Meserete Kristos Church - Head Office

Meserete Kristos Church - Head Office Meserete Kristos Church (MKC) is established in 1951 to proclaim the Good News of the Lord Jesus Chri

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ  #የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርት ቀረበ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ መምሪያዎች የ2018 በጀት አመት የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርታ...
22/06/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ #የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርት ቀረበ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ መምሪያዎች የ2018 በጀት አመት የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርታቸውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት በተገኙበት በዛሬው እለት አቀርበዋል።

ከሪፖርቱ አስቀድሞ በቀጣይ ወራት በሚካሄዱ የክልል ጠቅላላ ጉባኤዎች ላይ የሚቀርበውና 2ኛ ጴጥሮስ ምዕራፍ 1፥1-11'ን መሠረት በማድረግ "ጤናማ መንፈሳዊ ህይወት" በሚል ርዕስ በትምህርት ክፍል የተዘጋጀው ትምህርት በመምህር ሰለሞን ግዛቸው ቀርቧል፡።

በአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርት ባለፉት ሦስት ወራት የተገኙ ፍሬዎች በዝርዝር ለጉባኤው በመምሪያ ዳይሬክተሮቹ በኩል የቀረበ ሲሆን ከጉባኤው ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም ጉባኤው ስለተገኙት ፍሬዎችና እግዚአብሔር ስለሰጠን መከናወን እርሱን በማመስገን ስብሰባውን በጸሎት አጠናቋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

ደቀ መዛሙርትን ማብዛት በሚል ርዕስ ሀገር አቀፍ   በአዲስአበባ ተካሄደ።በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ የሀገር አቀፍ የእህቶች አገልግሎት ዴስክ ከቲዲኤምኤም...
22/06/2026

ደቀ መዛሙርትን ማብዛት በሚል ርዕስ ሀገር አቀፍ በአዲስአበባ ተካሄደ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ የሀገር አቀፍ የእህቶች አገልግሎት ዴስክ ከቲዲኤምኤም ሚኒስትሪ ጋር በመተባበር በሳል ሴት ደቀ መዝሙርትን ማብዛት በሚል ርዕስ ከሰኔ 11-13/2018 ዓ.ም በአዲስአበባ ስልጠና አካሂዷል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ተመስገን መንገሻ በስፍራው ተገኝተው ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ሲያስተላልፉ ከዮሐንስ 15፥8 መነሻ በማድረግ ተሳታፊዎች የወሰዱትን ስልጠና ወደ ክልላቸው በማውረድ ፍሬ እንዲያፈሩ እና ያመኑትን ደቀ መዛሙርት እንዲያደርጉ አሳስበዋል። ዳይሬክተሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን አምስቱን ዓላማዎች ለጉባኤው ሲያብራሩ በመጨረሻም በቤተ ክርስቲያን ስም TDMM እና አጋሮቻቸውን አመስግነዋል።

በስልጠናው ላይ ሴት መሪዎችና የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች፥ የክልል ተወካዮች፥ ሴት ወጣት የህክምና ባለሙያዎች፥ በልዩ ልዩ ሙያ የተማሩ ሴቶች እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎትና በእምነታቸው ጠንካራ ምሳሌ በመሆን ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ በሳል እህቶች ሲገኙ የህይወት ምስክርነትና ተሞክሮዎች ቀርበዋል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደውን ይህን ተልዕኮ ተኮር ስልጠና ከ15 የመሠረተ ክርስቶስ ክልሎች የተውጣጡ 64 እህቶች የተካፈሉ ሲሆን በቀጣይ ትምህርቱ በሌሎች አካባቢዎችም እንደሚቀጥል ይጠበቃል።



መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

  በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል ስር የምትገኘው የባቱ (ዝዋይ) አጥቢያ ከኒው ከቨናንት ሚኒስትሪ ጋር በመተባበር 248 ሰዎችን አጥምቃለች።ተጠማቂዎቹ በአካ...
19/06/2026



በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል ስር የምትገኘው የባቱ (ዝዋይ) አጥቢያ ከኒው ከቨናንት ሚኒስትሪ ጋር በመተባበር 248 ሰዎችን አጥምቃለች።

ተጠማቂዎቹ በአካባቢው በተሰማሩ 50 ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲዮናዊያን አማካኝነት ባለፉት ወራት በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የደህንነት ትምህርታቸውን ተምረው ያጠናቀቁ ናቸው።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

 #በጸጥታ ችግር ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው  የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ   አገልግሎት ተጀመረ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ልማት ኮምሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ ...
19/06/2026

#በጸጥታ ችግር ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ አገልግሎት ተጀመረ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ልማት ኮምሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ ዞን በፀጥታ ችግር ምክንያት ጉዳት በደረሰባቸው ቀበሌዎች የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የሰላም ግንባታ አገልግሎት ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ጀምሯል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ የሐይማኖት ተቋማት ከመንግሥት ጎን በመቆም በተለያዩ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን ለመሥራት እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር ነው ብለዋል።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የአርባምንጭ ጊዜያዊ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ ዘሪሁን ካሳሁን በስፍራው ሲገኙ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ልማት ኮምሽን በሰላም ዕሴት ግንባታ፣ በኑሮ ማሻሻያ፣ በወጣቶችና ህፃናት ፕሮጀክቶች በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ክልሎች በርካታ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ልማት ኮምሽን በክልሉ የሰላም ግንባታ አገልግሎት ከሚሰጥባቸው አምስት ዞኖች መካከል አንዱ በሆነው የኮሬ ዞን የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት ለቀጣይ ሶስት ዓመታት ለአካባቢው ሰላም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ይጠበቃል።

በፕሮግራሙ የተገኙት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም ሰላም ለሰው ልጅ መሰረታዊ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ በመሆኑ ለሰላም መስፈን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   አጥቢያ የወንጌል ስርጭት አካሄደች።በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የአለታ ወንዶ አጥቢያ በአለታ ወንዶ ከተማ በትላንትናው አለት የአንድ ለአንድ እና ...
19/06/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያ የወንጌል ስርጭት አካሄደች።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የአለታ ወንዶ አጥቢያ በአለታ ወንዶ ከተማ በትላንትናው አለት የአንድ ለአንድ እና የጀማ ወንጌል ስብከት አካሂዳለች።

" " በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ከተማ አቀፍ የወንጌል ስርጭት ብዙዎች ወንጌልን ሲሰሙ 15 ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተጨምረዋል።

የወንጌል ስርጭቱ ለአለታ ወንዶ መሠረተ ክርስቶስ አጥቢያ የተሰጠውንና በዘማሪት ስምረት ከበደ " በሚል ስያሜ የተዘጋጀውን የዝማሬ አልበም ምርቃት ምክንያት በማድረግ የተካሄደ ነው።

ሰኔ 14/2018 ዓ.ም የሚመረቀውን ይህን የዝማሬ አልበም ምክንያት በማድረግ በጎዳና ለሚኖሩ ወገኖቻችን ተመሳሳይ አገልግሎት መሰጠቱ የሚታወስ ነው።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

 #አዲስ ለተሰማሩ ቤተ ክርስቲያን ተካይ  #ሚሲዮናውያን የሦስት ቀናት  #ስልጠና ተሰጠ።በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ስርጭትና ቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ በዚህ አመት ለተሰ...
18/06/2026

#አዲስ ለተሰማሩ ቤተ ክርስቲያን ተካይ #ሚሲዮናውያን የሦስት ቀናት #ስልጠና ተሰጠ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ስርጭትና ቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ በዚህ አመት ለተሰማሩ 21 አዳዲስ ቤተ ክርስቲያን ተካይ ሚሲዮናውያን ከሰኔ 8-10/2018 ዓ.ም ለሦስት ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና ተሰጥቷል።

በእነዚህ ቀናት ሚሲዮናውያኑን በመስኩ ሥራ ውጤታማ የሚያደርጋቸው ስልጠና እና የሥራ መመሪያ ሲሰጥ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በስፍራው ተገኝተው "መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከየት ወዴት" በሚል ርዕስ ሥልጠና ሰጥተዋል። ለሚስዮናዊያኑም "ወንጌልን ካልሠራን ምንም አልሠራንም" በማለት ለወንጌል ተልዕኮ አበረታተዋል።

በዋናው ቢሮ የወንጌል ስርጭትና ቤተ ክርስታያን ተከላ መምሪያ አገልጋዮች ሥልጠናው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን ለሚስዮናዊያኑም የወንጌሉን አገልግሎት ለማከናወን የሚያግዙአቸው አጋዥ መጽሐፍ እና ላላመኑ ሰዎች የኢየሱስን ፊልም ማሳየት የሚያስችሏቸው አዳዲስ ታብሌቶች ተበርክቶላቸዋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

18/06/2026

"የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የ75ኛ አመት ክብረበዓል #በ2019 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁሉን ባሳተፈ መልኩ በተለያዩ ፕሮግራሞች በአዲስአበባ እና ባሉን ቀጣናዎች ሁሉ ይከበራል" የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰይፈ ወዳጅ

https://t.me/MKC_Official

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   አጥቢያ  #በጎዳና ለሚኖሩ ወገኖቻችን ድጋፍ አደረገች። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የአለታ ወንዶ አጥቢያ በዛሬው እለት የአጥቢያይቱ ዘማሪ የሆነች...
17/06/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያ #በጎዳና ለሚኖሩ ወገኖቻችን ድጋፍ አደረገች።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የአለታ ወንዶ አጥቢያ በዛሬው እለት የአጥቢያይቱ ዘማሪ የሆነችው ዘማሪት ስምረት ከበደ " " የሚል ስያሜ ያለውን የመጀመሪያ አልበም ምርቃት ምክንያት በማድረግ በጎዳና ለሚኖሩ ወገኖች ድጋፍ አድርጋለች።

"የደጉን ሳምራዊ ባህሪ እንኑረው" በሚል ሀሳብ ከ100 በላይ ለሚሆኑና በጎዳና ለሚኖሩ ወገኖቻችን የምግብ እና የአልባሳት ድጋፍ ተደርጓል።

የዝማሬ አልበሙ ሰኔ 14/2018 ዓ.ም በአለታ ወንዶ ከተማ በምትገኘው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እንደሚመረቅ ያገኘውን መረጃ ያመለክታል።

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

17/06/2026

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን #አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን #75ኛ አመት የመክፈቻ ክብረበዓል ላይ በአዳማ ተገኝተው ያስተላለፉት መልዕክትና ህብረቱ ያበረከተው የማስታወሻ ስጦታ

https://t.me/MKC_Official

 #በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ታሳቢ  #ቀጣና ተመሠረተ።‎በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ታሳቢ ቀጣና ሰኔ 6/2018 ዓ.ም የክልል...
15/06/2026

#በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ታሳቢ #ቀጣና ተመሠረተ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ታሳቢ ቀጣና ሰኔ 6/2018 ዓ.ም የክልልና አጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት በጅማ ከተማ ተመስርቷል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ታሳቢ ቀጣና ካፋ፣ ቢጣ፣ ዋቻ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢልባቦር፣ ጅማ አካባቢ፣ ሚዛንና አካባቢ ታሳቢ ክልሎችን በመያዝ ነው አምስተኛው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ቀጣና በመሆን የተመሰረተው።

በምሥረታው ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰብረላ ከድር፣ የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ተመስገን መንገሻ፣ የክልሎቹ ዋና ጸሐፊዎችና አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባላት እንዲሁም የአጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰብራላ ከድር "መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን አውቆ ማገልገል" በሚል መሪ ሀሳብ ለአንድ ቀን ተኩል ስልጠና ሰጥተዋል። በስልጠናው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነት፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ ውስጠ ደንብ፣ የሙሉ ጊዜ የወንጌል አገልጋዮች እና የአስተዳደር መመሪያዎች እንዲሁም ሌሎች ከአሰራር ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ተመልክተዋል።

መሪዎቹ በጉዞአቸው በኢልባቦር ክልል ስር ያለችውን የያዮ ታሳቢ ክልል ጥናት ያደረጉ ሲሆን በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጅማ ጽዮን አጥቢያ ጉብኝት አድርገዋል። ከታሳቢ ክልሉ እና ከአጥቢያዋ መሪዎች ጋርም ሰፊ የሆነ ምክክርና ጸሎት ተደርጓል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

Address

Africa Avenue Near Destiny Addis Hotel
Addis Ababa
24227

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251115506136

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Meserete Kristos Church - Head Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Meserete Kristos Church - Head Office:

Share

Category