26/05/2026
በግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. የጠቅላላ ጉባኤ ተከናወነ
የጠቅላላ ጉባኤው ሰብሳቢ በሆነው በዲያቆን ጥላዬ አያሌው መሪነት በወርሃዊ ጸሎት መርሐግብሩ የተጀመረ ሲሆን በማስከተልም የዕለቱ ስንክሳር የተነበበ ሲሆን እንዲሁም የጋር የህብረት ዝማሬ ተዘምረዋል።
በማስከተልም የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ በሆኑት በላዕከ ሄራን መንክር ግርማ በኢ/ኦ/ተ/ቤክ /ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች የማስፈጸሚያ ሰነድን በተመለከተ
➽ የተዘጋጀበትን ምክንያት
➽ የትኩረት አቅጣጫዎችን
➽ ስለ ጠቅላላ ጉባዔ
➽ ስለ አባላት አገልግሎት ማዕቀፍ
➽ ሰ/ት/ቤቶች ራሳቸውን ስለሚለኩባቸው 10 መስፈርቶች
➽ ስለ ምድብ አንድ ሰ/ትቤት አደረጃጀት
➽ ለሰ/ት ቤት ስለተሰጡ መብቶች እና ስለ አስመራጭ ምርጫ ማስፈጸሚያ መመሪያው ሰፊ ገለጻን አቅርበዋል ሲሆን በመቀጠልም ከሰንበት ት/ቤታችን አባላት ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በተጨማሪም ለተነሱ ስጋቶች ዋናው መፍትሄ ከአንድነቱ ጋር በመነጋገር መስራት መሆኑን ያወሱ ሲሆን በተሻለ ተቀራርበን ብንሰራ ለነገዋ ቤተክርስቲያን ውጤታማ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
አደረጃጀቱን በተመለከተ እንዲያጠኑት ሰ/ት/ቤቱ አስቀድሞ ያዋቀራቸውን አምስቱን አገልጋዮች ቢኒያም አበራ ፣ ዘካርያስ ክፍሌ ፣ ድርሻዬ ተሰማ ፣ ብሥራት ኃይሌ እና ኤፍራታ ከተማ በድጋሚ እንዲያዩት እና ከማደራጃው ጋር እየተነጋገሩ በአባሉ ያለውን ስጋት እንዲያቀሉ ጠቅላላ ጉባኤው ኃላፊነት ሰቷል።
በማስከተልም ከቂርቆስ ልደታ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነትን ወክለው በተገኙ ተወካዮች መሪነት የሰንበት ት/ቤታችን የአመራር ምርጫ የሚያስፈጽሙ አስመራጭ የመምረጥ ተግባር ሲሆን በምርጫውም
፩. ጤናዬ ደገፉ
፪. አዜብ ኢሳያስ
፫. ቢንያም ዘመዴ
፬. ደሳለኝ ከድር
፭. ጥሩነህ አለማርዬ ሆነው ሲመረጡ
በተጠባባቂነት
፩. ኤፍራታ ከተማ
፪. መ/ር ሰይፈ ጋረደው
፫. ደምሴ ኃ/ማርያም ሆነው ተመርጠው መርሐ ግብሩም በጸሎት ተጠናቋል።
👉ለቤተሰብ ለወዳጅ ያጋሩ👈
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Youtube | Facebook | Telegram | Tiktok