15/09/2026
#መስከረም 3
ርዕስ ፦ከሁሉም የሚበልጥ መገለጥ
መዝሙረ ዳዊት 150
ሃሌሉያ። እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤ በኃይሉ ጠፈር አመስግኑት።
2 በችሎቱ አመስግኑት፤ በታላቅነቱ ብዛት አመስግኑት።
3 በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።
4 በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት።
5 ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት።
6 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን። ሃሌ ሉያ።