Jesus TV

Jesus TV Jesus tv Ethiopian
Television 24/7 Channel

frequency 11636/7
Symbol rate 27500
polarization vertical
(218)

👉እባካችሁን በትዕግስት ጨርሱት እግዚአብሔር የሚፈልገው እረኛ ማን ነው? ቲቶ 1:5፤ ስለዚህ ምክንያት የቀረውን እንድታደራጅ በየከተማውም፥ እኔ አንተን እንዳዘዝሁ፥ ሽማግሌዎችን እንድትሾም በ...
28/07/2026

👉እባካችሁን በትዕግስት ጨርሱት

እግዚአብሔር የሚፈልገው እረኛ ማን ነው?

ቲቶ 1:5፤ ስለዚህ ምክንያት የቀረውን እንድታደራጅ በየከተማውም፥ እኔ አንተን እንዳዘዝሁ፥ ሽማግሌዎችን እንድትሾም በቀርጤስ ተውሁህ፤

በአዲስ ኪዳን ውስጥ ካሉት የጳውሎስ መልእክቶች መካከል ወደ ቲቶ የተጻፈው መልእክት የእውነተኛ እረኝነትን፣ የቤተ ክርስቲያን አመራርን እና የጤናማ ትምህርትን እጅግ በግልጽ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው። ይህን መልእክት በትክክል ለመረዳት ግን አንድ ዋና ጥያቄ መመለስ አለብን፦ ጳውሎስ ቲቶን ለምን ወደ ቀርጤስ ላከው? በቀርጤስ ምን ችግር አለ በዛስ ያሉት አማኞች እና ቤተክርስቲያንስ ችግራቸው ምን ይሆን ?

በቲቶ መጽሐፍ ላይ የምናነበው የጳውሎስ መልእክት የተጻፈው በሰላም ዘመን አልነበረም፤ ቤተ ክርስቲያን በውስጥና በውጭ ከባድ መናወጥ ባጋጠማት ጊዜ ነበር። የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ቤተ ክርስቲያን በሮማ ግዛት ውስጥ በፍጥነት እየተስፋፋች ነበር፤ ነገር ግን የወንጌል መስፋፋት ከሐሰተኛ ትምህርት፣ ከዓለማዊ ባህል እና ከመንፈሳዊ ጥቃት የተለየ አልነበረም። ጳውሎስ በየከተማው የተተከሉት አብያተ ክርስቲያናት በጤናማ ትምህርትና በቅድስና እንዲቆሙ ያለማቋረጥ ይጨነቅ ነበር።

በዚያ ዘመን ቀርጤስ በሜዲትራኒያን ባሕር ውስጥ ያለች ትልቅ ደሴት ነበረች። በንግድ መንገዶች መሀል ስለነበረች የብዙ ባህሎች፣ የብዙ ሃይማኖቶችና የብዙ ፍልስፍናዎች መገናኛ ሆና ነበር። ነገር ግን በሀብቷ የታወቀችው ያህል በሥነ ምግባሯ አልታወቀችም፤ በግሪክ ዓለም የቀርጤስ ሰዎች በውሸት፣ በማታለል፣ በስግብግብነትና በራስ ወዳድነት የታወቁ ነበሩ። እንዲያውም በግሪክ ቋንቋ “ክሬቲዜይን” የሚለው ቃል “እንደ ቀርጤሳዊ መዋሸት” የሚል ትርጉም እስኪኖረው ድረስ ስማቸው ከውሸት ጋር ተያይዞ ነበር።

ይህን የሚያሳየው ጳውሎስ ራሱ የተናገረው ብቻ አይደለም። ከክርስቶስ ልደት በፊት በስድስተኛው ክፍለ ዘመን የኖረው የቀርጤስ ታዋቂ ነቢይና ገጣሚ ኤፒሜኒዴስ ራሱ ስለ ሕዝቡ እንዲህ ብሎ ጽፎ ነበር፤ “የቀርጤስ ሰዎች ሁልጊዜ ውሸታሞች፣ ክፉ አራዊት፣ ሰነፍ ሆዳሞች ናቸው።” ጳውሎስም ይህንን በቲቶ 1፥12 ሲጠቅስ፣ “ከእነርሱ መካከል የገዛ ነቢያቸው አንዱ…” በማለት ነው የሚናገረው የውጭ ሰው ሳይሆን የራሳቸው ሰው ችግሩን ምን ያክል አስከፊ እንደነበር ያሳያል።

የሚያሳዝነው ግን ይህ የውጭ ማኅበረሰብ ችግር እና ስም በውጭ ብቻ አልቀረም፤ ወደ ቤተ ክርስቲያንም ገባ። የክርስቶስ ስም የተጠራባቸው ሰዎች ገና በእምነት አልበሰሉም፤ የቤተ ክርስቲያን አመራር አልተደራጀም፤ በየከተማው የተሾሙ ሽማግሌዎች አልነበሩም፤ እና ወደቤተክርስቲያን እና ወደ ህዝበ ክርስቲያኑ ዘልቆ በመግባቱ ይህንንም ክፍተት እንደ ትልቅ እድል በመቁጠር ሐሰተኛ አስተማሪዎች የክርስቲያኑን ቤተሰቦችን በትምህርታቸው ያፈርሱ ነበር። ለአስነዋሪ ትርፍ ሲሉ ማስተማር የማይገባቸውን ያስተምሩ ነበር፤ የአይሁድ ተረቶችንና የሰው ትእዛዞችን ከወንጌል ጋር ያቀላቅሉ ነበር። ከዚህ የተነሳ ብዙዎች በአፋቸው እግዚአብሔርን እናውቃለን ቢሉም፣ በሥራቸው ግን በድርጊቶቻቸው ይክዱት ነበር።

እንግዲህ እዚህ ላይ ነው የዚህ የእግዚአብሔር ሰው ሚና ይህን ሁሉ ያየ ጳውሎስ ስለ ራሱ ዝና አልተጨነቀም፤ ስለ ክርስቶስ መንጋ ተጨነቀ። በቲክቶክ ቢስድቡኝ አብረህ በላህ ቢሉኝ ዩቱብ ላይ ቢሰድቡኝ ስለ ስሙ ስለ ማንነቱ ሳይጨነቅ እየተበከለ ስላለው እና እየተበተነ ስለሚመለከተው የእግዚአብሔር ህዝብ ስለዚህም ምክንያት ለማስተካከል ቲቶን ወደ ቀርጤስ ላከው፤ እንዲሸሽ ሳይሆን እንዲቆም፣ እንዲያስተካክል፣ እንዲያቋቁም እና የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን በጤናማ ትምህርት እንደገና እንዲያንጽ።

ይህ ታሪክ የቀርጤስ ብቻ አይደለም፤ በየትውልዱ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነው። ጌታ ዛሬም የሚፈልገው ከችግር የሚሸሽ አገልጋይ ሳይሆን፣ እንደ ቲቶ ወደ ተናወጠው ወደሕዝብ ገብቶ የቀሩትን ነገሮች የሚያስተካክል ታማኝ እረኛ ነው።

ይህ ጥያቄ ስለ አንድ ሰው ጉዞ ብቻ አይደለም፤ ስለ እግዚአብሔር የአገልግሎት ልብ ነው። ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ባሪያዎቹን የሚልካቸው ሰላም ወዳለበት አይደለም፤ ሰላም ወደጠፋበት ነው። ሥርዓት ወዳለበት ሳይሆን ሥርዓት ወደፈረሰበት ነው። እውነት ወደቆመበት ሳይሆን ሐሰት ወደበዛበት ነው።

ቀርጤስ በዚያን ዘመን በሥነ ምግባር የወደቀች፣ በውሸት፣ በማታለልና በራስ ወዳድነት የታወቀች ደሴት ነበረች። ከዚያ የበለጠ የሚያሳዝነው ግን ያ መንፈሳዊ በሽታ ወደ ቤተ ክርስቲያንም መግባቱ ነበር። ሐሰተኛ አስተማሪዎች ተነስተው ቤተሰቦችን ያደናግሩ ነበር፤ የቤተ ክርስቲያን አመራር ገና አልተደራጀም ነበር፤ ብዙዎችም ስለ እግዚአብሔርን በአፋቸው ቢመሰክሩም በኑሯቸው ይክዱት ነበር (ቲቶ 1፥10–16)።

በዚህ ሁኔታ ጳውሎስ ዝም ብሎ አልተመለከተም። ቤተ ክርስቲያን ስትናወጥ እረኛ ዝም ብሎ አይቆምም፤ የተልእኮ ሰው ይልካል። ስለዚህ ቲቶን የላከው ወደ ምቹ አገልግሎት ሳይሆን፣ ወደ መንፈሳዊ ጦርነት ነበር፤ የቀሩትን እንዲያስተካክል፣ ሽማግሌዎችን እንዲሾም፣ ሐሰተኛ ትምህርትን እንዲገሥጽ፣ በጤናማ ትምህርትም የክርስቶስን መንጋ እንዲያጸና ነበር።

ይህ የታሪክ ታሪክ ብቻ አይደለም፤ የዛሬም ጥሪ ነው። ዛሬም ጌታ የሚፈልገው ዝናን የሚያሳድድ አገልጋይ ሳይሆን፣ የተሰበረውን የሚያቀና፣ የተበተነውን የሚሰበስብ፣ በእውነትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ቤቱን የሚያንጽ እረኛ ነው። ቲቶ ወደ ቀርጤስ የተላከበት ምክንያት ይህ ነበር፤ ይህም ዛሬም ለክርስቶስ እያንዳንዱ ታማኝ አገልጋይ የተሰጠ ጥሪ ነው።

ወንድሞቼ እህቶቼ ሆይ፣ ሰዎች “ገንዘብ ተቀብለዋል” ይሉ ይሆናል፤ “ለምን ወደዚያ ሄዱ?” ብለው ይወቅሱ ይሆናል፤ ስማችሁንም ሊያጠፉ ይሞክሩ ይሆናል። ጌታ ግን አንድ ጥያቄ ብቻ ይጠይቃል፤ ስለ እኔ ወይስ ስለ ስማቹህ ? “መንጋዬን ወደድክን?” ወይስ የራስህን ክብር ቀረህ ወይስ ሄደህ አስተካከልክ

በእናንተ መሄድ ምክንያት አንድ ኃጢአተኛ ወደ ንስሐ ቢመጣ፣ አንድ የተበተነ ቤተሰብ ቢታረቅ፣ አንዲት የደከመች ቤተ ክርስቲያን ብትጠነክር፣ አንድ የጠፋች ነፍስ ክርስቶስን ብትቀበል፣ አልያም ያቺ ቤተክርስቲያን ትምህርቷን ብታርም ብታቀና መንጋዎቿን በአግባቡ ብታሰማራ ያ ከሰዎች ነቀፋ ሁሉ ይልቅ የሚበልጥ ሽልማት አይደለምን? አንተ ታማኝ የሚያስብል ተሸላሚ አያደርግምን ?

አንዳንዶች “መልካም ስሜ ይጠፋል” ብለው ይፈራሉ። በእርግጥ ጌታ የሚታዘዙትን ያዛል ልብ አድርግ አንተ አገልጋይ ይህን ከማን ተማርከው ምሳሌህ ማን ነው
ኢየሱስ ካልክ እንግዲያውስ ልንገርህ ጌታ ኢየሱስ ስሙን ለመጠበቅ አልመጣም፤ ራሱን ለመስጠት መጣ (ማርቆስ 10፥45)። ጳውሎስም ቲቶን ወደ ቀርጤስ የላከው ዝናውን እንዲጠብቅ ሳይሆን፣ የፈረሰውን እንዲያቀና፣ የተበተነውን እንዲሰበስብ እና በእውነት እንዲያቆም ነበር።

እግዚአብሔር ከእኛ የሚፈልገው የማይነቀፍ ስም አይደለም፤ ታማኝ ልብ ነው። ከሰዎች ዘንድ ያለንን ክብር ከክርስቶስ በጎች በላይ ካስቀመጥን፣ ዝናችንን ከወንጌል በላይ ካደረግን፣ ስማችን እንዳይነካ ብለን የተበተነውን መንጋ ችላ ካልን፣ የመልካሙን እረኛ ልብ አንከተልም።

ክርስቶስ በዮሐንስ 10 እንደተናገረው ቅጥረኛው ተኩላውን ሲያይ ይሸሻል፤ እውነተኛው እረኛ ግን ሕይወቱን ለበጎቹ ያኖራል። በሕዝቅኤል 34 ደግሞ እግዚአብሔር እረኞችን፣ “ደካሞችን አበረታታችሁ? የተበተኑትን ሰበሰባችሁ? የጠፉትን ፈለጋችሁ?” ብሎ ይጠይቃቸዋል። ጌታ የሚጠይቀው ስለ ዲግሪያችሁ፣ ስለ ማዕረጋችሁ፣ ስለ ተከታዮቻችሁ ወይም ስለ ዝናችሁ አይደለም፤ ስለ መንጋው ታማኝነታችሁ ነው።

ስለዚህ ከስንፍና እረኝነት እንውጣ። በሩቅ ቆመን ከመተቸት ይልቅ ወደ ተሰበረው እንሂድ። ከማኅበራዊ ሚዲያ ክርክር ይልቅ የተበተነውን መንጋ እንሰብስብ። ከታላቅ ስም ይልቅ ታማኝ አገልግሎትን እንምረጥ።

ምክንያቱም በመጨረሻ ጌታ “ስንት ተከታይ ነበረህ?” አይልም፤ “የሰጠሁህን መንጋ በታማኝነት ጠበቅህን?” ብሎ ይጠይቃል። በዚያ ቀን የሚከበረው ታላቅ ስም ያለው ሰው ሳይሆን፣ ለመልካሙ እረኛ ታማኝ ሆኖ የኖረው አገልጋይ ይሆናል።

“እንግዲህ ታማኝና መልካም ባሪያ፣ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ።” (ማቴዎስ 25፥21)

ስለዚህ እመርቃችኋለሁ…አሜን በሉኝ

ሐዋርያው ጳውሎስ በቲቶ እንደተማመነ፣ እግዚአብሔርም በእናንተ እንዲታመን እመርቃችኋለሁ።

እንደ ቲቶ የምትሄዱበት ሁሉ የደከመች ቤተ ክርስቲያን ትበርታ፤ የተሰበረ ልብ ይፈወስ፤ የጠፋ ነፍስ ወደ ክርስቶስ ትመለስ።

የምትሰብኩት ወንጌል በቃል ብቻ ሳይሆን በኃይል፣ በመንፈስ ቅዱስና በተለወጠ ሕይወት ይገለጥ።

የምትናገሩት እውነት የተኙትን ያንቃ፣ የተሳሳቱትን ይመልስ፣ የደከሙትን ያበርታ፣ የተስፋ ቆራጮችን እንደገና በክርስቶስ ተስፋ ይሙላ።

እንደ ቲቶ የተበላሸውን ሥርዓት የምታቀኑ፣ ብቁ መሪዎችን የምታስነሱ፣ ጤናማ ትምህርትን የምታጸኑ፣ ቅዱሳንን ለመልካም ሥራ የምታዘጋጁ ይሁኑ።

በምትሄዱበት ሁሉ የጨለማ ሥራ ይፍረስ፤ የክርስቶስ ብርሃን ይብራ፤ ቤተ ክርስቲያን በእምነት፣ በፍቅርና በቅድስና ትታነጽ።

እንደ ቲቶ የምትተክሉት አገልግሎት ከእናንተ በኋላም ፍሬ የሚያፈራ ይሁን፤ የምታፈሩት ፍሬ ለአንድ ዘመን ሳይሆን ለትውልድ ይኑር።

👉በመጨረሻም፣ እንደ ቲቶ ስትጨርሱ የምትተዉት ሕንፃ ሳይሆን የተገነባ ቤተ ክርስቲያን፣ ስም ሳይሆን የተለወጠ ሕይወት፣ ዝና ሳይሆን የሚኖር ፍሬ፣ ክብርም ለእናንተ ሳይሆን ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን።
በመጨረሻዬም አሜን ካላችሁኝ እንደ ቃሉ መሰረት

🙏የጳውሎስ ራእይ፣ የቲቶ ታማኝነት፣ የመንፈስ ቅዱስ ቅባት እና የክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን።

🙏እግዚአብሔር ለምን ይህን ጠላው ? እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፤ በዚህ ችግር ያልተነካ ማን አለ?ምሳሌ 6፥16–19“እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤ ሰባተኛውም ለእርሱ አስጸያፊ ነ...
25/07/2026

🙏እግዚአብሔር ለምን ይህን ጠላው ? እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፤ በዚህ ችግር ያልተነካ ማን አለ?

ምሳሌ 6፥16–19“እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤ ሰባተኛውም ለእርሱ አስጸያፊ ነው፤ ትዕቢተኛ ዓይኖች፣ የውሸት ምላስ፣ ንጹሕን ደም የሚያፈሱ እጆች፣ ክፉ አሳብን የሚያስብ ልብ፣ ወደ ክፋት ለመሮጥ የሚፈጥኑ እግሮች፣ በሐሰት የሚመሰክር ሐሰተኛ ምስክር፣ በወንድሞችም መካከል ጠብ የሚዘራ።”

ወገኖቼ ሆይ፣ በዚህ ዘመን ሰውን በሐሰት ስም ማጥፋት እጅግ እየተበራከተ፣ እየተስፋፋ ያለ እንደ አደገኛ ወረርሽኝ ሆኗል። ይህ ክፉ ልማድ ከአንድ ሰው ወደ ሌላው፣ ከአንድ ቤት ወደ ሌላው፣ ከአንድ ቤተ ክርስቲያን ወደ ሌላው፣ ከአንድ ማኅበረሰብ ወደ ሌላው፣ ከአንድ አገር ወደ ሌላው በፍጥነት የሚዛመት መንፈሳዊ በሽታ ሆኗል። አንድ ሰው የሐሰት ወሬን ይጀምራል፤ ሌላው ያለማረጋገጥ ይቀበለዋል፤ ሦስተኛው ያሰራጨዋል፤ በመጨረሻም ውሸት እንደ እውነት ተቆጥሮ በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ ይቀመጣል።

እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ፤ በዚህ ችግር ያልተነካ ማን አለ? በሐሰት ያልተወነጀለ ማን አለ? በሐሜት ያልተጎዳ ቤተሰብ የት አለ? በውሸት ያልጠለሸ መልካም ስም የት አለ? በአንድ የሐሰት ቃል ያልተሰበረ ልብ፣ በአንድ የውሸት ወሬ ያልፈረሰ ወዳጅነት፣ በአንድ የሐሰት ክስ ያልተጎዳ አገልግሎት የት አለ?

የያዕቆብ መልእክት 3፥5–6 እንዲህ ይላል፦ “ምላስ ትንሽ ብልት ናት፤ ታላቅ ነገርም ትመካለች። ታናሽ እሳት እንዴት ትልቅ ዱር እንደምታቃጥል እዩ፤ ምላስም እሳት ናት።” ቃሉ “ምላስ እሳት ናት” ብሎ ሲናገር ያለ ምክንያት አይደለም። እሳት ሲለቀቅ መጀመሪያ አንድን ቅጠል ታቃጥላለች፤ ከዚያ ግን ሙሉ ጫካን ትበላለች። እንዲሁም አንድ የሐሰት ቃል የብዙ ዓመታትን መልካም ስም ሊያቃጥል ይችላል። አንድ የውሸት ወሬ ትዳርን ሊበትን፣ ቤተሰብን ሊያፈርስ፣ ወዳጅነትን ሊቆርጥ፣ አገልግሎትን ሊያዳክም፣ ማኅበረሰብን ሊከፋፍል ይችላል። ቃሉ ትንሽ ሊሆን ይችላል፤ የሚያስከትለው ጉዳት ግን እጅግ ትልቅ ነው።

ይህ ኃጢአት የተወሰነ ዕድሜ፣ ጾታ፣ ሀገር ወይም ማኅበራዊ ደረጃ አያውቅም። “ሕፃናት ናቸው የሚያደርጉት” ብለን ብናስብ አዋቂዎችም በዚህ ይወድቃሉ። “ሴቶች ብቻ ናቸው” ብለን ብንፈርድ ወንዶችም እንዲሁ ተሳታፊ ሆነው እናገኛቸዋለን። “ይህ የማያምኑ ሰዎች ጠባይ ነው” ብለን ብንገምት አንዳንድ ጊዜ አማኞችም፣ እንዲያውም አገልጋዮችም ያልጠበቅናቸው በቅዱስ ጉባኤ የሚቆሙ በዚህ ፈተና ውስጥ ወድቀው እናገኛቸዋለን። “ወጣቶች ናቸው” ብለን ብንወስን ሽበት የሸፈነ ራስ፣ በዓመት የገፋ ሰውም በዚህ ኃጢአት ውስጥ ሲመላለስ እናያለን። “ከሩቅ ሰዎች ይመጣል” ብለን ብንጠብቅ የሚያሳምመን ውሸት ከምንወዳቸው፣ ከምንቀርባቸው፣ ከምንተማመናቸው ሰዎች ሲወጣ እናገኘዋለን። ብዙ ጊዜ የሚያስለቅሰን ቃል ከጠላት ሳይሆን ከወዳጅ ይመጣል፤ የሚያቆስለን ውሸት ከባዕድ ሳይሆን ከቅርብ ሰው እንጀራቹሁን ከሚበላ ይወጣል።

ወገኖቼ ሆይ፣ እግዚአብሔር ምላስን የፈጠረው እርሱን እንድናመሰግንበት፣ እውነትን እንድንናገርበት፣ የተሰበረን እንድናጽናናበት፣ የወደቀን እንድናነሳበት ነው፤ እንጂ የሰውን መልካም ስም እንድናቃጥልበት አይደለም። ነገር ግን ምላስ ለሐሰት ስትገዛ እሳት ትሆናለች፤ ሰላምን ታቃጥላለች፣ ፍቅርን ታቃጥላለች፣ አንድነትን ታቃጥላለች፣ መልካም ስምንም እንደ አመድ ታደርጋለች።

ስለዚህ እግዚአብሔር በምሳሌ 6፥16–19 የውሸት ምላስን፣ በሐሰት የሚመሰክረውን እና በወንድሞች መካከል ጠብ የሚዘራውን እንደሚጠላ በግልጽ ተናገረ ። ይህ ሰዎች ብቻ የሚጠሉት ኃጢአት አይደለም፤ የሰማይና የምድር ፈጣሪ ራሱ የሚጠላው ኃጢአት ነው።

ስለዚህ ዛሬ ራሳችንን እንመርምር፤ ምላሳችን ሕይወትን እየዘራች ነውን? ወይስ እሳትን? ሰላምን እያበዛች ነውን? ወይስ ጠብን? እውነትን እየተናገረች ነውን? ወይስ የሰውን ስም የሚያጠፋ ውሸትን?

እኛ የክርስቶስ ተከታዮች ከሆንን፣ ምላሳችን የጥፋት መሣሪያ ሳይሆን የእውነት፣ የፍቅር፣ የሰላም እና የሕይወት መሣሪያ ትሁን። ምክንያቱም ውሸት ለጊዜው ሰዎችን ሊያሳምን ትችላለች፤ እውነት ግን በመጨረሻ ሁልጊዜ ትቆማለች። ሰው በሐሰት ስም ሊያጠፋ ይችላል፤ እግዚአብሔር ግን ፍትሕን ያቆማል፣ እውነትን ያጸናል፣ በጽድቅም ይፈርዳል።

ወዳጆቼ ሆይ፣ ብዙ ሰዎች ሐሰትን መናገር፣ ሰውን በሐሜት ማጥፋት ወይም ያልተረጋገጠ ወሬ ማሰራጨት እንደ ቀላል ነገር ያስባሉ። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ይህን እንደ ቀላል ስህተት አያየውም፤ እግዚአብሔር ራሱ “እጠላዋለሁ” የሚለው ኃጢአት መሆኑን ያስተምራል። ሰውን በሐሰት መወንጀል ሰውን ብቻ መጉዳት አይደለም፤ የፍትሕ አምላክ በሚጠላው የክፋት ሥራ ላይ ከሰይጣን ጋር በመተባበር በአንድነት እውነትን በመቃወም መስራት ነው።

ኢየሱስ በዮሐንስ 8፥44 ሰይጣንን “የውሸት አባት” ብሎ ጠርቶታል፤ እርሱ ግን በዮሐንስ 14፥6 “እኔ መንገድ፣ እውነትና ሕይወት ነኝ” ብሏል። ስለዚህ ሐሰትን የሚያሰራጭ ሰው የክርስቶስን መንገድ አይከተልም፤ የውሸትን አባት ባሕርይ እያሳየ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር በዚህ ኃጢአት ላይ ፍርዱን እንዴት እንዳሳየ በግልጽ ያስተምራል።

በ1 ነገሥት 21 ናቡቴን የአባቶቹን ርስት ለንጉሥ አክአብ ለመስጠት ፈቃደኛ አልነበረም። ኤልዛቤልም ሁለት የሐሰት ምስክሮችን አቆመች፣ “ናቡቴን እግዚአብሔርንና ንጉሡን ተሳድቧል” ብለው በሐሰት እንዲመሰክሩበት አደረገች። ናቡቴን በድንጋይ ተወግሮ ተገደለ፤ የወይን ቦታውም ተወሰደ። ሰዎች ዝም አሉ፣ እግዚአብሔር ግን ዝም አላለም።
በ1 ነገሥት 21፥17–24 ነቢዩ ኤልያስን ልኮ በአክአብና በኤልዛቤል ላይ የፍርድ ቃል ተናገረ። በኋላም በ2 ነገሥት 9፥30–37 ኤልዛቤል ከመስኮት ተወርውራ ሞተች፤ ቃሉም እንደተነገረው ተፈጸመ። ይህ ታሪክ የሚያስተምረን፣

👉ሐሰት ለጊዜው የሚያሸንፍ ቢመስልም የእግዚአብሔርን ፍርድ ማምለጥ እንደማይቻል ነው።

በሐዋርያት 5፥1–11 ደግሞ ሐናንያና ሰጲራ ለሰዎች ቅዱሳን ለመምሰል ዋሹ። ጴጥሮስ “ለሰዎች ሳይሆን ለእግዚአብሔር ዋሻችሁ” አላቸው። በዚያው ቀን ሁለቱም ሞቱ፣ በቤተ ክርስቲያንም ታላቅ ፍርሃት ሆነ።

👉ይህ እግዚአብሔር ሐሰትን በቤቱ ውስጥ እንደማይታገሥ ያሳያል።

በመጽሐፈ አስቴር 3–7 ሐማ በቅናት ሞርዶክዮስን ለማጥፋት እና መላውን የአይሁድ ሕዝብ ለማጥፋት ሴራ ሠራ። ነገር ግን እግዚአብሔር ፍርዱን አሳየ፤ ሐማ ለሞርዶክዮስ ያዘጋጀው ማንጠልጠያ ላይ ራሱ ተሰቀለ (አስቴር 7፥9–10)።

👉ይህ የሚያስተምረን፣ ሌላን ለማጥፋት የሚዘጋጀው ክፋት በመጨረሻ በራሱ ላይ ሊመለስ እንደሚችል ነው።

በዳንኤል 6 የዳንኤል ጠላቶች በቅናት ተነስተው ንጉሡን አሳስተው ዳንኤልን ወደ አንበሶች ጉድጓድ እንዲጣል አደረጉ።

እግዚአብሔር ግን መልአኩን ልኮ ዳንኤልን አዳነ። ከዚያም የሐሰቱ ሴራ በሠሩት ሰዎች ላይ ተመለሰ እነርሱ ለዳንኤል ባዘጋጁት ወጥመድ ላይ ገቡበት (ዳንኤል 6፥24)።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ እንኳን ይህን አይነት የሃሰት ክስ ደርሶበታል ። ማቴዎስ 26፥59–61 “ሊቃነ ካህናትና ሸንጎው ሁሉ ኢየሱስን ለማስገደል በእርሱ ላይ የሐሰት ምስክር ፈለጉ” ይላል። ፍጹም ጻድቅ የሆነው ጌታ በሐሰት ተከሰሰ። እግዚአብሔር ግን በትንሣኤው እውነቱን ገለጠ፤ ሰው ሊያጠፋው የሞከረውን ስም ከስሞች ሁሉ በላይ ከፍ አደረገ (ፊልጵስዩስ 2፥9–11)።

ስለዚህ ወንድሜ ሆይ፣ እህቴ ሆይ፣ ከሰው ስም ላይ አንድ ቃል ከመናገራችን በፊት እናስብ ። ያ ሰው አንተ የማታውቀው የእግዚአብሔር አገልጋይ ወይም በክርስቶስ ደም የተገዛ ሰው ሊሆን ይችላል። ዛሬ ሰዎችን በሐሰት ብታሳምንም፣ ነገ ግን በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እውነት ብቻ ይቆማል። ኢየሱስ “ሰዎች የተናገሩትን ከንቱ ቃል ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል ” ብሏል (ማቴዎስ 12፥36–37)።

ስለዚህ የክርስቶስ ተከታዮች ጥሪ የሰውን ስም ማጥፋት ሳይሆን፣ እውነትን በፍቅር መናገር፣ የተሰበረውን መጠገን፣ ሰላምን መዝራት እና የክርስቶስን አካል መገንባት ነው። ምላሳችን የጥፋት መሣሪያ ሳይሆን የእውነት፣ የፍቅር እና የሕይወት መሣሪያ ይሁን።

ስለዚህ ወንድሜ ሆይ፣ እህቴ ሆይ፣ ከሰው ስም ላይ አንዲት ቃል ከመናገራችን በፊት እናስብ። ያን ሰው ባትወደውም፣ ባትቀበለውም፣ በሐሳቡ ባትስማማም ወይም አገልግሎቱን የማትቀበለው ያልገባን ነገር ቢኖር ፣ በሐሰት ስሙን ለማጥፋት መብት የለንም ። ምክንያቱም የምታዋርደው ሰው በክርስቶስ ደም የተዋጀ፣ ወይም የእግዚአብሔር አገልጋይ ሊሆን ይችላል።

ዛሬ ሰዎችን በውሸት ልናሳምን እንችላለን ወይም ትችላለህ፤ ነገር ግን ነገ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ውሸት አይቆምም፤ እውነት ብቻ ትቆማለች። ሰው ያልሰማውን እግዚአብሔር ይሰማል፤ ሰው ያላየውን እግዚአብሔር ያያል፤ ሰው የረሳውንም እግዚአብሔር አይረሳውም።

ጌታ ኢየሱስ እንዲህ ብሏል፦ “ሰዎች የተናገሩትን ከንቱ ቃል ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል፤ በቃልህ ትጸድቃለህ፣ በቃልህም ትኮነናለህ።” (ማቴዎስ 12፥36–37)

ስለዚህ ወገኖቼ ሆይ፣ የሰውን ስም አታጥፉ፤ የራሳችሁን ፍርድ አታብዙ። ምላሳችሁ የጥፋት እሳት ሳትሆን የሕይወት ምንጭ ትሁን፤ ውሸትን ሳትዘሩ እውነትን ዝሩ፤ ሰውን ሳታዋርዱ ክርስቶስን አክብሩ።

ምክንያቱም የሰውን ስም በሐሰት ማጥፋት ለጊዜው የሚያሸንፍ ሊመስል ይችላል፤ በመጨረሻ ግን እውነት ትነግሣለች፣ እግዚአብሔርም በጽድቅ ይፈርዳል።

በመጨረሻም “በሐሰት ለተጎዳችሁ ወገኖቼ፣ ልባችሁ ምን ያህል እንደተሰበረ እግዚአብሔር ያውቃል። ሰዎች ስለ እናንተ ያልሆነ ነገር ሲናገሩ፣ ስማችሁን ሲያጠፉ እና ያላደረጋችሁትን ነገር ሲወነጅሏችሁ የሚሰማችሁን ህመም እርሱ ያውቀዋል። ነገር ግን ተስፋ አትቁረጡ። እግዚአብሔር የተሰበረውን ልባችሁን ይፈውሳል፣ እንባችሁን ያብሳል፣ የተጎዳችሁበትንም ይክሳል ይመልሳል። ሰው በሐሰት ሊፈርድባችሁ ይችላል፤ እግዚአብሔር ግን በእውነት ይፈርዳል። ዝምታችሁ ከንቱ አይሆንም፤ እውነት በመጨረሻ ሁልጊዜ ታሸንፋለች።”

“እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፤ መንፈሳቸውም ለደቀቀ ያድናል።” (መዝሙር 34፥18)
አሜን !

👂አንበጣው የበላውን ዓመታት እመልስላችኋለሁ” (ኢዮኤል 2፥25) 🔥🔥 የተሐድሶና የተአምራት ጉባኤ 🔥🔥ከማለዳዉ 12:00 ጀምሮ  በማለዳ  በመገኘት  የፀሎት  ቦታዎችን ይያዙ የእግዚአብሔር ሰ...
26/06/2026

👂አንበጣው የበላውን ዓመታት እመልስላችኋለሁ”
(ኢዮኤል 2፥25)

🔥🔥 የተሐድሶና የተአምራት ጉባኤ 🔥🔥ከማለዳዉ 12:00 ጀምሮ በማለዳ በመገኘት የፀሎት ቦታዎችን ይያዙ የእግዚአብሔር ሰዉ በማለዳ ለህዝቡ ፀሎት እንደሚጀምሩ እናሳስባለን

🙏ውድ የእግዚአብሔር ወገኖች ! በቅዳሜ መገኘት ካልቻላችሁ፣ እባካችሁን እሁድን ፈጽሞ አትቅሩ። እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያዘጋጀው የክብር ጉብኝትና የተሐድሶ ጊዜ እንደሚሆን እናምናለን።

እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ሕዝቡን ወደ ተሐድሶ፣ ወደ ፈውስ፣ ወደ ነጻነትና ወደ ክብሩ እየጠራ ነው።
ስለዚህ በዚህ ቅዳሜና እሁድ ለሚካሄደው የተሐድሶና የተአምራት ጉባኤ በፍቅር ተጋብዛችኋል።

“አንበጣው የበላውን ዓመታት እመልስላችኋለሁ” (ኢዮኤል 2፥25) የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል በእምነት እየጠበቅን፣ የጠፋው እንዲመለስ፣ የተሰበረው እንዲጠገን፣ የታሰረው ነጻ እንዲወጣ እና የእግዚአብሔር ክብር በኃይል እንዲገለጥ እንጠብቃለን።

በቅዳሜ መገኘት ካልቻላችሁ፣ እባካችሁ እሁድን ፈጽሞ አታምልጡ። እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያዘጋጀው የክብር ጉብኝትና የተሐድሶ ጊዜ እንደሚሆን እናምናለን።

ሐዋርያት ሥራ 3:19-20፤ እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።

በእምነት ኑ፤ በተስፋ ኑ፤ ለተሐድሶ ተዘጋጅታችሁ ኑ!

🔥 ተሐድሶ አለ!
🔥 ፈውስ አለ!
🔥 ተአምራት አሉ!
🔥 የእግዚአብሔር ክብር ይገለጣል!

🙏የመንግስቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን አድራሻ፡-ታክሲ ወይም አውቶቡስ ለምትይዙ

ከአራት ኪሎ ታክሲ ተራ ቤላ ታክሲ በመሳፈር ቤላ አስራ አስራ ስምንት ማዞሪያ ወደ አቦ በሚወስደው መንገድ 200 ሜትር ዳገቱን እንደወጡ በስተግራ በኩል ያገኙናል !
Our church Address Gps
Taxi 🚖 ride|| taxi 🚕

https://maps.app.goo.gl/26Gu8Y9VFS8eCi96A?g_st=it
የቤተክርስቲያን ስልክ
ለበለጠ -መረጃ
+251944723090
+251944723091
+251944723092
+251944723093

www.thegospelofkingdom.org

🚩ኑ በ4 ኪሎ ቤላ 18 ማዞሪያ ሲደርሱ ይውረዱ የመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን

Gps location just click
https://maps.app.goo.gl/ks7RCA2krKzB9kjZ8?g_st=ic https://youtu.be/H55Lsr2hGz4?si=E-co1cpkBSH70lfz

🚩 የድጋፍ እጆች እና የእግዚአብሔር ድል በዘፀአት 17:8–13)በዘፀአት 17 ላይ የምናየው ክስተት ብቻ የጦርነት ታሪክ አይደለም፤ ከዚያ በላይ የመንፈሳዊ ስርዓት መግለጫ ነው። “አማሌቅ መጥ...
24/06/2026

🚩 የድጋፍ እጆች እና የእግዚአብሔር ድል

በዘፀአት 17:8–13)በዘፀአት 17 ላይ የምናየው ክስተት ብቻ የጦርነት ታሪክ አይደለም፤ ከዚያ በላይ የመንፈሳዊ ስርዓት መግለጫ ነው። “አማሌቅ መጥቶ ከእስራኤል ጋር በራፊዲም ተዋጋ” (ዘፀአት 17፥8) ብሎ የሚጀምረው ጦርነት በምድር ላይ ቢመስልም፣ በእውነቱ በሰማይ እና በምድር መካከል የሚካሄድ መንፈሳዊ ትግል ነበር።

ሙሴ ኢያሱን ሰዎችን ምረጥ ብሎ ሲልከው በምድር ላይ የሚታየው ጦርነት ጀመረ፣ ነገር ግን ሙሴ ራሱ ወደ ኮረብታ ራስ ወጥቶ የእግዚአብሔርን በትር በእጁ ይዞ ቆመ። እዚያ ላይ የሆነው ነገር በጦር መሣሪያ አልተወሰነም፤ በእጆቹ አቅጣጫ ተወሰነ።
መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ ዘጸአት 17:11፤ እንዲህም ሆነ፤ ሙሴ እጁን ባነሣ ጊዜ እስራኤል ድል ያደርግ ነበር፤ እጁንም ባወረደ ጊዜ አማሌቅ ድል ያደርግ ነበር።ይህ ግን አንድ ነገር ያሳያል፤ ድል በሰው ኃይል ብቻ አይደለም፣ በመንፈሳዊ ትብብር ነው የሚቆይ።
ሙሴ ረጅም ጊዜ ቆሞ ስለነበር እጆቹ ደከሙ። ይህ የሰው ድካም እና የመሪነት ገደብ ምሳሌ ነው። በዚያ ጊዜ ግን አሮንና ሆር ተገኙ፤ ድንጋይ አምጥተው አስቀመጡት እና አንዱ በአንድ ወገን አንዱ በሌላ ወገን ቆመው እጆቹን ደገፉ። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ “እስከ ፀሐይ መጥለቂያ ድረስ እጆቹ ጸኑ” (ዘፀአት 17፥12)።እዚህ የምንያየው ብቻ የአካላዊ ድጋፍ አይደለም፤ የመንፈሳዊ ስርዓት ነው። ሙሴ የተሰጠውን ተልእኮ ሲያከናውን አሮንና ሆር በድካሙ ጊዜ ከጎኑ ቆመው አልተቀመጡም።
እነሱ ሙሴ በእግዚአብሔር የተሰጠውን ስራ እንዳይቆም ተደግፈው አቆዩት።ይህ ሁሉ ሲያጠቃልል የሚያሳየው ጥልቅ መንፈሳዊ እውነት አለ፤ እግዚአብሔር ሥራውን በአንድ ሰው ብቻ አያደርግም፣ በአካል አንድነት / በመንፈሳዊ ትብብር” ይፈጽማል ኢያሱ በጦር ሜዳ ተዋጋ፣ ሙሴ በኮረብታ ጸለየ፣ አሮንና ሆር ደግሞ የመደገፍ ኃላፊነት ተሸክመው ቆዩ። ሁሉም በቦታቸው ሲሰሩ ድል ተገኘ።ይህ ታሪክ የሚያስተምረን ነገር አንዱ ይህ ነው፤ የእግዚአብሔር ድል ብቻ በመድረክ ላይ በሚታዩ መሪዎች አይገኝም፤ ከጎን ቆመው የሚደግፉ ሰዎችም የድሉ አካል ናቸው።

✝️ 🕊️ የባርኮት ጸሎት አሜን በሉ ! በዚህ የአማሌቅ ጦርነት ታሪክ ውስጥ የምትገለጥ እግዚአብሔር ጣት እና ኃይል በህይወታቹህ ይገለጥ።

🙏 እግዚአብሔር የምትጀምሩትን ስራ እስከ ፍጻሜ የሚያደርስ ጸጋ ይስጣቹህ።እጆቻቹህ እንደ ሙሴ በእምነት የሚቆሙ ይሁኑ፣ በድካም እንኳን የማይወርዱ የምይርዱ ይሁኑ ።

🤝 እንደ አሮንና ሆር ያሉ የሚደግፉ ሰዎች እግዚአብሔር በህይወታቹህ ያኑር።በድካም ጊዜ እጆቻችሁን የሚያነሱ፣ በከባድ ሰዓት ደግፈው የሚቆሙ ከጎናቹህ አይለዩ።ሰው ሲደክመው በማይደክሙ
⚔️ በህይወት ጦርነት እግዚአብሔር እንደ ኢያሱ የምትዋጉበትን ሰይፍ እና ኃይል፣ ጥንካሬ እና ድል ይሰጣቹህ።

🕊️ እግዚአብሔር በምትሰሩት ሁሉ ድል ያስገኝ፣በብቸኝነት ሳይሆን በአንድነት የተባረከ ህይወት ይስጣቹህ።✝️ የሰማይ አምላክ እጆቻቹህን ያጽና፣ ልባቹህን ያበረታ፣ መንገዳቹህን ይባርክ።በጀመራቹህ ሁሉ ድል እንዲሆን ይደረግላቹህ።በኢየሱስ ክርስቶሰ ስም አሜን። 🙏

🙏በአደገኛ ስፍራም ቢሆን እግዚአብሔር እቅድ አለው!”ብዙ አማኞች የእግዚአብሔር ፈቃድ ሁልጊዜ ምቹ መንገድ እንደሚሆን ያስባሉ። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ መራው እንጂ ...
03/06/2026

🙏በአደገኛ ስፍራም ቢሆን እግዚአብሔር እቅድ አለው!”

ብዙ አማኞች የእግዚአብሔር ፈቃድ ሁልጊዜ ምቹ መንገድ እንደሚሆን ያስባሉ። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ መራው እንጂ ወደ ቤተ መንግሥት አልመራውም። ምድረ በዳው የፈተና፣ የብቸኝነትና የሰይጣን ግጭት ስፍራ ነበር። ለሰው ዓይን አደገኛ ቢመስልም በእግዚአብሔር ፊት ግን የዝግጅት ስፍራ ነበር።

የማቴዎስ ወንጌል 4:1፤ ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥

በመንግሥቱ ውስጥ ትልቅ ምስጢር አለ፤ እግዚአብሔር እጣ ፈንታን በመከራ ውስጥ ይደብቃል። ዮሴፍ ዕጣ ፈንታውን በአባቱ ቤት አላገኘም፤ በጉድጓድ፣ በባርነት፣ በሐሰት ክስና በእስር ቤት ውስጥ አገኘው። የገባበት እያንዳንዱ አደገኛ ስፍራ ከተስፋው እየራቀ ያለ ቢመስልም፣ በመንፈስ ግን ወደ ዙፋኑ እየቀረበ ነበር።

ጠላት ዮሴፍን እየቀበረ እንዳለ አሰበ፤ እግዚአብሔር ግን እየተከለው ነበር።
ዘፍጥረት 37፥24“ወስደውም ወደ ጉድጓድ ጣሉት፤ ጉድጓዱም ባዶ ነበር፥ ውኃም አልነበረበትም።”

ዘፍጥረት 39፥2“እግዚአብሔርም ከዮሴፍ ጋር ነበረ፥ የተከናወነለትም ሰው ሆነ።”

ስለዚህ አማኝ የእግዚአብሔርን አላማ በአሁኑ ሁኔታ ሊመዝነው አይገባም። የሰው ዓይን እስር ቤትን ያያል፤ እግዚአብሔር ግን ዝግጅትን ያያል። የሰው ዓይን ማዕበልን ያያል፤ እግዚአብሔር ግን መጓጓዣን ያያል። የሰው ዓይን ጦርነትን ያያል፤ እግዚአብሔር ግን መገለጥን ያያል። “ያለሁበትን ስፍራ ላልረዳ እችላለሁ፤ ነገር ግን ወደዚህ ያመጣኝን አምላኬን አምናለሁ። አደጋው እውነት ነው፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር እቅድ ከእርሱ ይበልጣል። ጦርነቱ ከባድ ነው፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ይበልጣል። ማዕበሉ ቢጮህም ዕጣ ፈንታዬ በእግዚአብሔር የማይለወጥ እቅድ ላይ ተመስርቶአል።”

እግዚአብሔር ለሕይወትህ እቅድ ሲኖረው፣ እጅግ አደገኛ የሚመስለው ስፍራ እንኳ የክብሩ መገለጫ መድረክ ይሆናል።“በአደገኛ ስፍራም ቢሆን እግዚአብሔር እቅድ አለው!”

ስለዚህ የሰው ዓይን እስር ቤትን ሲያይ፣ እግዚአብሔር ዝግጅትን ያያል። የሰው ዓይን ማዕበልን ሲያይ፣ እግዚአብሔር መጓጓዣን ያያል። የሰው ዓይን ጦርነትን ሲያይ፣ እግዚአብሔር መገለጥን ያያል።

ይህ የመንግሥቱ ምስጢር ነው። እግዚአብሔር እንደ ሰው አይመለከትም። መጽሐፍ ቅዱስ በ1ኛ ሳሙኤል 16፥7 “ሰው ፊትን ያያል፤ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል” ይላል። ሰው አሁን ያለውን ሁኔታ ያያል፤ እግዚአብሔር ግን የነገውን ክብር ያያል። ሰው የዛሬውን እንባ ያያል፤ እግዚአብሔር ግን የነገውን ምስክርነት ያያል።

በብዙ ጊዜ አማኞች እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር እንዳልሆነ የሚያስቡት በአደገኛ ስፍራ ውስጥ ሲገኙ ነው። ነገር ግን የቅዱሳት መጽሐፍ ምስክርነት ተቃራኒውን ይናገራል። ያዕቆብ በምድረ በዳ ብቻውን በድንጋይ ላይ ተኝቶ በነበረበት ሌሊት ሰማይ ተከፈተለት። ከእንቅልፉ በኋላ “እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ ነበረ፤ እኔ ግን አላወቅሁም” አለ። (ዘፍጥረት 28፥16)

አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር መገኘት በምቾት ስፍራ አይገለጥም፤ በሰው ጥንካሬ መጨረሻ ላይ ይገለጣል። ስለዚህ እግዚአብሔር ለጳውሎስ የተገለጠው በመርከቡ ላይ ሁሉም ተስፋ በተቆረጠበት ሌሊት ነበር። የሐዋርያት ሥራ 27፥20 እንደሚናገረው “ወደ ፊት እንድናለን የማለት ተስፋ ሁሉ ተቈረጠ።” ነገር ግን በዚያው ሌሊት መልአኩ መጣ።

አስተውሉ! መገለጡ የመጣው ከማዕበሉ በኋላ አይደለም፤ በማዕበሉ መካከል ነው። ተስፋው የመጣው ነፋሱ ከቆመ በኋላ አይደለም፤ ነፋሱ በሚነፍስበት ጊዜ ነው።

ይህ የሚያስተምረን ታላቅ እውነት ነው። መንፈስ ቅዱስ የሚሠራው በሰው አቅም ብቻ አይደለም፤ በሰው ድካምም ውስጥ ይሠራል። 2ኛ ቆሮንቶስ 12፥9 “ኃይሌ በድካም ይፈጸማል” ይላል።

ስለዚህ አንዳንድ ጊዜ የምታለቅሰው ስፍራ የሚቀባህ ስፍራ ነው። የምትጨነቅበት ስፍራ የምትለወጥበት ስፍራ ነው። የምትፈተንበት ስፍራ የምትዘጋጅበት ስፍራ ነው።

ዮሴፍ በጉድጓድ ውስጥ ሳለ ዙፋኑን አላየም፤ እግዚአብሔር ግን ያየው ነበር። ዳዊት ከሳኦል ሲሸሽ መንግሥቱን አላየም፤ እግዚአብሔር ግን ያየው ነበር። አስቴር ወደ ንግሥና ስትገባ ሕዝቧን ለማዳን እንደምትጠራ አላወቀችም፤ እግዚአብሔር ግን አውቆ ነበር።

ስለዚህ ዛሬ ያለህበትን ስፍራ ብቻ አትመዝን። እግዚአብሔር በሕይወትህ ላይ እየሠራ ያለውን ነገር በአሁኑ ሁኔታ ብቻ ማወቅ አትችልም። ምክንያቱም እርሱ “መጨረሻውን ከመጀመሪያው ይናገራል” (ኢሳይያስ 46፥10)።ስለዚህ ሰሙኝ የእግዚአብሔር ህዝቦች እህቴ ወንድሜ እናት እና አባቶቼ

አደገኛው ስፍራ የታሪካችን መጨረሻ አይደለም፤ የእግዚአብሔር ቀጣይ ምዕራፍ መግቢያ ነው።

በእውነት ቃል መጽናት            “ቃልህ እውነት ነው።”                       — ዮሐንስ 17፥17 🚩እሮብ ግንቦት 19 /2018 በመንግስቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲ...
12/05/2026

በእውነት ቃል መጽናት
“ቃልህ እውነት ነው።”
— ዮሐንስ 17፥17
🚩እሮብ ግንቦት 19 /2018
በመንግስቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን ከማለዳው 3:00 እስከ 11:00 ሰአት በስልጠና እለት ለሰልጣኞች በእለቱ የሻይ እና በምሳ ሰአት ማዕድን በጋራ የምንካፈልበት ፕሮግራም ይኖረናል

🚩የመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
ከ Gospel of the Son Apologetics International Ministry ጋር በመተባበር፣
በቤተክርስቲያኗ ስር የሚከተሉትን የስልጠና መርሃ ግብሮች ለማካሄድ ዝግጅት አድርጓል።

📚 የስልጠና ርእሰ ጉዳዮች

1. የቃል እምነት እንቅስቃሴና ያሳደረው ተጽእኖ
2. የጴንጤቆስጤ ነገረ መለኮት በኢትዮጵያ አውድ
3. ዕቅበተ እምነትና የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን

ይህ ስልጠና ከ ኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አቢያተክርስቲያናት ኅብረት ጋር በመተባበር ለወጣቶችና ለአገልጋዮች የሚሰጥ ይሆናል።

📖 የስልጠና መሠረታዊ የእምነት ጭብጦች

* ትምህርተ ሥላሴ
* ትምህርተ ክርስቶስ
* ትምህርተ ድነት
* ትምህርተ ቤተክርስቲያን
* የመጽሐፍ ቅዱስ መጨረሻዊ ባለሥልጣንነት

👉 እነዚህን መሠረታዊ የወንጌላውያን አስተምህሮዎች የሚያከብሩ ነባርና አዳዲስ ቤተእምነቶች በሙሉ ለመሳተፍ የተጋበዛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን።

እንዲሁም በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ኅብረት ውስጥ ወይም በተለያዩ ቤተእምነቶች ስር ያላችሁ ሆናችሁ ይህንን ስልጠና ለማግኘት ፍላጎት ያላችሁ ሁሉ በውስጥ መስመር እንድታገኙን በአክብሮት እንጠይቃለን።

የጌታ ኢየሱስ ፀጋ እና ሰላም ከእናንተጋር ይሁን

የመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
ከ Gospel of the Son Apologetics International Ministry ጋር በመተባበር።

🙏የመንግስቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን አድራሻ፡-ታክሲ ወይም አውቶቡስ ለምትይዙ

ከአራት ኪሎ ታክሲ ተራ ቤላ ታክሲ በመሳፈር ቤላ አስራ አስራ ስምንት ማዞሪያ ወደ አቦ በሚወስደው መንገድ 200 ሜትር ዳገቱን እንደወጡ በስተግራ በኩል ያገኙናል !
Our church Address Gps
Taxi 🚖 ride|| taxi 🚕

https://maps.app.goo.gl/26Gu8Y9VFS8eCi96A?g_st=it
የቤተክርስቲያን ስልክ
ለበለጠ -መረጃ
+251944723090
+251944723091
+251944723092
+251944723093

www.thegospelofkingdom.org

🚩ኑ በ4 ኪሎ ቤላ 18 ማዞሪያ ሲደርሱ ይውረዱ የመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን

Gps location just click
https://maps.app.goo.gl/ks7RCA2krKzB9kjZ8?g_st=ic https://youtu.be/H55Lsr2hGz4?si=E-co1cpkBSH70lfz

09/05/2026












መዝሙር 107፥20“ቃሉን ላከ፣ ፈወሳቸውም፣ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።”ድንቅ የፈውስ እና የበረከት የአምልኮ ጊዜ ✨📅 የፊታችን እሁድ ግንቦት 2/2018📍 በመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክር...
09/05/2026

መዝሙር 107፥20
“ቃሉን ላከ፣ ፈወሳቸውም፣ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።”

ድንቅ የፈውስ እና የበረከት የአምልኮ ጊዜ ✨

📅 የፊታችን እሁድ ግንቦት 2/2018
📍 በመንግሥቱ ወንጌል አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን ከማለዳው 12:00 ጀምሮ

ድንቅ የጌታ እጅ የሚገለጥበት፣
የፈውስ፣ የነፃነት እና የበረከት ታላቅ ጊዜ ይሆናል።

🙏 ሁላችሁም በክርስቶስ ፍቅር ተጋብዘዋል
🔥 የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ እና የፈውስ ኃይል ይገለጣል
🎶 በተጋባዥ ዘማሪያን የአምልኮ ጊዜ ይኖረናል

⸝

📖 “ጌታን እናመልከዋለን ይፈውሰናል እና ይባርከናል !

🇿🇦GOD HATES XENOPHOBIA“Do not mistreat or oppress a foreigner, for you were foreigners in Egypt.”— Exodus 22:21✋STOP AFR...
30/04/2026

🇿🇦GOD HATES XENOPHOBIA
“Do not mistreat or oppress a foreigner, for you were foreigners in Egypt.”
— Exodus 22:21

✋STOP AFRICA-TO-AFRICA VIOLENCE
NO MORE KILLING OF INNOCENT CIVILIANS

LOVE THE STRANGER. HONOR HUMANITY.
REJECT HATE. REFLECT CHRIST. WELCOME THE STRANGER.

ONE AFRICA. ONE PEOPLE. ONE FUTURE.
CHOOSE UNITY. CHOOSE HUMANITY.

• God hates hatred against strangers.
• God hates oppression of foreigners.
• God hates injustice, racism, and xenophobia.
• “Do not mistreat or oppress a foreigner.” – Exodus 22:21
• “Love the foreigner as yourself.” – Leviticus 19:34
• “God shows no favoritism.” – Acts 10:34

GOD HATES XENOPHOBIA Exodus 22:21
LOVE THE STRANGER. HONOR HUMANITY.






እንኳን ለእግዚአብሔር ታላቅ የድኅነት ሥራ—የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም በደስታ፣ በኃይል እና በሙሉ እምነት በሰላም አደረሳችሁ፤ ይህ ቀን የድል ቀን ነው፣ የሞት መሸ...
11/04/2026

እንኳን ለእግዚአብሔር ታላቅ የድኅነት ሥራ—የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም በደስታ፣ በኃይል እና በሙሉ እምነት በሰላም አደረሳችሁ፤ ይህ ቀን የድል ቀን ነው፣ የሞት መሸነፍ እና የሕይወት መነሳት ምልክት፤ እንግዲኛ በእርሱ ውስጥ አዲስ ሕይወት እንኖራለን፣ በተስፋ እና በፍቅር እንመራለን፣ ክርስቶስ ተነስቶአል፣ እውነት ተነስቶአል!

የእግዚአብሔር ሰው ነብይ ኤርሚያስ ሁሴን በሰጡት መግለጫ ይህን መልክት አስተላልፈዋል
|| ትንሳኤ ||የክርስቲያን እምነት የወንጌል ልብ ነው።
ክርስቶስ መሞቱ ብቻ አይደለም፣ ከሙታን በኩር ሆኖ መነሣቱ ጭምር እምነታችንን የሚያጸና ነው።

📖 “ክርስቶስ ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ነው” (1 ቆሮንቶስ 15:17)

http://bit.ly/jesustvethiopiaመንፈሶን የሚመግቡ አዳዲስ የአምልኮ፤የተከታታይ ትምህርቶች፤ስብከቶች እንዲሁም አስድናቂ ምስክርነቶች በየቀኑ እንዲድረሶት አሁኑኑ ሰብስክራይብ ያድርጉ http://bit.ly/j...

Address

Yeka Sub City Woreda 03 House Nember 452
Addis Ababa
57584

Telephone

251944723090

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jesus TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share