26/06/2026
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶክተር ጌትነት ለማ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ባደረጉት ጉብኝት ተቋሙ የደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ እጅግ አስደናቂ መሆኑን ገለጹ።
ጠቅላይ ጸሐፊው በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ ወደ ተቋሙ የመጡት ልምድ ለመውሰድና ሙያ ለመቅሰም ቢሆንም፣ በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ስራዎች ግን የሚበረታቱ ሆነው አግኝተዋቸዋል። በዕለቱ በነበራቸው ቆይታ በግብርና እና በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መመልከታቸውንም አብራርተዋል።
ካውንስሉ በቴክኖሎጂ ታግዞ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማቅለል ማቀዱን የገለጹት ፓስተር ዶክተር ጌትነት፣ "ከካውንስል አንጻር ብዙ ሥራዎችን እንጠብቃለን" ብለዋል። ወደፊት ማገልገል የሚገባቸውን ሥራዎች ከተቋሙ ባለሙያዎች ጋር በመነጋገርና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም፣ በካውንስሉ አገልግሎት የምወሰዱ ዜጎች በቀላሉ መስተናገድ የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና:-ቤተልሔም ደረጀ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/
• TikTok: https://www.tiktok.com/.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
ስልክ+251 991827226 ላይ ያገኙናል