ዝማሬ አርያም

ዝማሬ አርያም መዝሙረ ዳዊት 13:6 የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ለል መዝሙረ ዳዊት 13:6 የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ።

24/05/2026

ዓብይ መንፈሳዊ ጉባኤ //ከደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ

✨     ✨✨🙏🏾 እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም   የልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ   የእመቤታችንን ፍቅሯን በልባችኝ  ጣዕሟን በአንደበታችን ያኑርልን ✨🙏🏾      ...
08/05/2026

✨ ✨

✨🙏🏾 እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
የልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ
የእመቤታችንን ፍቅሯን በልባችኝ
ጣዕሟን በአንደበታችን ያኑርልን ✨🙏🏾

+ + + + +
+ ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፡
ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤
አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡ ✨ ኢሳ 11፡1 ✨

💫 ቁጥሩ ከዐበይት ነቢያት ወገን የሆነው ነቢዩ #ኢሳይያስም ጥበብንና እውቀትን በሚገልጽ ስለሚመጣውም ነገር ትንቢትን በሚያናግር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት “
/ በትር_ትወጣለች ፤ / ›› በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡

✨ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን፡፡ ይህንን መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ‹‹ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ›› በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡

✨ ‹‹በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ (መዝ 131፡13)›› የተባለልን የአባቶቻችን ልጆች እኛም እንዲሁ እያልን እናመሰግናታለን፡፡ ✨

✨✨✨✨✨✨✨✨
የሐና የኢያቄም የእምነታቸው ፍሬ
🌺 በእግዚአብሔር ፈቃድ ተወለደች ዛሬ🌺

የኢያቄም ስዕለቱ የሐና እምነት 👏🏾
ለምኝልን ለኛ ኪዳነ ምሕረት 👏🏾

✨ + + + + + ✨




✨ አማኑኤል የማይተረጎም የሥጋን ልብስነት
ከአንቺ የለበሳት መሥሪያ ነሽ።
ዝሐውን ከአዳም ጥንተ ሥጋ አደረገ ማጉም የአንቺ ሥጋ ነው። መወርወሪያውም ቃል እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

✨ መሕኑም ከልዕልና የወረደ
የልዑል እግዚአብሔር አምሳል ነው።
ሠሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው።

✨ ወዮ ይህ ነገር እጹብ ድንቅ ነው።
የቀደሙ አባቶች ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገሩብሽ ድልድይ ሆይ ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርሺ መሰላል ሆይ የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ በአንቺ ታደሰ ።

🙏🏽ከገነት #በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ።
/ ቅዳሴ ማርያም ቁ.29 - 31/

✨🙏🏾 እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
የልደት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ
የእመቤታችንን ፍቅሯን በልባችኝ
ጣዕሟን በአንደበታችን ያኑርልን ✨🙏🏾

ሚያዚያ 30🤲 ቅዱስ ማርቆስ ይጠብቀን 🤲ቅዱስ ማርቆስ  (በአለ እረፍቱ)    በአለ ንግሱ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በ    መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ወቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ       ል...
07/05/2026

ሚያዚያ 30🤲 ቅዱስ ማርቆስ ይጠብቀን 🤲

ቅዱስ ማርቆስ
(በአለ እረፍቱ)

በአለ ንግሱ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በ

መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ወቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ

ልዩ ስም፦ጉለሌ /ክ/ከ 6ኪሎ

ይከበራል።

🤲 ቅዱስ ማርቆስ ይጠብቀን 🤲

.     .         ቅዱስ አማኑኤል አባቴ ❤️ . .    🌺💒❤️👏👏ቅዱስ አማኑኤል በያለንበት ከክፉ ነገር ሁሉ ይታደገን ::
05/05/2026

. . ቅዱስ አማኑኤል አባቴ ❤️

.

.



🌺💒❤️👏👏

ቅዱስ አማኑኤል በያለንበት ከክፉ ነገር ሁሉ ይታደገን ::

✝️    #ከክፉ  #ነገር  #ሁሉ     ✝️🤍
04/05/2026

✝️ #ከክፉ #ነገር #ሁሉ ✝️🤍

የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
03/05/2026

የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏

🐎🛡️  #መርቆሬዎስ፦  !   🛡️🐎የችግሬ ደራሽ፣ በፀሊም (ጥቁር) ፈረስህ ተጭነህ የምትመጣው   ሆይ! እንባዬን ልታብስ፣ ከጭንቀቴም ልታሳርፈኝ ፈጥነህ ድረስ። ስምህን ስጠራ ትካዜዬ ይርቃል...
02/05/2026

🐎🛡️ #መርቆሬዎስ፦ !
🛡️🐎

የችግሬ ደራሽ፣ በፀሊም (ጥቁር) ፈረስህ ተጭነህ የምትመጣው ሆይ! እንባዬን ልታብስ፣ ከጭንቀቴም ልታሳርፈኝ ፈጥነህ ድረስ። ስምህን ስጠራ ትካዜዬ ይርቃል፣ ቤቴም በረድኤትህ ይሞላል። 🌟✨

✨ ፦

ቅዱስ መርቆሬዎስ በወጣትነት ዕድሜው የጦር አዛዥና ኃያል ተዋጊ ቢሆንም፣ የክርስቶስ ፍቅር ግን ከምድራዊ ሥልጣኑ በላይ በለጠበት። ዛሬም እኛ ወጣቶች በጉልበታችንና በዕውቀታችን ስንመካ፣ እውነተኛው ኃይል ከፈጣሪ የሚገኝ መሆኑን ከመርቆሬዎስ ሕይወት እንማራለን። ⚔️💎

✨ ፦

ባስልዮስና ጎርጎርዮስ በለመኑት ጊዜ ከሥዕሉ ተለይቶ በፈረስ በመዝለል ጠላትን ድል የነሳ ተአምረኛ ነው። አረማዊው ዑልያኖስ ተገድሎ ሃይማኖት እንድትስፋፋ ያደረገ ኃያል ሰማዕት እርሱ ነው። ዛሬም በሕይወታችን የሚነሱ "ዑልያኖሶችን" (ክፉ ፈተናዎችን) በሰይፍህ ቁረጥልን። 🛡️🔥

✨ ፦

"አብን የሚወድ" የተባልክ ጀግና ነህ። በጋለ ሹል ብረት ብትወጋም፣ በዳኪዮስ ፊት ብትሰቃይም እምነትህን አልካድክም። ወጣትነትህን ለክርስቶስ መሥዋዕት አድርገህ አቀረብክ። 👑✨

✨ ፦

አንተን ለማጥፋት የመጡት ገጸ ከላባቱ እንኳ ባሕርያቸውን ቀይረው፣ ለአንተና ለአምላክህ ለመገዛት ከእግርህ ሥር አደሩ። 🐾➡️🙏 ይህ ለአንተ የተሰጠህ ድንቅ የጸጋ ግርማ ነው።

✨ ፦

በፀሊም ፈረስህ እየገሰገስክ፣ "መርቆሬዎስ ወዳጄ" ብለን ስንጠራህ የምትደርስልን አማላጃችን ነህ። መርቆሬዎስ ካለኝ መከራና ችግርን አልፈራም፤ እርሱ የነፍሴ ጠባቂ ነውና። 🌪️🐎

🕯️ 🕯️

"ኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ! በወጣትነቴ ዘመን በፈተና እንዳልወድቅ በሁለቱ ሰይፎችህ ጠብቀኝ። የቂሳርያ እስር ቤት በአንተ ብርሃን እንደበራ፣ የእኔንም የጨለመ ሕይወት በረድኤትህ አብራልኝ።" 🤲🌹

"መርቆሬዎስ ወዳጄ ስጠራው ደረሰ፤
በፀሊም ፈረሱ እየገሰገሰ!" 🌈🐎

"የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል።" 📖 (መዝሙረ ዳዊት ፵፬፥፲፱)

#አሜን 🙏 #አሜን 🙏 #አሜን 🙏

የአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት እና ምልጃ አይለየን🙏በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴ...
01/05/2026

የአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት እና ምልጃ አይለየን🙏

በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡

አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡

ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብራል፡፡

ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡

የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

👉ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቴ አንተው ጠብቀን🙏       👉የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት እና❤            👉በረከቱ ይደርብን አሜን 🙏               👉እንኳን አደረሳችሁ 🌷🌷         ...
30/04/2026

👉ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቴ አንተው ጠብቀን🙏
👉የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት እና❤
👉በረከቱ ይደርብን አሜን 🙏
👉እንኳን አደረሳችሁ 🌷🌷
👉አደረሰን❤🙏❤🙏

⚖️ ቅዱስ ኡራኤል፡ ከክፉ ነገር ሁሉ ብክንፉ ጋርዶ ይስጥልን🙏🙏🙏     #አሜን✝️✝️✝️
29/04/2026

⚖️ ቅዱስ ኡራኤል፡ ከክፉ ነገር ሁሉ ብክንፉ ጋርዶ ይስጥልን🙏🙏🙏
#አሜን✝️✝️✝️

Address

4 Kilo
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዝማሬ አርያም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share