19/05/2026
የተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች
የጌታ ጸጋ ይብዛላችሁ
የኢትዮጽያ የትንቢት ቃል የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የጀሞ አጥቢያ ለአንድ ወር የሚቆይ ከጌታ በተቀበለችው ምሪት ለአንድ ወር የሚቆይ አማኞች በቃሉና በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ከልብ ወይም ከውስጣዊ ህመም ተፈውሰው ጤናማና የታደሰ ህይወትና አገልግሎት እንዲኖራቸው የሚያግዝ አዲስ ምዕራፍ የተሰኘ ልዩ ኮንፍራንስ አርብ ግነቦት 7 መጀመሯ ይታወቃል።
ይህ ኮንፍራንስ ማክሰኞ ከ10:00 ጀምሮ፣አርብ ከ10:00 እሁድ ጠዋት ከ4:00 ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቀጥል መሆኑን አውቃችሁ
1.በመገኘት ይህን የጌታን ጸጋና ወቅታዊውን መልእክት እንድትካፈሉ
2.ጌታን ለማያውቁ ሰዎችና በልዩ ልዩ ችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን በመጋበዝ ለደህንነታቸውና ለመፈወሳቸው ምክንያት እንድትሆኑ
3.ቤተክርስቲያን አገልግሎቷን በድል ማጠናቀቅ እንዲያስችላት የጸሎት ድጋፍ እንድታደርጉን በጌታ ፍቅር እየጠየቅን
በሁሉ ስለምታገለግሉ ደግሞም ስለምትገለገሉ ጌታ ከጸባኦት ይባርካችሁ እንላለን።
በመሪዎችና በጌታ ውክልና
መጋቢ ደረሰ