ቁጥር አንድ ወንጌል በገጠር የፍቅር አገልግሎት

ቁጥር አንድ ወንጌል በገጠር የፍቅር አገልግሎት “ኢየሱስም ወደ ቤትህ በቤተ ሰዎችህ ዘንድ ሄደህ ጌታ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገልህ እንዴትስ እንደ ማረህ አውራላቸው አለው።” ማር 5፥19

30/08/2025


(ከሶስት አመት በፊት ለቅዱሳን ለንባብ የቀረበ)

✍✍የደረስኩበት ✍✍

ምዕራፍ አንድ
ክፍል 6: ወንጌል በገጠር

ማታ ቤት እንደገባሁ ውዳ ባለቤቴ "ከሰሞኑ በዚህ ቴሌግራም እየተፃፉ ያሉትን ፅሁፎች እያነበብኩ ነዉ። ምን እንደ ምታወሩ አልገባኝም። አንተም ይህን ያክል ትኩረት የሰጠኸዉ ለምንድነዉ? የምትፈልገዉስ በግልፅ አማርኛ ምንድነዉ?" በማለት ጠየቀችኝ። ከሁኔታዋ ምን እነደሆነ ባለውቅም ስጋት አይነት ነገር ይነበባል። እኔም የምፈልገውን ረጋ በማለት እንዲህ ገለፅኩላት።

🏆🏆እኔ የምፈልገዉ በጉራጌ ምድር ተሀድሶ ይመጣ ዘንድ ነው። በቃ ይኸው ነው።🏆🏆

እኛ ስለዳንን አትይ ። ጉራጌ ምድር ዛሬም በጨለማ ነው ያለችው። ከጠቅላላው ጉራጌ ህዝብ የአማኞች ቁጥር 2% አይሞላም። ወንጌል አልደረሰም። እንደሚታወቀዉ አብዛኛው ህዝባችን ያለው አዲስ አበባ ነዉ።

የተማረው፣ ባለሀብቱ፣ ባለልዩ ፀጋው፣ ወጣቱ... እዚህ ነው።

ሁሉም ከተማ ያለ አማኝ በተወለደበት አካባቢ በምትገኝ አጥቢያ ቤተክርስቲያን በኩል የተቻለውን ለማድረግ እየጣረ ነው። በተጨማሪም እያንዳንዱ አማኝ እንደ ጉራጌ ወንጌል መስራት ይፈልጋል ። እስቲ ማነው ከእኛ ከሞቸያ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሞህር ወይም ጌቶ ላይ ወንጌል እንዲሰራ የማይፈልገው? እርግጠኛ ነኝ ማንም የለም።

ችግሩ ግን መንገድ የለም፤ የሚያስተባብር የለም። መንገድ መሆን የተገባው ተቋም ወንጌል በገጠር አገልግሎት ነበር። ግን ያ ማድረግ አልቻለም።

ወንጌል የሚሰራዉ በየዋህነት ነዉ ብለሽ ልስራ ብለሽ ብትንቀሳቀሺና ሁለት ሶስት ሆነሽ መንገድ ብትጀምሪ ወልቂጤ ሳትደርሺ እዚህ ያሉ ከእኔ ውጪ የሚሉ አመፀኛ ሰዎች ይደውልና ወንጌል በገጠር አያውቃቸውም አትቀበሏቸው ብሎ ከመንገድ ያስመልስሻል። ትንሽ ጠንካራ ካልሆንሽ ተሰባብረሽ ትቀሪአለሽ።

እናም ይህ የሚቀየርበት መንገድ መፈጠር አለበት።

ሌላውና ዋናው ነገር ሁሉንም የጉራጌ አብያተ ክርስቲያን የሚያስተሳስር አንድ ጠንካራ ተቋም የለንም።ይህ ተቋም ወንጌል በገጠር መሆን ነበረበት። አባቶች ሲመሰርቱት አላማቸዉ ይህ ነበር። ግን ይህ አልሆነም።

ሁሉም የጉራጌ የአጥብያ የከተማ ህብረት በንቃት የሚሳተፍበትና የሚወስንበት መንገድ መፈጠር አለበት። ለምሳሌ ለአስር አመታት የከተማ ህብረት የመሩ የቤተ ክርስትያናችን መሪዎች አንዳቸዉም ስለወንጌል በገጠር እንቅስቃሴ አያውቁም። ይህ ደሞ ለመላዉ ጉራጌ ተመሳሳይ ነዉ።

ያለፉት ዘመናት እኮ ቤተ ክርስትያን በጦርነት ነዉ ያሳለፈችዉ። አጥቢያ ከአጥቢያ፣ ግለሰብ ከአጥቢያ፣ ግለሰብ ከግለሰብ መላው የጉራጌ አብያተ ክርስቲያ ሲተራመሱ ነዉ የኖሩት። እርቅ ከባድ ሆኖ ይመስልሻል? እኔ አይመስለኝም።

ድቅል አመለካከት ያላቸዉ ጥቂት ሰዎች ከቀበሌ የወረሱት የከፋፍለህና የአታራምሰህ እራስህ ጥቀም አስተሳሰብ ነዉ። ቢያንስ የእርስ በርስ የትዉዉቅ መድረክ በዚህ ዘመን ሁሉ አይዘጋጅም። ጥቂት በስራ ጉዳይ ከሚተዋወቁት በስተቀር ማንም ከማንም ሳይተዋወቅ ነዉ ለዘመናት የኖረዉ።

ይህ ደግሞ ለወንጌል ከፍተኛ ማነቆ ሆኗል ። መለወጥ አለበት። በቃ ይኸዉ ነዉ ምፈልገው። እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን በጥቂት ሰዎች የተጠፈነገው ሰነሰለት ይበጣጥስና አንድ መላው የጉራጌ ቅዱሳን የሚያስተባብር ግዙፍ ተቋም እንገነባለን። ያም ተቋም አሁን ደብዛው የጠፋው ወንጌል በገጠር አገልግሎት ይሆናል።

መጋቢት 08/ 2017 ዓ.ም

Habtamu A.

   በመላው አለም ለምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወላጆችና ቤተሰቦች በሙሉአቶ ሀብታሙ አለሙጉዳዩ፦ ወደሚዲያ አገልግሎት መመለሴን ማሳወቅ ይሆናል!በመላው አለም የምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወ...
19/08/2025




በመላው አለም ለምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወላጆችና ቤተሰቦች በሙሉ

አቶ ሀብታሙ አለሙ

ጉዳዩ፦ ወደሚዲያ አገልግሎት መመለሴን ማሳወቅ ይሆናል!

በመላው አለም የምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወላጆችና ቤተሰቦች በያላችሁበት የከበረው ሰላምታዬን አቀርባለሁ። ከ8 ወራት በፊት ህዳር 21/2017 ዓ.ም በፃፍኩት ደብዳቤ ላለተወሰነ ጊዜ ከየትኛውም የጉራጌ ዞን አብያተክርስቲያናትና የወንጌል በገጠር አገልግሎት ዙሪያ የማቀርባቸው ፅሁፎችም ሆነ የድምፅ መልዕክቶች ሙሉ በሙሉ ለማቆም ወሰኔን ገልጫለሁ።

ለዚህም ዋነኛ ምክንያት የነበረው ላለፉት 4 ዓመታት በተደረገው ዞን አቀፍ የተሀድሶና የለውጥ እንቅስቃሴ የተገኘው ድል በጥሩ ሁኔታ መስመር ይዞ እየገሰገሰ በነበረበት ወቅት አንዳንድ ግለሰቦች የለውጡና የተሀድሶው እንቅስቃሴ ባለራዕዮችን ለማገለልና ለማጥቃት በማለም ሆነ ብለው ሂደቱን ለማደናቀፍ ሲያደርጉት የነበው ትንቅንቅ ስለተመለከትኩ ራዕዩ ከነችግሩም ቢሆን ዳር እንዲደርስ የእኔን ዝምታ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብዬ በማሰብ እንደሆነ ይታወሳል።

በጥልቀት የማውቃቸው ብዙ ያልተፈቱ፣ ያልተስተካከሉና ያልተሰሩ ስራዎች ቢኖሩም ፤መንፈሳዊ ያልሆኑ የአመፃና የክፍት ምክሮች ቢሰነጥሉም ከ4ዓመታት እልህ አስጨራሽ ጉዞ በኋላ ራዕያችን ከአንድ ሰው ወደ ሁለት ከሁለት ወደ ሶስት እያለ የመላው የጉራጌ ቅዱሳን ሆኖ ከማየት በላይ የሚያስደስት ነገር የለም!! ራዕዩ እግዚአብሔር ያስጀመረውና የመራው ስለነበር የእንቅስቃሴው ዋነኛ ምሰሶ የነበሩት ሁለት ጉዳዮች፦

1) የወንጌል በገጠር አገልግሎት የሚለው ስያሜ ማስመለስና
2) በሰባት ቤት የሚገኙ ሁሉንም ወረዳዎች፣ በየወረዳው የሚገኙ አብያተክርስቲያናት፣ በከተማ የተደራጁ ሁሉንም የአጥቢያ/አካባቢ ህብረቶች፣ የቀድሞ የወንጌል በገጠር መስራች አባቶችና መላው የጉራጌ ተወላጅ የሆኑ ቅዱሳ ያቀፈ ግዙፍ ተቋም መመስረት የሚሉትን በመሳካታቸው የድል ስሜት ይሰማኛል።

እነዚህ ሁለት ጉዳዮች የራዕዩ ማጠንጠኛዎችና ለዓመታት የታገልንባቸው ናቸውና ሆነው በማየቴ ደስታዬ ላቅ ያለ ነው። የእግዚአብሔር ስም የተመገነ ይሁን!!

መንገዳችን የሚመራው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ፣ ከእግዚአብሔር በተቀበልነው ራዕይ ምን እንደተሳካና ምን እንደሚቀር ጠንቅቀን ስለምናውቅ ስኬታችን በትክክል እንመዝናለን! እግዚአብሔር ባስጀመረን ጉዞ ያሳካናቸው ብዙ ናቸው። ያላሳካናቸውና የሚቀሩንም እንደዛው!

ቃሉ "ለሁሉም ጊዜ አለው"እንደሚለው ላለፉት ስምንት ወራት በአንድም በሌላ የለውጡና የተሀድሶው ራዕይ ገዝተው ለማስፈፀም የተሰማሩት የሰባት ቤት አብያተክርስቲያናት መሪዎችና በሂደቱ የተዋቀሩ ኮሚቴዎች ጉዞ በዝምታ መጠበቁ አስፈላጊ ነበር። ለዓመታት በተደጋጋሚ በድምፅና በፅሁፍ እንዳስቀመጥኩት የእነዚህ አካላት ጉዞ በትላንትና ዕለት ነሐሴ 11/2017 ዓ.ም ለህዝብ ቀርቧል። ስለፕሮግራሙ እግዚአብሔርን እያመሰገንኩ ከዛሬ ጀምሮ ባለፊት ዓመታት ያልተዳሰሱ ርዕሰ ጉዳዮችና እግዚአብሔር ከሰጠኝ ራዕይ ያልተጠናቀቁና ያልተሰሩ ስራዎችን በስፋት መዳሰስ እጀምራለሁ።

በመሆኑም በመላው አለም የምትገኙ አማኝ የጉራጌ ተወላጆችና ቤተሰቦች ለወራት ተቋርጦ የቆየውን መላው የጉራጌ ዞን አብያተክርስቲያናት እና የወንጌል በገጠር አገልግሎት የሚዳስሰውን የሚዲያ አገልግሎቴ ዳግም መጀመሬ ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው።

ስለዚህ ከነገ ጀምሮ በሁሉንም የማህበራዊ ሚድያ አማራጮች እንድትከታተሉኝ እየጋበዝኩ እግዚአብሔር በምድራችን ሊሰራ ያለውን ታላቅ የለውጥና የተሀድሶ ስራ አብረን እንድንሰራ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

19/08/2025




በመላው አለም ለምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወላጆችና ቤተሰቦች በሙሉ

አቶ ሀብታሙ አለሙ

ጉዳዩ፦ ወደሚዲያ አገልግሎት መመለሴን ማሳወቅ ይሆናል!

በመላው አለም የምትገኙ አማኝ የጉራጌ ዞን ተወላጆችና ቤተሰቦች በያላችሁበት የከበረው ሰላምታዬን አቀርባለሁ። ከ8 ወራት በፊት ህዳር 21/2017 ዓ.ም በፃፍኩት ደብዳቤ ላለተወሰነ ጊዜ ከየትኛውም የጉራጌ ዞን አብያተክርስቲያናትና የወንጌል በገጠር አገልግሎት ዙሪያ የማቀርባቸው ፅሁፎችም ሆነ የድምፅ መልዕክቶች ሙሉ በሙሉ ለማቆም ወሰኔን ገልጫለሁ።

ለዚህም ዋነኛ ምክንያት የነበረው ላለፉት 4 ዓመታት በተደረገው ዞን አቀፍ የተሀድሶና የለውጥ እንቅስቃሴ የተገኘው ድል በጥሩ ሁኔታ መስመር ይዞ እየገሰገሰ በነበረበት ወቅት አንዳንድ ግለሰቦች የለውጡና የተሀድሶው እንቅስቃሴ ባለራዕዮችን ለማገለልና ለማጥቃት በማለም ሆነ ብለው ሂደቱን ለማደናቀፍ ሲያደርጉት የነበው ትንቅንቅ ስለተመለከትኩ ራዕዩ ከነችግሩም ቢሆን ዳር እንዲደርስ የእኔን ዝምታ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብዬ በማሰብ እንደሆነ ይታወሳል።

በጥልቀት የማውቃቸው ብዙ ያልተፈቱ፣ ያልተስተካከሉና ያልተሰሩ ስራዎች ቢኖሩም ፤መንፈሳዊ ያልሆኑ የአመፃና የክፍት ምክሮች ቢሰነጥሉም ከ4ዓመታት እልህ አስጨራሽ ጉዞ በኋላ ራዕያችን ከአንድ ሰው ወደ ሁለት ከሁለት ወደ ሶስት እያለ የመላው የጉራጌ ቅዱሳን ሆኖ ከማየት በላይ የሚያስደስት ነገር የለም!! ራዕዩ እግዚአብሔር ያስጀመረውና የመራው ስለነበር የእንቅስቃሴው ዋነኛ ምሰሶ የነበሩት ሁለት ጉዳዮች፦

1) የወንጌል በገጠር አገልግሎት የሚለው ስያሜ ማስመለስና
2) በሰባት ቤት የሚገኙ ሁሉንም ወረዳዎች፣ በየወረዳው የሚገኙ አብያተክርስቲያናት፣ በከተማ የተደራጁ ሁሉንም የአጥቢያ/አካባቢ ህብረቶች፣ የቀድሞ የወንጌል በገጠር መስራች አባቶችና መላው የጉራጌ ተወላጅ የሆኑ ቅዱሳ ያቀፈ ግዙፍ ተቋም መመስረት የሚሉትን በመሳካታቸው የድል ስሜት ይሰማኛል።

እነዚህ ሁለት ጉዳዮች የራዕዩ ማጠንጠኛዎችና ለዓመታት የታገልንባቸው ናቸውና ሆነው በማየቴ ደስታዬ ላቅ ያለ ነው። የእግዚአብሔር ስም የተመገነ ይሁን!!

መንገዳችን የሚመራው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ፣ ከእግዚአብሔር በተቀበልነው ራዕይ ምን እንደተሳካና ምን እንደሚቀር ጠንቅቀን ስለምናውቅ ስኬታችን በትክክል እንመዝናለን! እግዚአብሔር ባስጀመረን ጉዞ ያሳካናቸው ብዙ ናቸው። ያላሳካናቸውና የሚቀሩንም እንደዛው!

ቃሉ "ለሁሉም ጊዜ አለው"እንደሚለው ላለፉት ስምንት ወራት በአንድም በሌላ የለውጡና የተሀድሶው ራዕይ ገዝተው ለማስፈፀም የተሰማሩት የሰባት ቤት አብያተክርስቲያናት መሪዎችና በሂደቱ የተዋቀሩ ኮሚቴዎች ጉዞ በዝምታ መጠበቁ አስፈላጊ ነበር። ለዓመታት በተደጋጋሚ በድምፅና በፅሁፍ እንዳስቀመጥኩት የእነዚህ አካላት ጉዞ በትላንትና ዕለት ነሐሴ 11/2017 ዓ.ም ለህዝብ ቀርቧል። ስለፕሮግራሙ እግዚአብሔርን እያመሰገንኩ ከዛሬ ጀምሮ ባለፊት ዓመታት ያልተዳሰሱ ርዕሰ ጉዳዮችና እግዚአብሔር ከሰጠኝ ራዕይ ያልተጠናቀቁና ያልተሰሩ ስራዎችን በስፋት መዳሰስ እጀምራለሁ።

በመሆኑም በመላው አለም የምትገኙ አማኝ የጉራጌ ተወላጆችና ቤተሰቦች ለወራት ተቋርጦ የቆየውን መላው የጉራጌ ዞን አብያተክርስቲያናት እና የወንጌል በገጠር አገልግሎት የሚዳስሰውን የሚዲያ አገልግሎቴ ዳግም መጀመሬ ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው።

ስለዚህ ከነገ ጀምሮ በሁሉንም የማህበራዊ ሚድያ አማራጮች እንድትከታተሉኝ እየጋበዝኩ እግዚአብሔር በምድራችን ሊሰራ ያለውን ታላቅ የለውጥና የተሀድሶ ስራ አብረን እንድንሰራ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

እግዚአብሔ

18/08/2025
30/03/2024
የእነሞር ወረዳ አብያተክርስቲያናት ህብረትና የወረዳ የከተማ ህብረት መሪዎችና የጉንችሬ ከተማ ክሩሴድ አዘጋጆች ለቀዳሚ የወንጌል በገጠር ባላደሮችን እውቅና ለመስጠትና ከትውልድ ለማስተዋወቅ ከ...
29/03/2024

የእነሞር ወረዳ አብያተክርስቲያናት ህብረትና የወረዳ የከተማ ህብረት መሪዎችና የጉንችሬ ከተማ ክሩሴድ አዘጋጆች ለቀዳሚ የወንጌል በገጠር ባላደሮችን እውቅና ለመስጠትና ከትውልድ ለማስተዋወቅ ከሁሉ በላይ በረከታቸውን ለትውልድ እንዲሰጡሳደረጋችሁት መልካም ስራ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ።

18/11/2022

ማርቆስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ እንድርያስንም ፊልጶስንም በርተሎሜውስንም ማቴዎስንም ቶማስንም የእልፍዮስን ልጅ ያዕቆብንም ታዴዎስንም ቀነናዊውንም ስምዖንን፥
¹⁹ አሳልፎ የሰጠውንም የአስቆሮቱን ይሁዳን።
²⁰ ወደ ቤትም መጡ፤ እንጀራም መብላት ስንኳ እስኪሳናቸው ድረስ እንደ ገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ።
²¹ ዘመዶቹም ሰምተው፦ አበደ ብለዋልና ሊይዙት ወጡ።
²² ከኢየሩሳሌም የወረዱ ጻፎችም፦ ብዔል ዜቡል አለበት፤ ደግሞ፦ በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ብለው ተናገሩ።
²³ እነርሱንም ወደ እርሱ ጠርቶ በምሳሌ አላቸው፦ ሰይጣን ሰይጣንን ሊያወጣው እንዴት ይችላል?
²⁴ መንግሥትም እርስ በርስዋ ከተለያየች ያች መንግሥት ልትቆም አትችልም፤
²⁵ ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ያ ቤት ሊቆም አይችልም።
²⁶ ሰይጣንም ራሱን ተቃውሞ ከተለያየ፥ መጨረሻ ይሆንበታል እንጂ ሊቆም አይችልም።
²⁷ ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለም፥ ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።
²⁸ እውነት እላችኋለሁ፥ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሁሉ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤
²⁹ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሳደብ ሁሉ ግን የዘላለም ኃጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።
³⁰ ርኵስ መንፈስ አለበት ይሉ ነበርና።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921352212

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቁጥር አንድ ወንጌል በገጠር የፍቅር አገልግሎት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ቁጥር አንድ ወንጌል በገጠር የፍቅር አገልግሎት:

Share