24/07/2026
💫RHAPSODY OF REALITIES 💫
(Amharic) 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
Friday 24, July 2026
አርብ፥ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
📜ለስኬት በቃሉ የታነጻችሁ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
📖 “በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።”(ኢሳይያስ 26፡3)
👤 ፓስተር ክሪስ
════════
ገና በለጋነቴ፣ ጌታ እየጨመረ ለሚሄድ ስኬትና ተጽዕኖ መንገዴን አቅንቶታል። ገና በልጅነቴ ነው ከቃሉ ጋር የተዋወቁት ለዚህም ደግሞ ጌታን ለዘለአለም አመሰግነዋለሁ። ዳግም የተወለድኩት ገና ዘጠኝ አመት ሳይሞላኝ ነበር፤ ከዚያ ወንጌልን መስበክ ስጀምር ብዙም አልቆየሁም። ጓደኞቼን ለክርስቶስ መማረክ ጀመርኩ፣ ወዲያውም ህብረት ማድረግ ጀመርኩ። በአስራ አምስት አመቴ፣ የወንጌል ዘመቻ እያደረኩ ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጉዞዬ ከክብር ላይ ክብር ነው።
ቃሉ እንደሚናገረው እግዚአብሔር በመንገድ ሲመራችሁና በእርሱ ላይ ስትታመኑ በእርሱ ላይ ተደግፋችኋልና ፈጽሞ በሰላም ይጠብቃችኋል። ያ ሰላም የብልጽግና ሰላም ነው፤ ያለማቋረጥ ወደ ፊት የሚሄድ ህይወት ነው።
መዝሙር 1፡3 ይህንን ህይወት በግልጽ ያብራራዋል፥”እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።” ቃሉ ህይወታችሁን እንዲቀርጸው ትኩረት ስትሰጡ፣ የሚሆነው እንዲህ ነው። ውጤቱ አስደናቂ ነው። እናንተ በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደተተከለች፣ ፍሬዋንም በጊዜዋ እንደምትሰጥ ዛፍ ናችሁ። በህወታችሁ ውድቀት የለም።
የአምፕሊፋይድ ትርጉም ኢያሱ 1፡8ን የሚያብራራበት መንገድ ደስ ይለኛል፥”ይህ የሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ ነገር ግን የተጻፈውን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አሰላስልበት፤ የዚያን ጊዜ መንገድህ ይቃናልሃል፥ ከዚያም በጥበብ ትሠራለህ፥ መልካምም ትሆናለህ።" ለቃሉ እራሳችሁን ስትሰጡ፣ በጥበብ ታደርጋላችሁ ይከናወንላችሁማል።
ምን አይነት ህይወት ነው፤ ለስኬት ብቻ የተሰራ ህይወት። ይህ ቃሉን የማሰላሰል ውጤት ነው፤ ቃሉ ራሱን በእናንተ ውስጥ ያበዛል። የእግዚአብሔር ቃል ዘር ነው። ማሰላሰል ቃሉ በመንፈሳችሁ ስር እንዲሰድና ሃሳባችሁን በመቆጣጠር ቃሉን ብቻ እንድታወሩና በቃሉ እንድትመላለሱ ያደርጋችኋል። ህይወታችሁ የቃሉ መገለጫ ይሆናል። ሃሌሉያ!
🙏 ጸሎት
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ውድ አባት ሆይ፣ ቃልህ በህይወቴ ላይ ስላለው ኃይልና ውጤት አመሰግናለሁ። በአንተ እደገፋለሁ በፍጹም ሰላምና በማያቋርጥብልጽግና እመላለሳለሁ። ራሴን ሙሉ ለሙሉ ለቃልህ እሰጣለሁ፣ በቀንም በሌሊትም አሰላስላለሁ፣ የማያቋርጥ ስኬትና ፍሬያማነት በእኔ ይፈጥራል። ህይወቴ የቃልህ ነጸብራቅ ነው፤ ሁል ጊዜ በድል እመላለሳለሁ፣ በኢየሱስ ስም። አሜን።
📖 ለተጨማሪ ጥናት
├─ቆላስይስ 3፡16
├─ዕብራውያን 4፡12
├─ያዕቆብ 1፡22
━━━━//━━━