Kidist Arsema maheber

Kidist Arsema maheber aresema ye guzo ena menefesawi mehaber

27/10/2022

የሐዋ ፯÷፶፰-፷
🧚🍀ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ።
59 እስጢፋኖስም። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር።
ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።🧚ከቀዳሚ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆን ቅዱስ እስጢፈኖስ ረድኤት በረከት ያሳትፈን♥🙏🙏

Ye tewahedo enat ebet kidist dingel mariam 💚💛❤ Orthodox☦️
01/10/2022

Ye tewahedo enat ebet kidist dingel mariam 💚💛❤ Orthodox☦️

✝️💚💛❤ Orthodox☦️
01/10/2022

✝️💚💛❤ Orthodox☦️

እንኳን ለሰማእቷ ቅድስት አርሴማ  በአል አደረሳችሁእናታችን ቅድስተ አርሴማ ሆይ በተሰጠሽ ቃል ኪዳን እኛ ልጆችሽን ጠብቂንቅድስት አርሴማ ማለት በወርቅ ልብሶች የተጎናጸፋችናየተሽለመች፤መልከመ...
15/03/2022

እንኳን ለሰማእቷ ቅድስት አርሴማ በአል አደረሳችሁ
እናታችን ቅድስተ አርሴማ ሆይ በተሰጠሽ ቃል ኪዳን እኛ ልጆችሽን ጠብቂን
ቅድስት አርሴማ ማለት በወርቅ ልብሶች የተጎናጸፋችና
የተሽለመች፤መልከመልካምና ውብ ማለት ነው።
እንኔም መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ
መስቀሌን ተሽክሞ ይከተለኝ ፤... ስው አለሙን
ሁሉ ቢገዛ ነፍሱንም ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?
ተብሎ የተነገረው የክርስቶስ ወንጌል ተከትላ
ዘመድ አዝማዳቿን ትታ ጌታን የተከተለች
በሮምና በአርማንያ ገዥዎች የነበሩ ሁለት
ከህዲያን ነገሥታት ዲዮቅልጥያኖስንና
ዲርጣድስን በሃይማኖቷ ጸንታ ድል ያደረግች
የሮም ወታደሮች የሚያደርሱባትን መከራና
ግፍ እስራትና ግርፈት ያልበገራት መላ
ሕይወታቸውን ለእሳትና ለስለት ከስጡት
ከ27ቱ ቅዱሳት ደናግል አንዷ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ናት።
ብፅዕት ቅድስት እመቤቴ አርሴማ ሆይ!
እነሆ የሕይወቴ መርከብ እልሻለሁ ።
ነፍሴን ከእሳት ባህር የምታሻግሪያት አንቺ ነሽና።
እመቤቴ ቅድስት አርሴማ ሆይ ክብርት ነሽ
በረከቷ በሁላችን ህይወት ይደርብን አሜን🙏

🕊† እንኳን ለጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †† አቡነ ገብረ ሕይወት ...
13/03/2022

🕊

† እንኳን ለጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† አቡነ ገብረ ሕይወት †

† ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ [ንሒሳ አካባቢ] ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ: የቅዱሳን የበላይ: ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው::

የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አንደበት ይኖራል?
- እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል?
- ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን?

አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ ፭፻፷፪ [562] ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ :-
- እህል ያልቀመሱ [ምግባቸው ምስጋና ነውና]
- ልብስ ያልለበሱ [ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና]
- ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት::
- ሃገራችንን አስምረው: አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል::

ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም : ገብረ ሕይወትም ይባላሉ:: በ፭፻፷፪ [562] ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል:: በዚህም በሚሊየን [አእላፍ] ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል::

ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል:: እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል:: ለየት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው:: ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና::

የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮዽያ ልዩ ፍቅር አላቸው:: ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ ፻ [100] ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል:: ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው::

ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ፳፻ [2,000] በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት:: በ8ኛው ክ/ዘመን አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው:: ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት ፭ [5] ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል::

ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ::
"ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ::
ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ::
ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ::
ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ::
ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ::" እንዲል::

† የጻድቁ በዓል ጥቅምት ፭ [5] ቀን የሚከበረው ብዙ ጊዜ መጋቢት ፭ [5] ዐቢይ ጾም ውስጥ ስለሚውል ተውላጥ [ቅያሪ] ሆኖ ነው::

† ቸር አምላክ ከጻድቁ ዋጋና በረከት ይክፈለን::

🕊

† መጋቢት ፭ [5] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

፩. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ [አባ ገብረ ሕይወት]
፪. ቅዱስ አባ ሰረባሞን [በምድረ ግብፅ ምንኩስናን ካስፋፉ ታላላቅ ቅዱሳን አንዱ]
፫. አባ ግርማኖስ ጻድቅ [ሶርያዊ]
፬. ቅድስት አውዶክስያ ሰማዕት [ከከፋ የኃጢአት ሕይወት ተመልሳ ለቅድስና የበቃች እናት]
፭. ቅዱሳን ስምዖንና ሚስቱ አቅሌስያ [የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወላጆች]

† ወርሐዊ በዓላት

፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፬. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

† "ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል:: ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላቹሃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም::" † [ማቴ.፲፥፵፩] (10:41)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

🕊 💖 🕊

ድንግል ማርያም እና ሔዋንክርስቶስ ከድንግል ማርያም ወጣ፣ አዳም ከምድር እንደ ወጣ፡አዳም በእግዚአብሔር መንፈስ እስትንፋስ -በእርሱም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት - እና ክርስቶስ በመ...
23/02/2022

ድንግል ማርያም እና ሔዋን

ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ወጣ፣ አዳም ከምድር እንደ ወጣ፡አዳም በእግዚአብሔር መንፈስ እስትንፋስ -በእርሱም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት - እና ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ መምጣት - መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል - ስለ ድንግል ማርያም ተባለ። እንዲሁ ክርስቶስ እንደ አዳም ምሳሌ ወጣ (ዘፍ 2፡7፤ ሉቃ. 1፡35)።
ነገር ግን ክርስቶስ ደግሞ ሄዋንን መስሎ ወጣ፡ እንዲሁ ሔዋን ያለ እናት ከአባት ወጣች ("ከጎድን አጥንት")፣ ስለዚህም ክርስቶስ ያለ አባት ከእናት ወጣ ("ባል አታውቅም")። ፊተኛው አዳም ያለ ሴት ተሳትፎ ከሔዋን እንዳስገኘ ሁሉ ማርያምም ያለ ወንድ ተሳትፎ ክርስቶስን ወለደች። ሔዋን በወንድ "ዘር" ብቻ ታየች, እና ክርስቶስ የተገለጠው በሴት "ዘር" ብቻ ነው. ሔዋን እና ክርስቶስ የተገኙበት መንገዶች አንድ ናቸው፡ሁለቱም ከአንድ ጾታ በእግዚአብሔር ኃይል የሰውን ተፈጥሮ ተቀበሉ። በመጀመሪያ ሴቲቱ (ሔዋን) ከወንድ አደረገች, ከዚያም ወንዱ (ክርስቶስ) ከሴት አደረገ. ስለዚህም ክርስቶስ የመጀመርያውን አዳምን ​​፣የሰውን ሁሉ ተፈጥሮ ወይም መላውን አዳምን ​​ከማርያም ተቀብሏል ፣ይህን የአዳምን ባሕርይ የሰጠው። ስለዚህም አዳም ስለሔዋን እንደተናገረው ስለ ማርያም እና በእሷም በኩል ስለ ክርስቶስ፡- ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት ሥጋም ከሥጋዬ ናት። በድንግል ማርያም በኩል ተፈጥሮአችን በክርስቶስ ዳግማዊ አዳም አለ (ዘፍ 2፡21፣23፤ ሉቃ.1፡34)።
ክርስቶስ ሁለተኛ አዳም እንደሆነ ሁሉ ማርያምም ሁለተኛዋ ሔዋን ናት። ይህም የሔዋንን ፈተና ከነገረ ማርያም ጋር በማነጻጸር ግልጽ ነው።
ከዚያም የወደቀ መልአክ፣ እባቡ፣ ዲያብሎስ ተገለጠ። የቅዱስ ገብርኤል መልአክ መገለጥ እዚህ አለ። ዘፍጥረት 3:1 (ራእ. 20:2) ሉቃ 1:26
ፊተኛይቱ ለሔዋን፣ በሰውዋ እንደ አምላክ እንደምትሆን፣ እናንተም እንደ አማልክት ትሆናላችሁ የሚል ተስፋ ሰጠች። ሁለተኛው ማርያም አምላክ በእሷ በኩል ሰው እንደሚሆን ቃል ገብቷል—የልዑል ልጅ ይባላል ... የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። አማኑኤል ሲተረጎም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ዘፍጥረት 3:4—ሉቃስ 1:32, 35፤ ማቴ. 1፡23።
በሔዋን በኩል - ውድቀት; በማርያም - መዳን. ሔዋን ስትታለል እና እንደ አምላክ መሆን ስትመኝ፣ አምላክ አልኾነችም።አሁን እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ሰው በእውነት መለኮት ይሆን ዘንድ ነው፡ ከሁሉ አስቀድሞ ማርያም በሰው ዘር ሁሉ የመጀመሪያ ሆና በመጣባት። ሴት በመጀመሪያ የወደቀች እና የመጀመሪያዋ የዳነች ነበረች።
ሔዋን በእግዚአብሔር ትእዛዛት የማታምን፣ እግዚአብሔርን ያላመነች እና በራሷ ተጨባጭ እውቀት ሟርትን ለመቀበል የምትመኝ ሆና ታየች። ማርያም እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ ታመነች; በዚህ እምነት እውቀትን ናቀች (ወንድ አላውቀውም አንዱንም ማወቅ አስፈላጊ አልነበረም) እና፡ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች። ያን ጊዜ ለእርስዋ [ሔዋን] ውድቀት ሆነ፤ በጥርጣሬና ባለማመንም ሰዎች ሁሉ ላይ። እነሆ መዳን ለእርስዋ [ለማርያም] እና በእምነት ለሰው ሁሉ አሉ። ዘፍጥረት 3:6— ሉቃስ 1:34, 37, 45 ።
ሔዋን ለእግዚአብሔርና ለትእዛዙ አለመታዘዝን አሳይታለች-ከእሱ (ከዛፉ) አትብላ... ከፍሬው ወስዳ በላች። ማርያም በዘመነ ብስራት ያለ ጥርጥር ለእግዚአብሔር ፈቃድ ታዛለች እና እንዲህ አለች፡- እነሆ የጌታ ባሪያ። ዘፍጥረት 2:17፣ 3:6— ሉቃስ 1:38 ።
ሔዋን በሃሳቧ ትኮራለች—እንደ አምላክ ትሆናላችሁ። ማርያም ትሑት የሆነች የጌታ ባሪያ ነበረች፣ በእግዚአብሔር በእሷ በሥጋ የመጣባትን የምስራች በተቀበለች ጊዜ፣ እና ደግሞ ከዚህ ክስተት በፊትም ቢሆን፣ በዚህም ምክንያት የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቷል፣ እናም ይህ በትክክል ነበር። በዚህ የነፍሷ ባሕርይ ትኩረቱን ወደ እርስዋ ስላዞረ እና ለእሱ እናት ልትሆን እንደሚገባት ስላደረጋት። ያን ጊዜ በትዕቢት ሔዋን አምላክ መሆንን ፈለገች፣ እናም አሁን በትህትና ማርያም እግዚአብሔርን በራሷ ውስጥ ለመቀበል እና ስለ እኛ መዳን ስትል ሰብአዊ ተፈጥሮን ልትሰጠው እንደሚገባ ተቆጥራለች። ዘፍጥረት 3:4—ሉቃስ 1:48
ሔዋን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተነፈገች እና ወደ ሕይወት ዛፍ እንድትቀርብ አልተፈቀደላትም። ማርያም በራሷ የእግዚአብሔርን ልጅ ተቀበለች, የዘላለም ሕይወት; ጸጋን አገኘች, እግዚአብሔር; ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ፣ ሰላምታ ተቀበለች። ጌታ ከአንተ ጋር ነው፣ እርስዋም እንደ ቃሉ ፀነሰች፡ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል።...
በእነዚህ የመጀመሪያ እና በጣም አስፈላጊ ምሳሌዎች እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን እንደሚቃወም፣ ለትሑታን ግን ጸጋን እንደሚሰጥ እናያለን። ዘፍጥረት 3:24—ሉቃስ 1:28, 30, 35፤ ያእቆብ 4:6
ስለ ኃጢአትዋ ሄዋን ለመከራና ለመውለድ ተሰጥታለች; ማርያም ባል እንደሌላት እና ኃጢአት እንዳልሠራች, ያለ ሥቃይ ወንድ ልጅ ወለደች.
ነገር ግን ሔዋን በሕይወት ዛፍ ፍሬ ጣፋጭነት ስለ ተታለለች፣ የማርያምን ነፍስ ሰይፍ የወጋባት፣ ልጇን በመስቀሉ ላይ ባየች ጊዜ። ክርስቶስ የሔዋንን ኃጢአት ዋጀ። ሔዋን የተፈጠረችበት የጎድን አጥንት በሁለተኛው አዳም የተወጋ ሲሆን የመጀመርያው ኃጢአት ማስተሰረያ እና መንጻት ምልክት ሆኖ ከዚያ ደምና ውሃ ፈሰሰ። ነገር ግን ወደ ልጇ መስቀል ማርያም ኃጢአት የለሽ፣ ቤዛ የሆነችውን የሞራል ስቃይና ስለ ሔዋን ኃጢአት መከራን አመጣባት፣ ምክንያቱም ልጇ ወደ መስቀሉ ያረገው በሔዋን ኃጢአት ምክንያት ነው። ማርያም በሔዋን ምክንያት እና የሔዋን ኃጢአት በታጠበበት በመስቀል ላይ መከራ ተቀበለች። ሉቃስ 2:35; ዮሐንስ 19፡34
ክርስቶስ ሁለተኛ አዳም ከሆነ፣ ማርያም በእውነት ሁለተኛዋ ሔዋን እንደሆነች እና ሔዋን ረዳት ሆና ከተፈጠረች፣ ለአዳም የተገናኘችና የምትመስል (ዘፍ. 2፡18, 20)፣ ማርያምም በሁሉም ባሕርያቷ እንደ ሆነ እናያለን። የሁለተኛው አዳም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ “ረዳት፣ ተገናኘን እና መስደድ” ሆኖ ታየ እናም የሁለተኛው አዳም ታላቅነት ወሰን እስካልሆነ ድረስ የሁለተኛይቱ ሔዋን ታላቅነት ቅዱስና ከፍ ያለ ነው ለዚህም የተገባ ነው። አዳም.
ከወንዶች መካከል ከእርስዋ ጋር የሚወዳደር ማንም የለም። በታሪክ መጀመሪያ እና መሃል ላይ ሔዋን እና ማርያም የተባሉ ሁለት ሴቶች ቆመው ነበር። ሔዋን የወደቀው እና ኃጢአተኛ የሰው ልጅ እናት ነች። ማርያም እየዳነ ያለው የአዲስ፣ ዳግም የተወለደ የሰው ልጅ እናት ነች። በመጀመሪያ ዓለም አቀፋዊ የክፋት መንስኤ ነበር; በሁለተኛው ውስጥ, ሁለንተናዊ መልካም ምክንያት.


†✝† እንኳን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት...
01/02/2022

†✝† እንኳን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ †††

††† ልደት †††

††† መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን
የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው::
እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ
እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::

በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ
ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ
አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን
መወለድ አብስሯቸዋል::

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24 ቀን
በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታኅሣሥ 24 ቀን
በ1207 ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት
ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::

††† ዕድገት †††

የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል::
ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው
አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት:
ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ
እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ጳጳስ አባ ጌርሎስ
ተቀብለዋል::

††† መጠራት †††

አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት
ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት
በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::

የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ
ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን::
ከዚህ በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር
ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላ ሰዓትን አላጠፉም::
ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው
እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

††† አገልግሎት †††

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከጳጳሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው
ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን
አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮጵያ 2 መልክ ነበራት::

1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች
ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን
ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::
2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ
ተነቃቅቶ ነበር::

ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ
አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ
መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን:
መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቋዮችን) አጥፍተዋል::

††† ገዳማዊ ሕይወት †††

††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮጵያን
ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል::
እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት
አገልግለዋል::

እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል::

በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ
(ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት
ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን
በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::

††† ስድስት ክንፍ †††

ኢትዮጵያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት
ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ
መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

ከወቅቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው
ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ
ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም
ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::

ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት
የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
*በቤተ መቅደስ ብስራቱን
*በቤተ ልሔም ልደቱን
*በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
*በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
*በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ
ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት
ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና
ዓይናቸው ጠፋ::

በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል
ማርያም ፈጥና ደርሳ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ወደ ሰማይ
አሳረገቻቸው::

††† በዚያም:-
*የብርሃን ዐይን ተቀብለው
*6 ክንፍ አብቅለው
*የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
*ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
*ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
*ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
*"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

††† ተአምራት †††

የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት
የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ
ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን
ታሥሯልና::

††† ዕረፍት †††

††† ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው: መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን
አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው
ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል
ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10
ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

††† በዚህ ዕለት አባታችን ተክለ ሃይማኖት ለ22 ዓመታት
የቆሙበት ቀኝ እግራቸው መሠበሩንና በአንድ እግራቸው
ለ7 ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
ታስባለች::

††† ጥር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅድስት ማርያ ግብጻዊት
3.ታላቁ አባ ቢፋ
4.አባ አብሳዲ ቀሲስ
5.ቅዱሳን ጻድቃነ ሐውዚን

††† ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ ዘዮሐንስ (ዘክብራን ገብርኤል-ጣና)
2.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ
3.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ
4.ቅዱስ ሙሴ ጸሊም
5.ቅዱስ አጋቢጦስ
6.ሃያ አራቱ ካህናተ ሠማይ

††† "በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር :
አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት :
ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ
ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . .
የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው::" †††
(፪ቆሮ ፲፩፥፳፫)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

🕊   እንኳን ለእመቤታችን ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።   🕊† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †🕊†...
28/01/2022

🕊


እንኳን ለእመቤታችን ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

🕊

† ዕረፍተ ድንግል †

† እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር::

ዓለም ተፈጥሮ : አዳምና ሔዋን ስተው: መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው: በኃዘን ንስሃ ቢገቡ "እትወለድ እም ወለተ ወለትከ - ከ5 ቀን ተኩል (5500 ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ ንጽሕት ዘር ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው::

ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው: ነቢያትና ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ እጅ ነሷት::
"እምርሑቅሰ ርእይዋ: ወተአምኅዋ" እንዲል::

† የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ

✞ ከአዳም በሴት
✞ ከያሬድ በሔኖክ
✞ ከኖኅ በሴም
✞ ከአብርሃም በይስሐቅ
✞ ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ
✞ ከይሁዳ በእሴይ : በዳዊት : በሰሎሞንና በሕዝቅያስ ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች::

✞ ከሌዊ ደግሞ በአሮን : አልዓዛር : ፊንሐስ : ቴክታና በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች::

🕊

አባታችን አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት ወላዲተ አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት: ኃጢአት ሳያገኛት: ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ ኢያቄም ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7) "ወኢረኩሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ" እንዳለ:: (ቅዱስ ቴዎዶጦስ ዘዕንቆራ)

ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ ቤተ መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12 ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና እያገለገለች: እርሷን ደግሞ መላእክተ ብርሃን እያገለገሏት: ሕብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ አረጋዊ ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት::

በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው:: ነደ እሳትን ተሸከመችው: ቻለችው:: "ጾርኪ ዘኢይትጸወር: ወአግመርኪ ዘኢይትገመር" እንዳለ:: (ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ለብሐዊ)

*ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ: እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14) "ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በገሊላ ለ2 ዓመታት ቆዩ::

አርዌ ሔሮድስ እገድላለሁ ብሎ በተነሳበት ወቅትም ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም: በላበትና በድካም: በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር ሲሆነው: ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ::

በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን እያሳደገች: ነዳያንን እያሰበች ኑራለች:: እርሷ 45 ዓመት ልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት: ተአምራት ጀመረ:: ለ3 ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች: ካደረበትም እያደረች ትምሕርቱን ሰማች::

የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች:: ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች::

ከልጇ ዕርገት በሁዋላ በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትን ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮንም ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች:: በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ: ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና: ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች::

ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን መድኃኒታችን አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት ባልተደረገ: ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ: ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል::

"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ::
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ::" እንዲል::

ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ: ሐዋርያቱም እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ: በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው ወሰዱ:: ይሕንን ሊቃውንት:-
"ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ::
እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ:: ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል::

በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ ቅዱስ ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ: እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል:: በዚያም መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት ቆይታለች::

ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል ማርያምን ንጹሕ ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም በጌቴሴማኒ ቀብረዋታል::

በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ::

ለ2 ሳምንታት ቆይተው: ሁሉንም ወደ ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ የማይነገር ተድላ: ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ ደብረ ዘይት ተመልሰዋል::

🕊

††† ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን: ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: †††

[ከዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ገጽ የቀረበ]

╭══•: |❀:✧๑♡๑✧:❀| :•══╮

🕊"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።               🕊   ጥር ፲ [ 10 ] ቀን   🕊እንኳን ለገሀድ [ ጋድ ] ጾመ ፣ ለከተራ በሰላም አደረሰን።      ...
17/01/2022

🕊

"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

🕊 ጥር ፲ [ 10 ] ቀን 🕊

እንኳን ለገሀድ [ ጋድ ] ጾመ ፣ ለከተራ በሰላም አደረሰን።



በዚች ዕለት ምንም ምን መብልን ሰይቀምሱ ምእመናን ሁሉ እስከ ምሽት ይጾሙ ዘንድ ከእኛ አስቀድመው የነበሩ ታላላቅ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓትን ሠሩ። በምሽትም ቢሆን በታላቁ ጾም ከሚበላው በቀር ጥሉላትን እንዳይቀምሱ።

በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንዲጾሙ ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው ፦ የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን [የበዓሉ ዕለት] በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።

እኛ በዚህ በኅላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን።

የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ ዕለተ ማክሰኞንና ዕለተ ሐሙስን ምትክ አድርገን እንድንጾማቸው ይገባልና። በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው። እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው።

በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው። በዋዜማው ዓርብ እስከ ምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ። የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾም ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን [የፍስክ ምግቦችን] ከመብላት ይጠበቁ።

በጥምቀትም ዕለት ከእኵለ ሌሊት በፊት ተነሥተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ። ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቊርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙ።

ስለዚህም የዘንድሮ ጾመ ገሐድ ፣

በዓለ ጥምቀት ረቡዕ የዋለ ስለሆነ ጾመ ገሃድ ነገ ማክሰኞ ጥር ፲ [10] ቀን ይሆናል።

እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮርዳኖስም ወንዝ እንደ ተገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው።

ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና ከቸር አባቱ ጋር ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።

የሥላሴ ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁንና፦ጥር 7 እና ሐምሌ 7 የቅድስት ሥላሴ ክብረ ኃይለ መለኮትን የምንዘክርበት እናለዓለሙ ሁሉ ደንነትን ቸርነትን ዕድገትን ሰላምና ጤናን የምንማጸንበት ታላቅ...
15/01/2022

የሥላሴ ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁንና፦
ጥር 7 እና ሐምሌ 7 የቅድስት ሥላሴ ክብረ ኃይለ መለኮትን የምንዘክርበት እና
ለዓለሙ ሁሉ ደንነትን ቸርነትን ዕድገትን ሰላምና ጤናን የምንማጸንበት ታላቅና በልዩ የሚታሰቡበት በዓለ ሥሉስ ቅዱስ
ናቸዉ። ይክበሩ ይመስገኑ ለዘላለም ።
አሜን አሜን አሜን ። ተ ተ ተ

ከጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ያገኘነው ምንድን ነው?ዳግም ልደትበአዳም በደል ምክንያት አጥተነው የነበረው ልጅነታችንን ክርስቶስ በልደቱ ዳግመኛ እንደመለሰልን ነባቤ መለኮት ...
07/01/2022

ከጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ያገኘነው ምንድን ነው?

ዳግም ልደት
በአዳም በደል ምክንያት አጥተነው የነበረው ልጅነታችንን ክርስቶስ በልደቱ ዳግመኛ እንደመለሰልን ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው።” ዮሐ 1፥12 በማለት ገልጾታል።

ሰላም
በጌታችን ልደት ለዓለም ሁሉ የሚሆን ዘላለማዊ ሰላም ተገኝቷል። ይህም “ክብር እግዚአብሔር በሰማያት ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጐ ፈቃድ” እያሉ ቅዱሳን መላእክት በመዘመራቸው ተረጋግጧል። ሉቃ 2፥14። ስለዚህ በክርስቶስ ያገኘነው እውነተኛ ሰላም በእኛ ጸንቶ እንዲኖር ዘወትር በጾምና በጸሎት እየተጋን ስለሰላም የምንማፀን ሆነን ልንገኝ ይገባል። ሰላም የክርስትና መታወቂያ አርማ ነውና።

ብርሃን
“በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃንን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።” ኢሳ 9፥2። ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ያህል በዲያብሎስ ቁራኝነት ተይዞ የነበረው አዳም ወደሚደነቀው ብርሃን የተሸጋገረው በክርስቶስ ልደት ነው። እኛም በልደቱ ያገኘነውን የጽድቅ ብርሃን ጠብቀን ለመኖር (ብርሃነ ወንጌልን) ፈጽመን ከኃጢአት ርቀን በጽድቅ ሥራ ተወስነን ብርሃን ሆነን ልንኖር ይገባል።

ነጻነት
“በነጻነት እንኖር ዘንድ ክርስቶስ ነጻ አወጣን። ከእንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደገና በባርነት ቀንበር አትያዙ”። ገላ 5፥1። የሰው ልጅ እግዚአብሔርን በነጻነት እያመሰገነ ይኖር ዘንድ ተፈጥሯልና። ኃጢአት በመሥራት የዲያብሎስ ባርያ ሳንሆን በተሰጠን ነጻነት በመጠቀም የጽድቅ አገልጋዮች ሆነን ልንመላለስ ይገባል።

ይቅርታ
በአዳም በደል ምክንያት ከአብራኩ የተከፈሉ በሙሉ በደለኛ ሆነው የነበሩበትን ዘመን ለውጦ አዳምንና የልጅ ልጆቹን በደል ደምስሶ ፍቅርን ይመሰርት ዘንድ ጌታ ተወለደ። በምድርና በሰማይ ላሉት ፍቅርን መሠረተ። እርሱ የሰው ልጆችን በደል ሳይቆጥር ሁሉን ይቅር እንዳለ ክርስቲያንም የበደሉትን ሁሉ ይቅር ይል ዘንድ የፈጣሪው ትዕዛዝ ነውና ዘወትር ሊፈጽማት የምትገባ ከእግዚአብሔር ጸጋ የምታስደምር የልደቱን ብርሃን ለማየት እንደበቁ በዚህም ደስ እንደተሰኙ እንደ ቅዱሳን መላእክት ለእውነተኛ ምስጋና የምታደርስ የጽድቅ መሠረት የበረከት በር ናት። ማቴ 18፥21-23፣ ማቴ 5፥23-25። መባህን ትተህ ሂድ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ የሚለው አምላካዊ ቃል ይቅርታ የክርስትና ሕይወት መመሪያ መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልንፈጽማት ይገባል።

ፍቅር
ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተናገረው እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጅን በደል ሳይቆጥር በዙፋኑ ሆኖ ምሬሃለሁ ማለት ሲችል ፍቅሩን ይገለጽ ዘንድ በከብቶች በረት ተወለደ። እውነተኛ ፍቅሩ ለክርስትናችን መሠረት ለጽድቃችን ፋና እንደሆነ መጻሕፍት ያረጋግጣሉ።

እንግዲህ በልደቱ ያገኘነውን ሰላም፣ ነጻነት፣ ይቅርታ፣ ብርሃንና ፍቅር ዋጋ የተከፈለበት ጸጋ የወረስንበት በመሆኑ ዘወትር በድንቅ ፍቅሩ የሚታደገን አምላካችን እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ እስከ መጨረሻው ድረስ ጸንተን እንድንኖር ክብራችንንና ጸጋችንን አስተውለን ከኃጢአት ርቀን በንሰሐ ታጥበን እራሳችንን ለክርስቶስ የተወደደ መስዋዕት አድርገን እንድናቀርብ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት አይለየን።
#ጌራራ

Address

Bole Bulbula
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kidist Arsema maheber posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Kidist Arsema maheber:

Share

Category