24/08/2026
በክርስቶስ የማይለወጥ ልብ የማይሰበርም አጥር የለም!
።።።።።።።።።። //።።።።።።።።።።።።።
ትላንት እሁድ ጠዋት በነበረን አገልግሎት ከአገልጋይ ዮሴፍ ለማ ጋር Jo Yoseph ከሐዋርያት ሥራ 9–11 ቃለ እግዚአብሔርን የተማርን ሲሆን ትምህርቱም ጥቅልል መልዕክት የሚከተለው ነበር
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“የጌታ ጸጋ አሳዳጁን ሳዎልን ለወጠው ፤ ወንጌልም ከአይሁድ አልፎ በአንጾኪያ ላሉ አሕዛብ ሁሉ በኃይል ደረሰ። እውነተኛ ክርስትና የምቾት መደለያ ሳይሆን ስለ ክርስቶስ ስም ዋጋ ለመክፈል ራስን መስጠትና በቤተክርስቲያን አካል ውስጥ አብሮ መቆም ነው።” ጌታን በመፍራትና በመንፈስ ቅዱስ ሀይል እየተመላለስን እኛም ዛሬ እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ሆነን በድፍረት የኢየሱስን አዳኝነት ልንመሰክር ይገባናል! 🙏🙏🙏
እንዲሁም ከዘማሪ ይስሀቅ ሰድቅ ጋር እግዚአብሔርን አመለክን። ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ ይሁን‼️