Meserete Kristos Church - Head Office

Meserete Kristos Church - Head Office Meserete Kristos Church (MKC) is established in 1951 to proclaim the Good News of the Lord Jesus Chri

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሰሜን አዲስ አበባ አጥቢያ መዘምራን https://youtu.be/xohfi62Qxps?si=YE7UH1J62i0Wpr5c
20/05/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሰሜን አዲስ አበባ አጥቢያ መዘምራን

https://youtu.be/xohfi62Qxps?si=YE7UH1J62i0Wpr5c

በዚህ መዝሙር ውስጥ የምናገኘው ዋናው መልዕክት፤ እግዚአብሔርን በዜማና በቃል ከማመስገን ባለፈ፣ በዕለት ተዕለት ኑሯችንና በባህሪያችን እርሱን መግለጥ እንደሚገባን ነው። ቃላቶቻች.....

  🎼https://youtu.be/Q-CLAB2axPk?si=Xm6mCIpcAtN0XKul
19/05/2026

🎼

https://youtu.be/Q-CLAB2axPk?si=Xm6mCIpcAtN0XKul

እንኳን ወደ ካራ መሰረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን "ሀ" መዘምራን ዩቲዩብ ቻናል በደህና መጡ። በአስደናቂ የፕሮቴስታንት መዝሙሮች ልንባርካችሁ እዚህ መጥተናል። “እግዚአብሔርን በመተ.....

የ2018 ዓ.ም የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የተማሪዎች ምርቃት ፕሮግራም  #በምስል
18/05/2026

የ2018 ዓ.ም የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የተማሪዎች ምርቃት ፕሮግራም #በምስል

የመሠረተ ክርስቶስ  #ሴሚናሪ ተማሪዎቹን አስመረቀ የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በድግሪ መርሐግብር ለአራት አመታት ያስተማራቸውን 38 ተማሪዎች በዛሬው እለት በቢሾፍቱ አስመርቋል።በምረቃ ፕሮግራ...
16/05/2026

የመሠረተ ክርስቶስ #ሴሚናሪ ተማሪዎቹን አስመረቀ

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በድግሪ መርሐግብር ለአራት አመታት ያስተማራቸውን 38 ተማሪዎች በዛሬው እለት በቢሾፍቱ አስመርቋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀመንበር ዶ/ር ሰይፈ ወዳጅ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ሲያስተላልፉ የዘንድሮው ምረቃ በቅርቡ 100 ተማሪዎችን በማስተርስ ፕሮግራም ባስመረቅንና ከACTEA ሙሉ እውቅና ባገኘን ማግስት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸው በመጨረሻም ለተመራቂዎች ስነመለኮት መማር ትልቅ ኃላፊነት ሲሉ ከእግዚአብሔርና ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን አደራ በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ ፕሪንሲፓል መጋቢ ጊሹ ጀቤቻ ሴሚናሪው ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባስቀመጠው ስልታዊ እቅድ ቤተ ክርስቲያን የነደፈችውን የአጀንዳ 2819 የወንጌል ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ ከዘንድሮው 38 ምሩቃን መካከል 17ቱ በሴሚናሪው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሽንና ኢንተርካልቸራል (Mission and Intercultural Studies) ፕሮግራም መመረቃቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም ፕሪንሲፓሉ ሴሚናሪው በቅርቡ ከመላው ሀገሪቱ የመጡ 166 ሚሲዮናውያንን ማሰልጠኑን አስታውሰው በገቢ ራሱን ለመቻልም ባለ አምስት ወለል ሁለገብ ሕንፃ ለመገንባት ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

በምረቃ መርሐግብሩ ዝማሬ የቀረበ ሲሆን መምህር አለሙ ሽመሎ ከማቴዎስ 14፥22-32 "ኢየሱስን እያዩ ወደ ፊት መጓዝ" በሚል ርዕስ "በችግርና ማዕበል ውስጥ ከሁኔታው በላይ ሆነን መጓዝ የምንችለው ኢየሱስን ስናይ ነው!" በማለት ከእግዚአብሔር ቃል መልዕክት አስተላልፈዋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአሁን ሰዓት በሀገሪቱ በሚገኙ 30 ካምፓሶቹ 1300 ተማሪዎችን በድግሪና ማስተርስ መርሐግብር በማስተማር ላይ ይገኛል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   በዛሬው እለት አስቸኳይ ስብሰባ አካሂዷል። የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባውን በዛሬው እለት ሲያካሂድ በተለያዩ የቤ...
15/05/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በዛሬው እለት አስቸኳይ ስብሰባ አካሂዷል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባውን በዛሬው እለት ሲያካሂድ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቷል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰብረላ ከድር በመሩት ስብሰባ በዋናው ቢሮ የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በስብሰባው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን 75ኛ አመት ክብረበዓል ዝግጅት፣ የ2019 በጀት አመት እቅድ እንዲሁም በቀጣይ በተለያዩ ክልሎች ስለሚካሄዱ ጠቅላላ ጉባኤዎች ውይይት በማድረግ ውሳኔዎች ተላልፈዋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

የመሠረተ ክርስቶስ  #ሴሚናሪ ግንቦት 8 ተማሪዎቹን  #እንደሚያስመርቅ ገለጸ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ ባለፉት አራት አመታት በድግሪ መርሐግብር ያስተማራ...
13/05/2026

የመሠረተ ክርስቶስ #ሴሚናሪ ግንቦት 8 ተማሪዎቹን #እንደሚያስመርቅ ገለጸ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ ባለፉት አራት አመታት በድግሪ መርሐግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎቹን የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 8/2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ካምፓስ እንደሚያስመርቅ ገልጿል።

የዘንድሮው ተመራቂዎች በተለይ ሴሚናሪው ባስቀመጠው የአምስት አመት ስልታዊ እቅድ መሠረት በጀመራችው Mission and Intercultural study እንዲሁም Biblical and Theological study በተሰኙ ሁለት አዳዲስ ፕሮግራሞቹ ያሰለጠናቸው መሆኑን ታውቋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአፍሪካ ለሚገኙ የስነመለኮት ተቋማት እውቅና ከሚሰጠው Association for Christian Theological Education in Africa (ACTEA) ባለፈው አመት ሙሉ እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

 "ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ። አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና። ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን...
10/05/2026



"ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ። አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና። ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፥ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤ እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሸክም ሊሸከም ነውና።" ገላትያ 6፥2-5

ሙሉውን ትምህርት ከታች ያለውን መስፈንጠሪያ ተጭነው ይከታተሉ 👇

https://youtu.be/CTD43DFHtSQ?si=4M-PyONsj5wP5jbB

☎️ +251 967 555511ቴሌግራም፡ ኮሚኒኬሽን አገልግሎታችን ጋር በተገናኘ ያልዎትን ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል አልያም በጽሑፍ መልዕክት.....

" " በሚል ርዕስ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ክፍል ሁለት መጽሐፍ ታትሞ መቅረቡ ተገለጸ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ከዚህ በፊት ቤተ ክ...
08/05/2026

" " በሚል ርዕስ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው ክፍል ሁለት መጽሐፍ ታትሞ መቅረቡ ተገለጸ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ከዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያናችን የድነት አስተምህሮ ወጥነትን ለማስጠበቅና አዳዲስ አማኞችን በተገቢ ሁኔታ በማስተማር ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ ለማስቻል "ክርስቶስን መከተል" በሚል ርዕስ መጽሐፍ በማዘጋጀት ለረዥም አመታት እየተጠቀመች መቆየቷን አስታውሶ አሁን ደግሞ የዚህ መጽሐፍ ክፍል ሁለት ተዘጋጅቶ ለስርጭት መቅረቡን አሳውቋል።

"ክርስቶስን መከተል" በመጀመሪያው መጽሐፍ ላይ ያልተካተቱና ለክርስትና ህይወት አስፈላጊ የሆኑ ስድስት ዋና ዋና ርዕሶችን በውስጡ ይዟል።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ምዕመኖቿ ወጥነትን በተከተለ መንገድ እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሆነው እንዲያድጉ በማሰብ እነዚህን መጽሐፍት በቀጣና፣ ክልሎችና አጥቢያዎቿ ጥቅም ላይ እንዲውል አዘጋጅታለች።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

በመሠረተ ክርስቶስ  #ሴሚነሪ ለአራት ሳምንታት ሲሰጥ የቆየው  #የሚሲዮሎጂ ስልጠና ተጠናቀቀ። የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተወጣጡ 166 ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲ...
07/05/2026

በመሠረተ ክርስቶስ #ሴሚነሪ ለአራት ሳምንታት ሲሰጥ የቆየው #የሚሲዮሎጂ ስልጠና ተጠናቀቀ።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተወጣጡ 166 ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲዮናውያንና ወንጌላውያን ለአራት ሳምንታት በሚሲዮሎጂ (Missiological) ትምህርት ዘርፍ በመጀመሪያ ዙር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል።

በስልጠናው ማጠናቀቂያና ምረቃ መርሐግብር ላይ የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ለተመራቂዎቹ የባርኮት ጸሎት አድርገዋል።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን 75ኛ አመት ክብረበዓል ዋዜማ ላይ የተመረቁት እነዚህ ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲዮናውያን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከዛሬ ሰባ አምስት አመት በፊት በአደራ የተቀበለችውን የወንጌል ዘር በመላው ሀገሪቱ እንደሚያስቀጥሉ ይጠበቃል።

ሴሚነሪው ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲዮናውያንን ውጤታማ ደቀ መዝሙር የማድረግና አውዳዊ በሆኑ የቤተ ክርስቲያን ተከላ ስልጠናዎች የማስታጠቅ ተግባሩን በቀጣይ ዙሮችም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የ75ኛ አመት ክብረበዓልን አስመልክቶ የተሰጠውን ሙሉ መግለጫ ከታች የተቀመጠውን መስፈንጠሪያ ተጭነው ይመልከቱ 👇https://youtu.be/yxqCrxUf9m...
06/05/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የ75ኛ አመት ክብረበዓልን አስመልክቶ የተሰጠውን ሙሉ መግለጫ ከታች የተቀመጠውን መስፈንጠሪያ ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/yxqCrxUf9mw?si=I-KiIix0JzyUjB6I

መሰረተ ክርስቶስ አንጋፋ ከሚባሉት ቤተክርስቲያናት አንዷ ነች፣ በርካታ ቤተ እምነቶችን የተከሉ አገልጋዮችንም አበርክታለች፣ በቅርቡም በደመቀ ሁኔታ 75ኛ አመት ልደቷን ለማክበር ተዘ.....

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን  #75ኛ አመት የምስረታ ክብረበዓል " " በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ተገለጸ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን 75ኛ አመት ክብረበዓልን አስመልክቶ በዛሬ...
04/05/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን #75ኛ አመት የምስረታ ክብረበዓል " " በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ተገለጸ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን 75ኛ አመት ክብረበዓልን አስመልክቶ በዛሬው እለት የተለያዩ መንፈሳዊ ሚዲያዎች በተገኙበት በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ አዳራሽ መግለጫ ተሰጥቷል።

በመግለጫው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ እንኳን ለ75ኛ አመት የምስረታ ክብረበዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት ቤተ ክርስቲያኒቱ እስራትና ሞት ሳይበግራት በመከራ ውስጥ ማደጓን ገልጸው በቅርብ አመታትም ወንጌል አጀንዳችን ነው በማለት የወንጌል ንቅናቄ በመፍጠር ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል።

በቀደሙ አባቶችና በአሁኑ ትውልድ መካከል ቅብብሎሽን ለመፍጠር መከባበርና መቀባበልን ባህል እናደርጋለን በሚል መሪ ሃሳብ በየአመቱ የመሠረተ ክርስቶስ ቀን እየተከበረ መቆየቱን አስታውሰው በዚህ አመትም የ75ኛ አመት ክብረበዓሉ ከግንቦት 30_ሰኔ 7/2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ መከበር እንደሚጀምርና በቀጣይም በልዩ ልዩ መንፈሳዊና ሰብአዊ አገልግሎቶች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ የመሠረተ ክርስቶስ ቀጣናዎች፣ ክልሎችና አጥቢያዎች እየተከበረ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የሰሜን አዳማ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መጋቢ እና የ75ኛ አመት ክብረበዓል አዘጋጅ ኮሚቴ አባል የሆኑት መጋቢ እውነቱ ነስጋ በበኩላቸው ቤተ ክርስቲያናችን ከጥቂት ተነስታ ዛሬ ለደረሰችበት ደረጃ መብቃት የቻለችው በእግዚአብሔር እርዳታ መሆኑን በማስታወስ እርሱን አመስግነዋል።

ክብረበዓሉ "በአደራ የተሰጠች ዘር" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች መከበሩ ከሀገር ውጪ የመጡት ሚሲዮናውያን በአደራ የሰጡንን የወንጌል ዘር ለማስታወስ እንደሆነ ሲገልጹ መዝሙር 145፥4 ለክብረበዓሉ እንደ መነሻ ጥቅስ ሆኖ መመረጡን በመናገር ዝግጅቱ እግዚአብሔርን ማመስገን፣ የወንጌል አደራን ጠብቀው ላቆዩ አባቶች እውቅ መስጠት፣ እርስ በእርስ መተያየትና ህብረታችንን ማደስ እንዲሁም በሚመጡት ዘመናት ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮዋን በብቃት መወጣት እንድትችል የድርሻችንን ለመወጣት ቃል መግባትን አላማው እንዳደረገ ተናግረዋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስር ተጠማቂ አባላትን በመያዝ ሰኔ 9 ቀን 1943 ዓ.ም መመስረቷ ይታወሳል።

"ትውልደ ትውልድ ሥራህን #ያመሰግናሉ፥ ኃይልህንም #ያወራሉ።" መዝሙር 145፥4

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

Address

Africa Avenue Near Destiny Addis Hotel
Addis Ababa
24227

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251115506136

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Meserete Kristos Church - Head Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Meserete Kristos Church - Head Office:

Share

Category