25/12/2025
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ-ክርስቲያን በትላንትናው ዕለት ታኅሳስ 15/2018 ዓም በቀጣና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክን ባደረገው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ቤተ-ዕምነቱን የሚመሩትን ፕሬዚዳንቶች መርጦአል። ጠቅላላ ጉባዔው መጋቢ ላኮ በዳሶን በዋና ፕሬዚዳንትነት እንዲሁም መጋቢ ለወየሁ ስንሻውን በምክትል ፕሬዚዳንትነት መርጦ በመሾም ጸልዮላቸዋል። የኢትዮጲያ ሙሉ ወንጌል ስነ መለኮት ሴሚናሪየም ለቤተ-ዕምነት መሪዎቻችን መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እየተመኘ በቀጣዩ ዓመታት አብሮ ለመሥራት ከጎናችሁ የሚቆም መሆኑን በታላቅ ደስታ ይገልጻል።
እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ።