Meserete Kristos Church - Head Office

Meserete Kristos Church - Head Office Meserete Kristos Church (MKC) is established in 1951 to proclaim the Good News of the Lord Jesus Chri

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   ጊዜያዊ ቀጣና ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን አካሄደ።በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጣና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን...
22/08/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጊዜያዊ ቀጣና ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን አካሄደ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጣና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ መንበር ዶ/ር ሰይፈ ወዳጅ፣ የቀጣናው አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባላት፣ የቀጣናው ዋና ጸሐፊ እና በቀጣናው ስር የሚገኙ ክልሎች አስተዳደር መሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት ከነሐሴ 15_16/2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ የመሠረተ ክርስቶስ ሴምናሪ ሦስተኛ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን አካሂዷል።

የጊዜያዊ ቀጣናው አሰተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባለት ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ስብሰባቸውን ሲያደርጉ የ2018 በጀት አመት ሪፖርትና የ2019 በጀት አመት እቅድ በጊዜያዊ ቀጣናው ዋና ጸሐፊ መጋቢ ተስፋዬ ለገሰ ቀርቦላቸው ሰፊ ውይይት በማድረግ ሪፖርቱና እቅዱ ለጠቅላላ ጉባኤ እንዲቀርብ ተስማምተዋል።

በዚህም መሠረት ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም መደበኛ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን ያካሄደው ጊዜያዊ ቀጣናው ስብሰባውን በጸሎት ሲጀምር መጋቢ ዮሐንስ ተሾመ የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል።

በእለቱ የቀጣናው ዋና ጸሐፊ የ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድን ሲያቀርቡ ከሰፊ ውይይትና ጥያቄዎች በኋላ በጉባኤው ጸድቋል። እንዲሁም ጉባኤው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎች አስቀምጧል።

በመጨረሻም በቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቀ መንበር ዶ/ር ሰይፈ ወዳጅ መልእክትና የጋራ ጸሎት ጉባኤው ተጠናቋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   ጊዜያዊ ቀጣና አመታዊ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን አካሄድ።በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ደቡብ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጣና አመታዊ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤ...
22/08/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጊዜያዊ ቀጣና አመታዊ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን አካሄድ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ደቡብ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጣና አመታዊ ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤውን በዛሬው እለት በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲያካሂድ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዘዳንት፣ የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር፣ የቀጣናው አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባላት፣ የቀጣናው ዋና ጸሐፊ፣ ከ16 ክልሎች የመጡ ከ60 በላይ የክልል አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባላትና አገልጋዮች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

ጉባኤው በጋራ ጸሎት፣ በአምልኮ እና በእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ሲጀምር የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ከዘዳግም 33፥26-27 በመነሳት “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም” በሚል ርዕስ መልዕክት አቅርበዋል። በመልዕክታቸውም እግዚአብሔር መኖሪያችን መሆኑን፣ የዘላለም ክንዶቹ ከበታችና ደጋፊዎቻችን መሆናቸውንና በፊታችን ያሉ ጠላቶችን በማሸነፍ የሚያስወርሰን እርሱ መሆኑን አብራርተዋል።

በመቀጠልም የጊዜአዊ ቀጣናው ጠቅላላ ጉባኤ ሲጀምር የቀጣናው አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ ሰብሳቢ ወንድም አየለ ጋቲሶ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ከ16 ክልሎች የመጡ ተወካዮችን እርስ በርስ በመተዋወቅ ጉባኤው ስብሰባውን ጀምሯል።

በጉባኤው የ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድ ቀርቦለት ከጥያቄና ውይይት በኋላ ሲያጸድቅ ሌሎች አጀንዳዎችን ተመልክቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።

በመጨረሻም በጊዜያዊ ቀጣናው ሥር ባሉ ክልሎች ለበርካታ ዓመታት በዋና ጸሐፊነት ያገለገሉና ያረፉ 8 ዋና ጸሐፊዎች በአገልግሎታቸው ተዘክረው እውቅና ሲሰጣቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ቤተ እምነታችንን ላለፉት 7 ዓመታት በፕሬዘዳንትነት ሲመሩ ላስመዘገቡት ውጤት፣ በተለይም ባለፉት 5 ዓመታት በስትራቴጂክ ዕቅዱ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላመጣችው ለውጥና ዕድገት ላበረከቱት ከፍተኛ የአመራር ሚና ቀጣናው ጋቢና ሰርተፊኬት በማበርከት እውቅና ሰጥቷቸዋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

21/08/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ የደቡብ ኢትዮጵያ ቀጣና ጉብኝትና ስልጠና

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት   ጎበኙ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዘደንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ፣ የዋናው ቢሮ መምሪያ ኃላፊ መጋቢ ንጉሤ በቀለ እንዲሁም የቀጣናና የክ...
21/08/2026

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት ጎበኙ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዘደንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ፣ የዋናው ቢሮ መምሪያ ኃላፊ መጋቢ ንጉሤ በቀለ እንዲሁም የቀጣናና የክልል ዋና ጸሐፊዎች በጋራ በመሆን በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሶዶ መሐል አጥቢያን አገልግሎቶችና እያከናወነች የምትገኘውን የባለ 6 ወለል ሕንፃ የጸሎት ቤት ግንባታ መሠረት ዛሬ ጠዋት በስፍራው ተገኝተው ጎብኝተዋል።

መጋቢ ደሳለኝ አበበ ከመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የወላይታ ሶዶ ክልል አጥቢያዎች ለመጡ አገልጋዮችና መሪዎች የእግዚአብሔርን ቃል ከትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ሲያካፍሉ በትምህርታቸውም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ በፈቃደኝነት መቀበል፤ ከስህተታችን ተምረን ወደ እግዚአብሔር መመለስ፤ የእግዚአብሔር ምሕረት ለሁሉም ሰዎች መሆኑን መረዳት፤ እኛ የምንፈልገውን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማስቀደም እና ለሌሎች መዳን በትጋት መሥራት የሚሉ አምስት መሠረታዊ ነጥቦችን ከመጽሐፉ አንስተዋል።

በዕለቱ ጉብኝትና የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት መሪዎችና አገልጋዮቹ እግዚአብሔርን በመታዘዝ፣ በትሕትና፣ በምሕረትና በታማኝነት አገልግሎታቸውን ለመፈጸም መንፈሳዊ መነቃቃትና መበረታታትን አግኝተዋል።

በመጨረሻም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንቱ በአጥቢያዋ ሥራዎች ደስታቸውን ሲገልጹ ይህም ትጋትንና የወደፊት ራዕይን የሚያሳይ መልካም ሥራ መሆኑን ገልጸዋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   ስር በሚገኙ አጥቢያዎች ጉብኝት ተደረገ።የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ፣ የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ...
20/08/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ስር በሚገኙ አጥቢያዎች ጉብኝት ተደረገ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ፣ የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ንጉሤ በቀለ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ቀጣና ዋና ጸሐፊ መጋቢ ደነቀ ሁሴን እና የወላይታ ሶዶ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ አለማየሁ አበራ በጋራ በመሆን በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ወላይታ ሶዶ ክልል ሥር የሚገኙትን የአረካ፣ አቹራና ቦዲቲ አጥቢያዎችን እንዲሁም የሾኔ ክልልንና ሾኔ አጥቢያን ያካትት ጉብኝት በዛሬው እለት አካሂደዋል።

መሪዎቹ በጉብኝታቸው ከአጥቢያ ሽማግሌዎች፣ አገልግሎት ተጠሪዎችና ከክልሉ አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ አባላት ጋር በመገናኘት ስለአገልግሎት፣ ስለተግዳሮቶቻቸውና ስለቀጣይ ዕቅዶች በጋራ ተወያይተዋል፤ በጋራም ጸልየዋል።

በጉብኝቱ የጸሎት ቤት ግንባታ ላይ ያሉ አጥቢያዎችን የግንባታ ሂደት ሲመለከቱ ለማበረታቻ የሚሆን የፍቅር ስጦታቸውን የገንዘብ ድጋፍ አበርክተዋል። ጉብኝቱም በመሪዎችና አገልጋዮች ዘንድ ትልቅ ደስታና መበረታትን እንዲሁም ለአገልግሎታቸው አዲስ መነቃቃትና መነሳሳትን መፍጠር ችሏል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንትና መሪዎቹ በዚህ ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ ቀጣና ያደረጉት ጉብኝት በአጠቃላይ አጥቢያ፣ ክልል፣ ቀጣናና ዋናው ቢሮን በተሻለ መልኩ እንዲያያዙና አገልግሎታቸውን በአንድነት እንዲያጠናክሩ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

📢 በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣና፣ ክልሎችና አጥቢያዎች በሙሉ ‼️
20/08/2026

📢 በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣና፣ ክልሎችና አጥቢያዎች በሙሉ ‼️

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   የመሪነት ስልጠናና የአገልግሎት ምክክር ተካሄደ። የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበና የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ...
19/08/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የመሪነት ስልጠናና የአገልግሎት ምክክር ተካሄደ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበና የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ንጉሤ በቀለ ከሌሎች የቀጣናና ክልል መሪዎች ጋር በመሆን ከነሐሴ 11 ጀምሮ በደቡብ ኢትዮጵያ እያደረጉ በሚገኘው ጉብኝት በዶዮገና ክልል ሥር የምትገኘውንና በ5000 ካሬ ሜትር ይዞታዋ ላይ ጸሎት ቤት የገነባችውን የሠራራ አጥቢያን ለማየት ዕድል አግኝተዋል።

በጉብኝታቸው ከአጥቢያዋ ሽማግሌዎችና የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ጋር ሲወያዩ በአጥቢያዋ አገልግሎትና እድገት እጅግ መደነቃቸውን ገልጸዋል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት በዛሬው እለት በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሺንሺቾ ክልል ሥር ከሚገኙ 22 አጥቢያዎች ለመጡ 70 የአጥቢያ ሽማግሌዎች፣ የአጥቢያ አገልግሎት ተጠሪዎችና የቀጣናና ክልል ተወካዮች “ #የቡድን አመራር አስፈላጊነትና ተግዳሮቶቹ” በሚል ርዕስ የሙሉ ቀን የመሪነት ስልጠና ሲሰጡ ከመሪዎቹ ጋር የአገልግሎት ምክክር ተካሂዷል።

በስልጠናው የቡድን አመራር ያለው ጠቀሜታ፣ በቡድን ውስጥ ያለ የትብብር አስፈላጊነትና መሪዎች ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶች ሲዳሰሱ በተሳታፊዎች ዘንድም ንቁ ተሳትፎና አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት ተችሏል።

በመጨረሻም ጉባኤው መጋቢ ደሳለኝ አበበን በመባረክና ለአገልግሎታቸው በመጸለይ የስልጠና መርሐግብሩን አጠናቋል።

!

መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን   ክልሎች ስልጠናና ጉብኝት ተካሄደ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሆሳዕናና ዶዮገና ክልሎች ከነሐሴ 11_12/2018 ዓ.ም በተካሄደው ስልጠናና ጉብኝ...
18/08/2026

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ክልሎች ስልጠናና ጉብኝት ተካሄደ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሆሳዕናና ዶዮገና ክልሎች ከነሐሴ 11_12/2018 ዓ.ም በተካሄደው ስልጠናና ጉብኝት የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ እና የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ንጉሤ በቀለ እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ቀጣና ዋና ጸሐፊ መጋቢ ደነቀ ሁሴን በስፍራዎቹ ተገኝተዋል።

መሪዎቹ ከሆሳዕናና ዶዮገና ክልል መሪዎች ጋር ሰፊ ምክክርና ውይይት ሲያደርጉ የክልሎቹን አገልግሎት ሁኔታ፣ በክልሎቹ ያሉ ተግዳሮቶችና ዕድሎች፣ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያናችንን አገር አቀፍ አገልግሎትና አጠቃላይ ሁኔታ በስፋት ተመልክተዋል። ውይይቱ ለቀጣይ አገልግሎት ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠበት እንደሆነ ተገልጿል።

ጉብኝቱን ተከትሎ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በዶዮገና ክልል ከ31 አጥቢያዎች ለመጡ 108 መሪዎችና የአጥቢያ አገልጋዮች “መሪን ውጤታማ የሚያደርጉ መንገዶች” በሚል ርዕስ የሙሉ ቀን ስልጠና ሰጥተዋል። ስልጠናውም የተሳካና ስልጠኞችን ያስደሰተ መሆኑ ሲገለጽ በቀጣይ ወደ አጥቢያዎች እንደሚወርድ ይጠበቃል።

የዶዮገና ክልል ባለፉት አምስት አመታት የቤተ ክርስቲያናችንን የአጀንዳ 2819 - የወንጌል አጀንዳ ስልታዊ ዕቅድ ተከትሎ 54 ሚሲዮናውያንን ወደ ሌሎች ክልሎች በመላክ ያሳየው ትጋት የሚያስመሠግነው እንደሆነና አጠቃላይ የክልሉ እድገትም አስደሳች መሆኑን በጉብኝቱ ተመላክቷል።

በሁለቱ ክልሎች ጉብኝትና ስልጠና ከመሪዎቹ ጋር ውጤታማ ምክክርና ውይይት ሲካሄድ ለቀጣይ የጋራ አገልግሎት አቅጣጫ ማስቀመጥ ተችሏል።



መረጃዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ይከታተሉ 👇

በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice

Address

Africa Avenue Near Destiny Addis Hotel
Addis Ababa
24227

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251115506136

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Meserete Kristos Church - Head Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Meserete Kristos Church - Head Office:

Shortcuts

Share

Category