30/05/2026
RHAPSODY OF REALITIES
(Amharic) 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
Saturday 30, May 2026
ቅዳሜ፣ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም.
📜 ስኬት፣ ድል እና ጭማሪ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
📖 “በፈሳሽ ውኃ ዳር እንደ ተተከለች [እንደተንከባከቧት]፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ወይም እንደማይጠወልግ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል [ወደ ሙሉ ብስለትም ይደርሳል]።” (መዝሙር 1:3 በአምፕሊፋይድ ትርጉም )።
👤 ፓስተር ክሪስ
════════
እግዚአብሔር ውድቀትን ፈጽሞ አይፈጥርም። አንድ ሰው ከክርስቶስ ጋር ሲቀላቀል፣ ለስኬት፣ ለድል እና ለጭማሪ ብቻ ተብሎ ወደተዘጋጀ ሕይወት ይገባል። በእናንተ ውስጥ ያለው የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ብቃትን፣ እድገትን እና ታላቅነትን ያመጣል። ይህ የአዲሱ ፍጥረት ሕይወት እውነታ ነው።
እኔ ወደዚህ ግንዛቤ የገባሁት በጣም ቀደም ብዬ ነው። ዘጠኝ ዓመት ሳይሞላኝ ነው ዳግም የተወለድኩት፣ ብዙም ሳይቆይ ወንጌልን መስበክ ጀመርኩ። ጓደኞቼን ወደ ክርስቶስ መማረክ ጀመርኩ፤ ከአሥር ዓመቴ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣ ኅብረት ጀመርኩ። በአሥራ አምስት ዓመቴ ቀድሞውኑ ትላልቅ የወንጌል ስርጭቶችን አከናውን ነበር። ይህንን መንገድ ለረጅም ጊዜ ስለድሄኩበት፣ ያለ ምንም ጥርጥር ቃሉ እንደሚሠራ ለማወቅ ችያለሁ።
እግዚአብሔር በመንገዱን ሲያሳችሁና አእምሯችሁ በእርሱ ላይ ሲጸና፣ በእርሱ ስለታመናችሁ ፍጹም ሰላም እንደሚጠብቃችሁ ቃሉ ያውጃል። ያ ሰላም የብልጽግና ሰላም ነው፣ ይህም ያለማቋረጥ ወደፊት የሚገሰግስ ሕይወት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በክርስቶስ ስላለው ሰው ሲናገርም፦ “የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል” ይላል።
በቃሉ የሚኖር ሰው ዕጣ ፈንታው ይህ ነው፤ በመክፈቻ ጥቅሳችን ላይ እንዳየነው። የክፉዎችን ምክር የማይከተል ሰው የተባረከ ነው። አንዳንዶች አምላክ የሌላቸው ጓደኞች፣ ዘመዶች ወይም ጎረቤቶች ውሳኔዎቻቸውን እንዲቀርጹ ይፈቅዳሉ፤ በፍጹም ይህ መሆን የለበትም!
የተባረከ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ደስ ይለዋል፣ ቀንም ሌሊትም ያሰላስለዋል። ለቃሉ ትኩረት ይሰጣል፣ በቃሉም ሕይወቱን ይቀርጸዋል። ውጤቱም አስደናቂ ነው፦ በውኃ ፈሳሾች አጠገብ እንደተተከለች፣ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፣ ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ይሆናል፤ ይህ ማለት በእናንተ ዘንድ ውድቀት የለም ማለት ነው። ምን ዓይነት ሕይወት ነው!
ራሳችሁን ለቃሉ ስትሰጡ፣ ሕይወት ወደላይ እና ወደፊት ብቻ ለሚደረግ የአንድ አቅጣጫ ጉዞ ያዘጋጃችኋል ። ቃሉ ዘር ነው፣ ማሰላሰል ደግሞ ቃሉ ስኬትን፣ ድልን እና ክብርን ብቻ እንድታስቡ አእምሯችሁን እንዲገዛ በመንፈሳችሁ ውስጥ ስር እንዲሰድ ያደርገዋል። ሕይወታችሁ የቃሉ መገለጫ ይሆናል፣ ይህም መልካም ስኬት እንዲኖራችሁ ያደርጋል (ኢያሱ 1:8)። ሃሌሉያ።
ጸሎት
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ውድ አባት ሆይ፣ በክርስቶስ ስለሰጠኸኝ የማያልቅ የስኬት ሕይወት አመሰግንሃለሁ። ቃልህ በእኔ ውስጥ በኃይል ይሠራል፣ ብቃትን፣ ብልጽግናን እና ድልን ያመጣል፤ ስኬትን በስኬት ላይ እደረርባለሁ። በየቀኑ ቃልህን አስማለሁ፣ ቃልህን እናገራለሁ፣ እንዲሁም በቃሉ ብርሃን እመላለሳለሁ፤ በኢየሱስ ስም። አሜን።
ለተጨማሪ ጥናት
├─ኢያሱ 1:8 3
├─ዮሐንስ 1:2
├─ምሳሌ 4:20-22
━━━━//━━━