30/08/2025
(ከሶስት አመት በፊት ለቅዱሳን ለንባብ የቀረበ)
✍✍የደረስኩበት ✍✍
ምዕራፍ አንድ
ክፍል 6: ወንጌል በገጠር
ማታ ቤት እንደገባሁ ውዳ ባለቤቴ "ከሰሞኑ በዚህ ቴሌግራም እየተፃፉ ያሉትን ፅሁፎች እያነበብኩ ነዉ። ምን እንደ ምታወሩ አልገባኝም። አንተም ይህን ያክል ትኩረት የሰጠኸዉ ለምንድነዉ? የምትፈልገዉስ በግልፅ አማርኛ ምንድነዉ?" በማለት ጠየቀችኝ። ከሁኔታዋ ምን እነደሆነ ባለውቅም ስጋት አይነት ነገር ይነበባል። እኔም የምፈልገውን ረጋ በማለት እንዲህ ገለፅኩላት።
🏆🏆እኔ የምፈልገዉ በጉራጌ ምድር ተሀድሶ ይመጣ ዘንድ ነው። በቃ ይኸው ነው።🏆🏆
እኛ ስለዳንን አትይ ። ጉራጌ ምድር ዛሬም በጨለማ ነው ያለችው። ከጠቅላላው ጉራጌ ህዝብ የአማኞች ቁጥር 2% አይሞላም። ወንጌል አልደረሰም። እንደሚታወቀዉ አብዛኛው ህዝባችን ያለው አዲስ አበባ ነዉ።
የተማረው፣ ባለሀብቱ፣ ባለልዩ ፀጋው፣ ወጣቱ... እዚህ ነው።
ሁሉም ከተማ ያለ አማኝ በተወለደበት አካባቢ በምትገኝ አጥቢያ ቤተክርስቲያን በኩል የተቻለውን ለማድረግ እየጣረ ነው። በተጨማሪም እያንዳንዱ አማኝ እንደ ጉራጌ ወንጌል መስራት ይፈልጋል ። እስቲ ማነው ከእኛ ከሞቸያ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሞህር ወይም ጌቶ ላይ ወንጌል እንዲሰራ የማይፈልገው? እርግጠኛ ነኝ ማንም የለም።
ችግሩ ግን መንገድ የለም፤ የሚያስተባብር የለም። መንገድ መሆን የተገባው ተቋም ወንጌል በገጠር አገልግሎት ነበር። ግን ያ ማድረግ አልቻለም።
ወንጌል የሚሰራዉ በየዋህነት ነዉ ብለሽ ልስራ ብለሽ ብትንቀሳቀሺና ሁለት ሶስት ሆነሽ መንገድ ብትጀምሪ ወልቂጤ ሳትደርሺ እዚህ ያሉ ከእኔ ውጪ የሚሉ አመፀኛ ሰዎች ይደውልና ወንጌል በገጠር አያውቃቸውም አትቀበሏቸው ብሎ ከመንገድ ያስመልስሻል። ትንሽ ጠንካራ ካልሆንሽ ተሰባብረሽ ትቀሪአለሽ።
እናም ይህ የሚቀየርበት መንገድ መፈጠር አለበት።
ሌላውና ዋናው ነገር ሁሉንም የጉራጌ አብያተ ክርስቲያን የሚያስተሳስር አንድ ጠንካራ ተቋም የለንም።ይህ ተቋም ወንጌል በገጠር መሆን ነበረበት። አባቶች ሲመሰርቱት አላማቸዉ ይህ ነበር። ግን ይህ አልሆነም።
ሁሉም የጉራጌ የአጥብያ የከተማ ህብረት በንቃት የሚሳተፍበትና የሚወስንበት መንገድ መፈጠር አለበት። ለምሳሌ ለአስር አመታት የከተማ ህብረት የመሩ የቤተ ክርስትያናችን መሪዎች አንዳቸዉም ስለወንጌል በገጠር እንቅስቃሴ አያውቁም። ይህ ደሞ ለመላዉ ጉራጌ ተመሳሳይ ነዉ።
ያለፉት ዘመናት እኮ ቤተ ክርስትያን በጦርነት ነዉ ያሳለፈችዉ። አጥቢያ ከአጥቢያ፣ ግለሰብ ከአጥቢያ፣ ግለሰብ ከግለሰብ መላው የጉራጌ አብያተ ክርስቲያ ሲተራመሱ ነዉ የኖሩት። እርቅ ከባድ ሆኖ ይመስልሻል? እኔ አይመስለኝም።
ድቅል አመለካከት ያላቸዉ ጥቂት ሰዎች ከቀበሌ የወረሱት የከፋፍለህና የአታራምሰህ እራስህ ጥቀም አስተሳሰብ ነዉ። ቢያንስ የእርስ በርስ የትዉዉቅ መድረክ በዚህ ዘመን ሁሉ አይዘጋጅም። ጥቂት በስራ ጉዳይ ከሚተዋወቁት በስተቀር ማንም ከማንም ሳይተዋወቅ ነዉ ለዘመናት የኖረዉ።
ይህ ደግሞ ለወንጌል ከፍተኛ ማነቆ ሆኗል ። መለወጥ አለበት። በቃ ይኸዉ ነዉ ምፈልገው። እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን በጥቂት ሰዎች የተጠፈነገው ሰነሰለት ይበጣጥስና አንድ መላው የጉራጌ ቅዱሳን የሚያስተባብር ግዙፍ ተቋም እንገነባለን። ያም ተቋም አሁን ደብዛው የጠፋው ወንጌል በገጠር አገልግሎት ይሆናል።
መጋቢት 08/ 2017 ዓ.ም
Habtamu A.