የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት Saint kirkos church

በግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. የጠቅላላ ጉባኤ ተከናወነየጠቅላላ ጉባኤው ሰብሳቢ በሆነው በዲያቆን ጥላዬ አያሌው መሪነት በወርሃዊ ጸሎት መርሐግብሩ የተጀመረ ሲሆን በማስከተልም የዕለቱ ስን...
26/05/2026

በግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. የጠቅላላ ጉባኤ ተከናወነ

የጠቅላላ ጉባኤው ሰብሳቢ በሆነው በዲያቆን ጥላዬ አያሌው መሪነት በወርሃዊ ጸሎት መርሐግብሩ የተጀመረ ሲሆን በማስከተልም የዕለቱ ስንክሳር የተነበበ ሲሆን እንዲሁም የጋር የህብረት ዝማሬ ተዘምረዋል።

በማስከተልም የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ በሆኑት በላዕከ ሄራን መንክር ግርማ በኢ/ኦ/ተ/ቤክ /ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች የማስፈጸሚያ ሰነድን በተመለከተ
➽ የተዘጋጀበትን ምክንያት
➽ የትኩረት አቅጣጫዎችን
➽ ስለ ጠቅላላ ጉባዔ
➽ ስለ አባላት አገልግሎት ማዕቀፍ
➽ ሰ/ት/ቤቶች ራሳቸውን ስለሚለኩባቸው 10 መስፈርቶች
➽ ስለ ምድብ አንድ ሰ/ትቤት አደረጃጀት
➽ ለሰ/ት ቤት ስለተሰጡ መብቶች እና ስለ አስመራጭ ምርጫ ማስፈጸሚያ መመሪያው ሰፊ ገለጻን አቅርበዋል ሲሆን በመቀጠልም ከሰንበት ት/ቤታችን አባላት ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በተጨማሪም ለተነሱ ስጋቶች ዋናው መፍትሄ ከአንድነቱ ጋር በመነጋገር መስራት መሆኑን ያወሱ ሲሆን በተሻለ ተቀራርበን ብንሰራ ለነገዋ ቤተክርስቲያን ውጤታማ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

አደረጃጀቱን በተመለከተ እንዲያጠኑት ሰ/ት/ቤቱ አስቀድሞ ያዋቀራቸውን አምስቱን አገልጋዮች ቢኒያም አበራ ፣ ዘካርያስ ክፍሌ ፣ ድርሻዬ ተሰማ ፣ ብሥራት ኃይሌ እና ኤፍራታ ከተማ በድጋሚ እንዲያዩት እና ከማደራጃው ጋር እየተነጋገሩ በአባሉ ያለውን ስጋት እንዲያቀሉ ጠቅላላ ጉባኤው ኃላፊነት ሰቷል።

በማስከተልም ከቂርቆስ ልደታ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነትን ወክለው በተገኙ ተወካዮች መሪነት የሰንበት ት/ቤታችን የአመራር ምርጫ የሚያስፈጽሙ አስመራጭ የመምረጥ ተግባር ሲሆን በምርጫውም
፩. ጤናዬ ደገፉ
፪. አዜብ ኢሳያስ
፫. ቢንያም ዘመዴ
፬. ደሳለኝ ከድር
፭. ጥሩነህ አለማርዬ ሆነው ሲመረጡ
በተጠባባቂነት
፩. ኤፍራታ ከተማ
፪. መ/ር ሰይፈ ጋረደው
፫. ደምሴ ኃ/ማርያም ሆነው ተመርጠው መርሐ ግብሩም በጸሎት ተጠናቋል።

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

ዜና ውሉደ ብርሃንየሰንበት ትምህርት ቤታችን ቅዱስ ቂርቆስ አዳጊዎች ማዕከል ግንቦት 16 ቀን  2018 ዓ.ም የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች የሆኑ 96 ያህል ተማሪዎችን በአዲስ አበባ ማህበረ ቅዱሳ...
25/05/2026

ዜና ውሉደ ብርሃን

የሰንበት ትምህርት ቤታችን ቅዱስ ቂርቆስ አዳጊዎች ማዕከል ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች የሆኑ 96 ያህል ተማሪዎችን በአዲስ አበባ ማህበረ ቅዱሳን የስነ ስዕል ጉብኝት እንዲሁም በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በዓታ ለማርያም ገዳም እና ደብረ መንክራት ሥዕል ቤት ኪዳነ ምህረት ቤተ- ክርስቲያን የሙዚየም ጉብኝት አድርገዋል።

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

ልዩ የመጻሕፍት ሳምንት👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok
25/05/2026

ልዩ የመጻሕፍት ሳምንት

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

የሕይወት ቃል👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok
24/05/2026

የሕይወት ቃል

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

ቅዳሴ👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok
23/05/2026

ቅዳሴ

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

ዜና ውሉደ ብርሃንየሰንበት ትምህርት ቤታችን ቅዱስ ቂርቆስ አዳጊዎች ማዕከል  የ2018ዓ.ም የዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች ግንቦት 9 ቀን በሕጻናት ልጆች ክፍለ ...
20/05/2026

ዜና ውሉደ ብርሃን

የሰንበት ትምህርት ቤታችን ቅዱስ ቂርቆስ አዳጊዎች ማዕከል የ2018ዓ.ም የዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች ግንቦት 9 ቀን በሕጻናት ልጆች ክፍለ ጊዜ እና በማዕከላውያን ቋሚ መዘምራን የምስጋና መርሃ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ አልፏል።

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

ግንቦት 11 በዓሉ ለቅዱስ ያሬድ ማሕሌታይ" ከመ ተሰወርከ ያሬድ እምቅድመ ዓይኑ ለሞት አድህነነ በጸሎትከ እምእለተ እኪትወባለሐነ እምኩሉ መንሱት"ቅዱስ ያሬድ ሆይ ከሞት ፊት እንደተሰወርክ ሁ...
19/05/2026

ግንቦት 11 በዓሉ ለቅዱስ ያሬድ ማሕሌታይ

" ከመ ተሰወርከ ያሬድ እምቅድመ ዓይኑ ለሞት
አድህነነ በጸሎትከ እምእለተ እኪት
ወባለሐነ እምኩሉ መንሱት"

ቅዱስ ያሬድ ሆይ ከሞት ፊት እንደተሰወርክ ሁሉ በጸሎትህ እኛን ከክፉ ቀን እና ከክፉ ነገር አድነን

የቤተ ክርስቲያን ጌጥ የዜማ አባት የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የቅኔ እና የሥነ መለኮት ሊቅ ማሕሌታይ ቅዱስ ያሬድ ደብረ ሐዊ በተባለ ቅዱስ መካን በምናኔ ለብዙ ዘመን ከኖረ በኃላ ሞት ሳይቀምስ በሰባ አምስት አመቱ የተሰወረው ግንቦት 11 ቀን ነው

በገድለ ቅዱስ ያሬድ ተጽፎ እንደምናገኘው በዘመኑ የነበሩ ሁሉ እንደ መበረቅ የሚደምቅ፣ ምሥጢሩ እንደ መስታወት የሚያንጸባርቅ ጥበብ የተሞላበትን ድንቅ ዜማውን ለመስማት ከህጻናት እስከ ንጉሡ ድረስ ይከቡት የነበረ ማሕሌታይ ነው

" ንጉሥ ገብረ መስቀል ይህን ታላቅ ጣዕም ያለው ዜማ በሰማ ጊዜ ጫማውን ከእግሩ አልጨመረም ንግሥቲቱም አገልጋዮቿን ተወች ያንን ጥዑም ዜማ ትሰማ ዘንድ በአንድነት ሮጡ ጳጳሳት ካህናት የቤተ መንግሥቱ ወይዛዝርት ሹማምንት ወደ ቅዱስ ያሬድ መጡ ሲሰሙት ዋሉ፤ ከድምፀ ቃናው ጣዕም የተነሣ አጥንትን የሚያለመልም ልቡናን የሚያስደስት ነገር አግኝተዋልና፤ የቃሉን ድምፅ በሰሙ ጊዜ ሮጡ ወደ እርሱ ደረሱ ንጉሡም ንግሥቲቱም ከካህናቱ ጋር፣ ከመንግሥት ሹማምንትና ከሕዝቡ ጋር በመኾን ሲያዳምጡት ዋሉ›› እንዲል ገድለ ቅዱስ ያሬድ

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ የክብርህ ምስጋና ሰማያትንና ምድርን የመላ ነው እያሉ በስማይ ከሚኖሩ ከቅዱሳን መላእክት የሰማሁት ዜማ ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ እንደምን ያለ ረቂቅ ነው ለዚህ አንክሮ ይገባል እያለ በምስጋና ሥርዓታቸው ሲደነቅባቸው ከነበሩ ከቅዱሳን መላእክት ጋራ ሊያመስገን ከዚህ ዓለም መከራ እና ድካም ሊያርፍ ሞትን ሳይቀምስ ተሰወረ በድርሣነ ቅዱስ ዑራኤል የስኔ ወር ምንባብ ላይ " ከሰው ዓይን ተሰወረ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ " እንዲል

ተዓምረ ኢየሱስ የተሰኘው የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍም

" ካህኑ ያሬድ ከዚህ ዓለም የሚለይበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዓት እንድታይ እና ወደ ምድር አስተላልፈህ ይህንኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኩ ሁሉ አሁንም ከዚህ ዓለም በምትለይበት ሰዓት እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሳቸው ህጻናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊል እና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልሃል ብሎት ወደ ሰማይ ዐረገ " ሲል ሞትን ሳይቀምስ መሰወሩን ይገልጻል

+ የቅዱስ ያሬድ በረከት በሁላችን ይደር በምልጃው ሀገራችንን ከክፉ ነገር ይሰውርልን

ምንጭ: ፍቁረ እግዚእ ሚድያ

ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉለሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ በወረደለት መመሪያ መሰረት፤ ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች መዋቅር በሰንበት ትምህርት ቤቶች አቅም ...
18/05/2026

ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ

ለሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ በወረደለት መመሪያ መሰረት፤ ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች መዋቅር በሰንበት ትምህርት ቤቶች አቅም ልክ ወደ ትግበራ እያስገባ መሆኑ ይታወቃል።

ሰንበት ትምህርት ቤታችንም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የሚተገበረውን የአንድነቱን መዋቅር እና ዝርዝር ሁኔታውን በተመለከተ ከኅብረቱ በሚመደቡ አሰልጣኞች ስልጠናው የፊታችን እሁድ የሚሰጥ ይሆናል።

ሥልጠናውን በመውሰዳችን
1) ስለምንተገብረው መዋቅር በቂ ግንዛቤ እናገኛለን
2) ያልገቡን ግልጽ ያልሆኑልን ጥያቄዎች ከሥልጠናው በኋላ በሚኖር ውይይት ምላሽ ይሰጥባቸዋል
3) መዋቅሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ የወረደ እንደመሆኑ የክፍሎች አደረጃጀትና መሠል ጉዳዮች ከለመድነው ውጪ አዲስ ነገር ይዞ ስለሚመጣ እኛ ተረድተን በቀጣይ ለምንመራው አገልጋይ በበቂ ሁኔታ ለማስረዳት በር ይከፍታል።

ማሳሰቢያ

👉 ውድ አባላት በጠቅላላ ጉባኤው ላይ መገኘት ውዴታ ሳይሆን ግዴታ ነው።
👉 ከተላከው ሰነድ ውስጥ በተቻለ መጠን ከገጽ 1-46 ያለውን በጥልቀት አንብባችሁ እንድትገኙ።

ማስታወሻ፡ ሰነዱን ለማግኘት ከስር በተቀመጠው የቴሌግራም ሊንክ በመግባት ማግኘት እንደምትችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/weludebirhan

የእሑድ ጉባኤ ግንቦት ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተከናውኗልየዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት የተጀመረ ሲሆን በእለቱም ስንክሳር ከተነበበ በኋላ፤ በሰ/ት/ቤቱ መዘምራን ወረብ ቀርቧል፤ በእለቱም በተጋባዥነት ...
17/05/2026

የእሑድ ጉባኤ ግንቦት ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተከናውኗል

የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት የተጀመረ ሲሆን በእለቱም ስንክሳር ከተነበበ በኋላ፤ በሰ/ት/ቤቱ መዘምራን ወረብ ቀርቧል፤ በእለቱም በተጋባዥነት በዘማሪ ብሌን ታምሩ ዝማሬ ከተዘመረ በኋላ፤ በመቀጠልም የእለቱን ትምህርተ ወንጌል በመምህር ዲያቆን ሰይፈ ጋረደው "ክርስቶስን መምሰል" በሚል ርዕስ ተሰጥቶ፤ በመጨረሻም ጉባኤው በፀሎት ተዘግቷል፡፡

ውድ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ የእሑድ ጉባኤ የሚዘጋጀው ለሁላችንም ስለሆነ ጉባኤውን በመሳተፍ እራሳችንን በእግዚአብሔር ቃል እናንፅ፡፡

👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok

“ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡”          ሃይማኖተ አበው  ዘስምዓትበዛሬው ዕለት...
17/05/2026

“ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡”

ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት

በዛሬው ዕለት ግንቦት ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም. በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ጋብቻችሁን የፈጸማችሁትን የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ወንድማችን በሱፍቃድ ሸዋለማ እና እህታችን ማህደር መቅጫ የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ።

መልካም ምኞት ይመኛሉ የውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251953853535

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት:

Share