መጽሐፉ በአገር ውስጥና በውጭ እየተሰራጨ በመሆኑ ከዚህ በኋላም የሚገኝ የሽያጭ ገቢ ለቤተ ክርስቲያን በቀጣይ ዙር እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ

የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://youtube.com/
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ 0991827226 ላይ ያገኙናል

የሚድያ ህግ እና የወንጌል አደራ፡ ለክርስቲያን የሚድያ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠየወንጌላውያን የሚድያ ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ክርስቲያን የህግ ባለሙያዎች (ECLF) ጋር በመተባበር "የ...
25/04/2026

የሚድያ ህግ እና የወንጌል አደራ፡ ለክርስቲያን የሚድያ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ

የወንጌላውያን የሚድያ ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ክርስቲያን የህግ ባለሙያዎች (ECLF) ጋር በመተባበር "የሚድያ ህግ መብትና ግዴታ" ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዶ ሆቴል አካሄደ።

በዚህ ስልጠና ላይ ከተለያዩ ክርስቲያን ሚድያዎች የተወጣጡ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል። ስልጠናው በዋናነት ያተኮረው የሚድያ ህጎችን ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር በመገንዘብ፣ የክርስቲያን ሚድያ ባለሙያዎች የተሰጣቸውን የወንጌል አደራ በኃላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ነው።

የህግ እውቀትና ኃላፊነት፡ የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ እስክንድር ገዛህኝ፣ የሚድያ ህጎችንና መብቶችን በውል ማወቅ ለትውልድ የሚጠቅም ስራ ለመስራት እና ወንጌልን በተሰጠ ማንነት በኃላፊነት ለማድረስ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ፡ የኢትዮጵያ ክርስቲያን የህግ ባለሙያዎች (ECLF) ዳይሬክተር አቶ ኒቆዲሞስ ጌታሁን እንደገለጹት፣ ስልጠናው በሀገሪቱ ጸንተው የቆዩትን የሚድያ ህጎች ከእግዚአብሔር ቃል ጋር በማጣጣም ባለሙያዎች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል የተዘጋጀ ነው።

ቀጣይነት ያለው ስራ፡ የወንጌላውያን የሚድያ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዘሪሁን ግርማ፣ በስራ ላይ የሚከሰቱ የሚድያ ህግ ክፍተቶችን ለመቀነስ ይህ ስልጠና ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ለሌሎችም የክርስቲያን ሚድያ ባለሙያዎች ስልጠናው እንደሚዳረስ አረጋግጠዋል።
ስልጠናውን የወሰዱ ባለሙያዎች መድረኩ እጅግ ጠቃሚ እንደነበር ገልጸዋል። እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች የክርስቲያን ሚድያ ዘርፉን በህግና በመንፈሳዊ መርሆዎች እንዲመራ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል።
ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ

የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://youtube.com/
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ 0991827226 ላይ ያገኙናል

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የ100ኛ አመት በዓል  ዝግጅትን አስመልክቶ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራሮች የተገኙበት ግብረ ሃይሎችን የማቋቋም መርሃግብር በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክ...
25/04/2026

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የ100ኛ አመት በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራሮች የተገኙበት ግብረ ሃይሎችን የማቋቋም መርሃግብር በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጽሕፈት ቤት ዛሬ ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሂዷል።

በስፍራውም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቃላይ ጸሐፊ ፓስተር ጌትነት ለማ(ዶ/ር) እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ

የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://youtube.com/
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ 0991827226 ላይ ያገኙናል

ታላቁ የቤተ ክርስቲያን አባትና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቄስ ጉዲና ቱምሳ መታሰቢያ በትውልድ ቀያቸውሃውልት ቆመላቸው። በምዕራብ ወለጋ፣ ቦጂ ወረዳ ቢላ ከተማ በ1929 ዓ.ም የተወለዱት ቄስ ጉ...
25/04/2026

ታላቁ የቤተ ክርስቲያን አባትና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቄስ ጉዲና ቱምሳ መታሰቢያ በትውልድ ቀያቸው
ሃውልት ቆመላቸው።

በምዕራብ ወለጋ፣ ቦጂ ወረዳ ቢላ ከተማ በ1929 ዓ.ም የተወለዱት ቄስ ጉዲና ቱምሳ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጠቅላይ ጸሃፊ በመሆን ቤተ ክርስቲያኒቱን በሊቀነትና በስነ-መለኮት ያገለገሉ፣ በሰብአዊ መብት ጥበቃም የማይረሳ አሻራ ያኖሩ የቤተ ክርስቲያን መሪ ነበሩ።

አሁን በተወለዱበት የቢላ ከተማ የተመረቀው ይህ መታሰቢያ ሃውልት፣ የትውልዱን ትውስታ የሚጠብቅ ብቻ ሳይሆን፣ ስለ እውነት መቆምን የሚያስተምር ነው።

በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የጉዲና ቱምሳ ፋውንዴሽን መሪ እና የቄስ ጉዲና ልጅ ወ/ሮ ሌንሳ ጉዲና እንዳሉት፦
“ይህ ሃውልት ለትውልዱ፣ ስላለፈው በእውነት፣ ስለ ወደፊቱ ደግሞ በብርታት፣ በፍርሃት ፊት ስለ እምነት ይናገራል” ብለዋል።

የሃውልቱ ምረቃ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ አባ ገዳዎች፣ የተከበሩ እንግዶች እና የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ

በኦቦሌሳ አዶላ - GTF እንዳስነበበው

የጎዳና ላይ  የወንጌል  ስርጭት እና የስርዓተ አምልኮ  ይዞታ  አጠቃቀም  ላይ  ውይይት ተካሄደ።የኢትዮጵያ ወንጌል  አማኞች አብያተክርስቲያናት  ካውንስል  ስራ አስፈጻሚ  ኮሚቴ  ከአዲስ ...
24/04/2026

የጎዳና ላይ የወንጌል ስርጭት እና የስርዓተ አምልኮ ይዞታ አጠቃቀም ላይ ውይይት ተካሄደ።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመቀናጀት ባዘጋጀው መድረክ በጎዳና ላይ የወንጌል ስርጭት እና የስርዓተ አምልኮ ማስፈጸሚያ ይዞታ አጠቃቀም ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል ።
የመፍትሄ አቅጣጫዎችም ተቀምጧል ።

"እኔ በሰውነቴ ከማንም አልበልጥም፣ አላንስም እርስዎስ?!"ይህ ጥያቄ ለሰላም ግንባታ ያለን የጋራ ቁርጠኝነት እና ለሰው ልጅ ክብር ያለንን እሴት የሚፈትን ነው። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒ...
23/04/2026

"እኔ በሰውነቴ ከማንም አልበልጥም፣ አላንስም እርስዎስ?!"
ይህ ጥያቄ ለሰላም ግንባታ ያለን የጋራ ቁርጠኝነት እና ለሰው ልጅ ክብር ያለንን እሴት የሚፈትን ነው።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ያለመ ሀገራዊ የምክክር መድረክ በስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ ከተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
🔹 የአብሮነት እሴት፦ የወል ትርክትን በመገንባት፣ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር እና የጋራ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ መፍጠር።
🔹 የሃይማኖት ተቋማት ሚና፦ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ የሃይማኖት ተቋማት ከመንፈሳዊ ትምህርት ባሻገር ለማህበራዊ ክብር መሰረት በመሆናቸው፣ ግጭትና አለመግባባቶችን ለመፍታት ያላቸው ሚና የጎላ ነው። በመሆኑም ለሰላም ግንባታ ሂደቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
🔹 የጋራ ንቅናቄ፦ ሕገ-መንግስታዊ ቃል ኪዳኖችን በተግባር በመተርጎም፣ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ባለድርሻ አካላት በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተመላክቷል።
በመድረኩ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተው ስለ ሰላም ግንባታ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
ሰላም የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት ነው፤ አብረን እንስራ!
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ ምዕራፍ ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን ነጋዴዎችየኢትዮጵያ ወንጌላውያን ነጋዴዎች ኔትወርክ (EBN Ethiopia) በንግድና በማህበረሰብ ልማት ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በ...
23/04/2026

አዲስ ምዕራፍ ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን ነጋዴዎች

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ነጋዴዎች ኔትወርክ (EBN Ethiopia) በንግድና በማህበረሰብ ልማት ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በይፋ መጀመሩን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።
ኔትወርኩ ካስጀመራቸው ቁልፍ ፕሮግራሞች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል:-
የአጥቢያ ቤተክርስቲያናት ድጋፍ እና አገልግሎት
ይህ ፕሮግራም በሁሉም የወንጌል አማኝ አብያተክርስቲያናት የሚተገበር ሲሆን፤ በመጀመሪያው ዙር ከ15 አጥቢያ አብያተክርስቲያናት የተወጡ 30 አስተባባሪዎች (Facilitators) ስልጠና ወስደዋል። እነዚህ የሰለጠኑ ባለሙያዎች በቀጣይ 300 የሚያህሉ ነጋዴዎችንና ባለሙያዎችን በማደራጀት በዘርፉ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ።
በእለቱም “Marketplace Miracles” የተሰኘ የገበያ ስፍራ ተአምራቶች መፅሀፍ ተመርቋል የGlobal Advance Inc. ፕሬዝዳንት Jonathan Shibley የጻፉትንና በአሜሪካ የሚገኙ ክርስቲያን ስራ ፈጣሪዎች በማህበረሰባቸው ውስጥ ያሳዩትን ተጽዕኖ የሚዳስሰው “Marketplace Miracles” መጽሐፍ የመጀመሪያ የአማርኛ ትርጉም በይፋ ተመርቋል።
ኔትወርኩ በቀጣይ ዙሮች ተጨማሪ አብያተክርስቲያናትን ወደ ፕሮግራሙ በማስገባትና አሰልጣኞችን በማብቃት ተልዕኮውን አጠናክሮ ይቀጥላል።
ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ

በጋብቻ እና በቤተሰብ መፍረስ ዙሪያ የተካሄደ ወሳኝ አውደ ጥናትተምናሴር ዓለም አቀፍ ወንጌል ለቤተሰብ ሚኒስትሪ፤ በጋብቻ የፍቺ መበራከት በልጆች፣ በባለትዳሮች፣ በቤተክርስቲያን እና በሀገር ...
22/04/2026

በጋብቻ እና በቤተሰብ መፍረስ ዙሪያ የተካሄደ ወሳኝ አውደ ጥናት

ተምናሴር ዓለም አቀፍ ወንጌል ለቤተሰብ ሚኒስትሪ፤ በጋብቻ የፍቺ መበራከት በልጆች፣ በባለትዳሮች፣ በቤተክርስቲያን እና በሀገር ደረጃ ያስከተለውን ቀውስ በመመርመር የጥናታዊ ግኝት ሪፖርት አቀረበ።

በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዘደንት ቄስ ደረጀ ጀንበሩ፣

የኢፌድሪ የሴቶች፣ የህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአረጋውያንና የቤተሰብ ጉዳይ መሪ አቶ ተስፋዬ ሮበሌ፣
እንዲሁም የአብያተክርስቲያናት መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአውደ ጥናቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡ባለፉት ሶስት ወራት የተደረገ ጥናታዊ ግኝት ለታዳሚዎች በዝርዝር ቀርቧል።

የፍቺ መንስኤዎች እንዲሁም ከፍቺ በኋላ የሚከሰቱ ማህበራዊ፣ ስነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ተዳሰዋል።

በዶ/ር ንጉሴ ተፈራ፣ በመጋቢ ሰንበቶ በሼና እና በወ/ሮ ረቂቅ (በወጣቶችና ዩንቨርስቲ ተማሪዎች አገልግሎት ዙሪያ) ጥናቱን መሠረት ያደረጉ ሀሳቦች ቀርበዋል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት አቶ ተስፋዬ ሮበሌ እንደገለጹት፤ ቤተሰብ በህገመንግስቱ የተደነገገ በመሆኑ፣ ጋብቻ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንዳይጋለጥ ተቋማቸው የተጠናከረ ስራ እየሰራ ይገኛል።

ተምናሴር ዓለም አቀፍ ወንጌል ለቤተሰብ ሚኒስትሪ በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ካውንስል ተባባሪ አባል በመሆን በቤተሰብ ጉዳይ ላይ እያገለገለ የሚገኝ ድርጅት ነው።
ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
ዘገባው በሰለሞን ተክለፃድቅ

Address

Bole
Addis Ababa
32753

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Evangelical MEDIA/Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Evangelical MEDIA/Council:

Share