22/06/2026
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ #የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርት ቀረበ።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ መምሪያዎች የ2018 በጀት አመት የአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርታቸውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት በተገኙበት በዛሬው እለት አቀርበዋል።
ከሪፖርቱ አስቀድሞ በቀጣይ ወራት በሚካሄዱ የክልል ጠቅላላ ጉባኤዎች ላይ የሚቀርበውና 2ኛ ጴጥሮስ ምዕራፍ 1፥1-11'ን መሠረት በማድረግ "ጤናማ መንፈሳዊ ህይወት" በሚል ርዕስ በትምህርት ክፍል የተዘጋጀው ትምህርት በመምህር ሰለሞን ግዛቸው ቀርቧል፡።
በአራተኛ ሩብ አመት ሪፖርት ባለፉት ሦስት ወራት የተገኙ ፍሬዎች በዝርዝር ለጉባኤው በመምሪያ ዳይሬክተሮቹ በኩል የቀረበ ሲሆን ከጉባኤው ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ ተሰጥቷል።
በመጨረሻም ጉባኤው ስለተገኙት ፍሬዎችና እግዚአብሔር ስለሰጠን መከናወን እርሱን በማመስገን ስብሰባውን በጸሎት አጠናቋል።
!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice