IT-EL 46

IT-EL 46 Senbet Media ፔጃችንን like በማድረግ ሁለገብ የኦርቶዶክስን ተዋህዶን አስተምህሮ ያገኛሉ

አላማዬ ሳያውቁና ተታለውም ጭምር ከሃይማኖታችን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትተው የወጡትን እርቶዶክስ እውነተኛ እንደሆች ለማስረዳትና ለመመስከርም ጭምር ነው።ትልቁ አላማዬ ግን የሌላው ሃይማኖትን ለመንቀፍ ሳይሆን እውነትን እውነት ማለት ብቻ ነው።በዚህ ደግሞ ቤልሆር ብቻ ነው የሚቀየመኝ።ለሱ ደግሞ ደንታ የለኝም።ማንም የቆመ ቢመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።

17/12/2023

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Rabira FG, Natnael Kasim Abiyo

11/07/2023

ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አንድነት ገዳም በካሊፎርኒያ። Want to join Us in making a difference? I'm raising money to benefit SAINT JOHN ...

23/06/2023
ስደት ሰይጣን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚጠቀምበት መሣሪያ ነው።ለማጥፋት የሚደክሙት ደግሞ የአጋነንት ሰራዊቶች ናቸው፡፡ የሚገርመው ታዲያ፥ስደት እግዚአብሔርም ዓላማውን ለመፈጸም የሚጠቀምበ...
15/02/2023

ስደት ሰይጣን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚጠቀምበት መሣሪያ ነው።ለማጥፋት የሚደክሙት ደግሞ የአጋነንት ሰራዊቶች ናቸው፡፡ የሚገርመው ታዲያ፥ስደት እግዚአብሔርም ዓላማውን ለመፈጸም የሚጠቀምበት ታላቅ መሣሪያ መሆኑ ነው፡፡

https://www.youtube.com/channel/UCWovK-lfhs5zr0ryAJuZOZw
07/09/2021

https://www.youtube.com/channel/UCWovK-lfhs5zr0ryAJuZOZw

መንፈሳዊነታቸውን የጠበቁ የኢትዮጽያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙርና ሌሎችንም ትምህርቶችን አቀርብላችኋለው።I'll give it to you Who have kept their spirituality of ethiopian orthodox tewahido songs a...

11/06/2021
12/04/2020

ሆሳዕና

በመምህር ኃይለ ማርያም ላቀው
ሆሳዕና የሚለው ቃል በዕብራይስጥ ሆሼዕናህ Â የሚል ሲሆን ትርጉሙም እባክህ አሁን አድንÂ ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩከ ነው፡፡ Â መዝ.117፡25-26 የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፣ ሆሳዕና በአርያም Â በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሳዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡
በሌላ አነጋገር ይህ ዕለት የጸበርት እሑድ Â /Palm Sunday/ ይባላል፡፡ ታሪካዊ አመጣጡ የመልካም ምኞትና የድል አድራጊነት መገለጫ ሆኖ ከደገኛው አባታችን ይስሐቅ ልደት ጋር ተያይዞ የመጣ ነው፡፡ ይኸውም ሣራ የወላድነት ዕድሜዋን ጨርሳ ልማደ እንስት ከተቋረጠባት በኋላ ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ ይስሐቅን በሰጣት ጊዜ ዘመዶችዋ የተሰማቸውን ደስታ ለመግለጽ የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ የጎበኟትን አምላክ አመስግነዋል፡፡ እስራኤል ከአስከፊው የግብፃውያን አገዛዝ ተላቀው ባሕረ ኤርትራን በደረቅ ሲሻገሩ የተሰማቸውን እጥፍ ድርብ ደስታ በገለጡ ጊዜ፣ እንዲሁም ዮዲት የተባለች ንግሥተ እስራኤል ሆሎፎርኒስ የተባለ አላዊ ንጉሥን ድል ባደረገች ጊዜ ቤተ እስራኤል እንደ ሰንደቅ ዓለማ የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ አደባባይ ወጥተው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
በዘመነ ሐዲስም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ዘር ከዲያብሎስ ቁራኝነት ከሲኦል ባርነት ነጻ ለማውጣት ወደ ዙፋን መስቀሉ /ሉቃ.22፤18/ በተጓዘ ጊዜ ሕፃናት እና አእሩግ ነጻ የሚወጡበት ቀን መድረሱን እነርሱ ሳያውቁ እግዚአብሔር ባወቀ ዘንባባ በመያዝ ዘምረዋል፡፡ እስራኤል ዘንባባ በመያዝ እንዳመሰገኑት እኛም አስራኤል ዘነፍስ ዕለቱን ዘንባባ /ጸበርት/ በግንባራችን በማሰር በዓሉን በየዓመቱ እያስታወስን እናከብራለን፡፡ በዚህ ዕለት ዘንባባ እየተባረከ ለሕዝቡ ይታደላል፡፡
ሕፃናትና አእሩግ ለዳዊት ልጅ መድኃኒት መባል ይገባዋል፡፡
 እያሉ ዘምረዋል፡፡ ይህ ሁሉ በአንድ ወገን የነበረው የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ሲሆን በሌላ በኩል የነበረው አቀባበል ደግሞ እጅግ የሚያሳዝን ነበር፡፡ ሥርዓተ ኦሪትን፣ ትንቢተ ነቢያትን በሚገባ እንከተላለን ይሉ የነበሩ ጸሐፍት ፈሪሳውያን መምህር ሆይ ደቀ መዛሙርትህን ገሥጻቸው  አሉት፡፡ ጌታችንም መልሶ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ  ሲል መልሶላቸዋል፡፡ ቅናት አቅላቸውን ያሳታቸው ፈሪሳውያንም የዋህ የሆነው ሕዝብ ምስጋና ወደ ጥላቻ እንዲለወጥ አድርገዋል፡፡ ከሁሉ የሚያሳዝነው በዕለተ ሆሳዕና እሑድ ዘንባባ ይዘው የዘመሩለትን ጌታ ዓርብ ይሰቀል ዘንድ ይገባል  ብለዋል፡፡
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ በዚህም በነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ፡፡ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፣ በአህያዪቱ ግልገል በውርንጫዪቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡Â ዘካ.9፡9፤ ማቴ.21፡4፤ ማር.11፡1-10፤ሉቃ.19፡28-40፤ ዮሐ.12፤15፡፡ ጌታችን በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱ የሰላም ንጉሥ መሆኑን ያመለክታል፡፡ እስራኤል ዘመነ ምሕረት ሲሆንላቸው አባቶቻቸው በአህያ ጀርባ ተቀምጠው ይታዩ ነበር፡፡ ጌታም እውነተኛ የኅሊና ሰላም ይዤላችሁ መጣሁ ሲለን በአህያ ጀርባ ወደ ቤተ መቅደስ ሕይወታችን ተጉዟል፡፡
መላእክት በዕለተ ልደቱ በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባዋል በምድር ሰላም ለሰው ሁሉ ይሁን Â /ሉቃ.2፡13/ እያሉ የዘመሩለት የሰላም ባለቤት ነው፡፡ በመዋዕለ ትምህርቱም
ሰላሜን እሰጣችኋለሁ Â /ዮሐ.14፡27/ ብሎ እንዳስተማረ ያን ሰላም የሚሰጥበትን ዕለት መቅረቡን ለማመልከት ነው፡፡ በሌላ በኩልም በአህያ ጀርባ መቀመጡ ኅቡዕ ምሥጢር አለው፡፡ በአህያ ጀርባ የተቀመጠ ሰው ሌላውን አሳድዶ አይዝም፣ እርሱም ሮጦ አያመልጥም፡፡ በዚህም ጌታችን በእምነት ለሚፈልጉት የሚገኝ ቅርብ ሲሆን በእምነት ለማይፈልጉት ግን የማይገኝ መሆኑን አስተምሯል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ፀሐይ ዕድሜያችን ሳትጠልቅ በእምነት እንፈልገው፡፡ አሞጽ4፡፡ የአህያን ጀርባ ያልናቀ ጌታችን ትሑት ሰብእና እና የተሰበረ ልቡና ወዳለው ሰው ዘወትር ይጓዛል፣ የተዋረደውንና የተሰበረውን ልብ አይንቅም፡፡ ኢሳ.66፡2፤ መዝ.50፡17፡፡
ለታሰሩት መፈታትን ሊሰብክ ሰው የሆነ ጌታችን ከማሰሪያዋ በተፈታች አህያ እንደተቀመጠ ሁሉ ከኃጢአት እስራት በተፈታ ሕይወት ዛሬም ያድራል፤ የኅሊና ሰላምን ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ንስሐ ገብተን ጌታችንን ሆሳዕና በአርያም እያልን ልናመሰግነው ይገባል፡፡
ምንጭ፡ ሐመር ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፣ መጋቢት/ሚያዝያ 1996 ዓ.ም

30/10/2019

ዘፈን ኃጥያት ነው?

' #ዘፈን' ኃጥያት ስለሆነ ነው ቤተክርስቲያን ዘፈንን አጥብቃ የምታወግዘው::" ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።"(የያዕቆብ መልእክት 1:15)

ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያን ለምን ዘፈንን አወገዘች???

1. ዘፈን የአጋንንት ሥራ ነው:: አጋንንት ይዘፍናሉና:: ለዚህ ምንም ማስተባበያ አያስፈልገውም:: መጽሐፍ ቅዱስ "በዚያም አጋንንት ይዘፍናሉ" በማለት ስለ አጋንንት
ዘፋኝነት ይናገራል::(ኢሳ.13:21) አትዝፈኑ ማለት የአጋንንትን ሥራ አትሥሩ ማለት መሆኑን እንረዳ:: ይህን በተመለከተ መጽሐፈ መቃብያን ደግሞ እንዲህ ይላል:-
"....እየዘፈኑም ከአጋንንት ጋር ይጫወቱ ነበር::
አጋንንትም ጫወታቸውንና ዘፈናቸውንም ሁሉ ያደንቁላቸው ነበር::" (1ኛ.መቃ.36፥27-28)
በዚህ ስፍራ አገላለጥ ደግሞ ለየት የሚለው አጋንንት ዘፋኞች ብቻ ሳይሆኑ ከዘፈን አድናቂዎች ጐራ መሰለፋቸው ነው::ስለዚህ ከዘፋኞች ጎን በመሆን የሚያግዟቸውና የሚደሰተው አጋነንት እንጂ እግዚአብሔር አይደለም፡፡

2. ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ሥራን አስመልክቶ ሲናገር እንዲህ ይላል:- "ስለ ተግባረ ዕድ ግን በዓለም ከሚሠሩ ሥራዎች መንፈሳዊ ሕግን ከሚቃወም ሥራ በቀር ሁሉንም ሊሠሩ ይገባል:: ... እንደ ዘፋኝነት፥ እንደ መጥፎ ጫወታ፥
በእግር እንደ ማሸብሸብ(ዳንስና ጭፈራ) ካልሆነ በቀር ነው::" (ፍት.ነገ.መን.አን. 23:820) መንፈሳዊን የሚቃወምን ምንም ነገር መሥራት እንሌለብን እየነገረን፡፡
ይህ የአበው ቃል ዘፋኝነት በመንፈሳዊ እይታ እንደ ሥራ መቆጠር እንደሌለበት ያስረዳል::ምክንያቱም አንድ አንድ ሰዎች ስራዬ ነው ካልሰራው አልበላም ስለዚህ መዝፈኔ እንደ ኃጥያት አይቆጠርብኝም የሚሉ አሉና ዘፈንን መዝፈን እንደ ስራ አይቆጠርም፡፡ ይህም ስራ ነው ከተባለ ጠንቋዩም ጥንቁልናውን ስራዬ ነው ማለት ይችላል ማለት ነው::.::
ክርስትያን የሆነ ሁሉ ዘፋኝነት በቅዱሳን መጻሕፍት የተከለከለ ተግባር መሆኑን ማወቅ አለበት፡፡ ዘፋኝነት እንደ መተዳደርያ ስራም ተደርጎ መታየት የለበትም፡፡ በዘፋኝነት ‹‹ሥራ›› የተሰማሩ ክርስትያኖች በሃይማኖት ለመኖር ከወደዱ በንስሐ እንደተመለሱ ዝሙት አዳሪዎችና ቀማኞች ሁሉ እነርሱም ሌላ የስራ አማራጭ መፈለግ ይኖርባቸዋል፡፡
በዘመናችን የሐጢያት ተግባራ ሁሉ ገቢ ማስገኛ እየሆኑ ነው፡፡ ገቢ ያስገኘ ተግባር በሙሉ ግን እንደ ሙያ (ፕሮፌሽን) መቆጠር የለበትም፡፡ ‹‹መተዳደሪያዬ ነው›› እያሉ ሕሊናን የሚቆጠቁጥና መንፈሳዊነትን የሚጋፋ ስራ ከመስራት መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ አትስረቅ አታመንዝር ያለ እግዚአብሔር ‹‹አትዝፈን›› ደግሞ ብሏል፡፡ ታዲያ በመንፈሳዊ ጎዳና ለሚመለከተው ዘፈን ከስርቆትና ከምንዝር በምን ይለያል? ሁሉም የእግዚአብሔርን ሕግ በማፍረስ አንድ ናቸውና፡፡ ምን ላድርግ? መተዳደሪያዬ ነው እያሉ በዘፋኝነት ጸንቶ ከመኖር አማራጭ መሻት ይበጃል፡፡ በዚህ ዓለም ስጦታው ዘፋኝነት ብቻ የሆነና ሌላ ምንም ዓይነት ተውህቦ (ስጦታ) የሌለው ሰው የለም፡፡ እንዲህ ቢሆን ኖሮ ፈጣሪም ዘፋኝነትን ባላወገዘ ነበር፡፡ዘፋኞች እንደሌላው ሰው በሌላ የሥራ ዘርፍ ተሰማርተው መኖር የማይችሉ ቢሆኑ ኖሮ ፈጣሪ ዘፋኝ አትሁኑ የሚል ትእዛዝ አይሰጥም ነበር፡፡ ስለዚህ ካሰቡበት እንደሌላው ሰው ሁሉ ዘፋኞችም ሌላ የስራ አማራጭ አላቸው፡፡

3. ዘፋኝነት "የሥጋ ሥራ" በመሆኑ ኃጢአት ነው::
(ገላ.5:21):: "በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ፤" ተብሏልና:: (ገላ.5:16)::
ዝማሬ ሰማያዊ፡ዘላለማዊ የሆነውን እግዚአብሔርን ማመስገን ነውና አሱን መምረጥ ይኖርብናል፡፡
ቅዱሳንን ስናመሰግን በቅዱሳን የከበረውን እግዚአብሔርን ማመስገን ነው እንጂ ሠውን እያመሰገንን አይደለም፡፡

4. ዘፈን በመንፈሳውያን መጻሕፍት ተወግዟል:: ሐዋርያት በዲድስቅልያ "ኢትኩኑ ዘፈንያነ" ፥ "ዘፋኞች አትሁኑ" ብለዋል:: (ዲድስቅልያ፤ አንቀጽ 7) ቅዱስ ጳውሎስ "በቀን እንደምንሆን በአግባብ እንመላለስ:: በዘፈንና በስካር አይሁን" ብሏል:: (ሮሜ.13፥13) ቅዱስ ጴጥሮስ
ደግሞ "በስካርና በዘፈን የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል::" ይለናል:: (1ኛ.ጴጥ.4:3)::በማለት በዘፈን ያረከስናትን ሕይወታችንን እንድንተው ይመክረናልና ልንተው ያስፈልጋል፡፡

መጽሐፈ ሐዊ ደግሞ "ከሰይጣን የተገኘ ነውና
ዘፈንንና ዳንስን ከኛ ማራቅ ይገባናል::" ይለናል::
ዘፈን የአጋንንት ስራ መሆኑን ስታውቂ አይንሽ ተገልጦ አንድ ምሥጢር መመርመር ይጀምራል፡፡ እስኪ ሀገራችንን ጨምሮ የጃማይካውያንንና የአንዳንድ የአፍሪካንና የሌሎችንም አህጉራት ዘፋኞችን ድርጊት ልብ ብለሽ መርምሪ፡፡ ደግሞም ፀጉራቸውን አንጨብርውና በመናጥና በአሺሽ ጦዘው አንገታቸውን በማወናጨፍ የሚዘፍኑት ዘፈን መገኛውም እንደሆነ ማስተዋል ሞክሪ፡፡ የባለ ዛሮች ዝየራ አይተሽ የምታውቅ ከሆነ ፍፁም ተመሳሳይ ሆኖ ታገኘዋለሽ፡፡
ባለውቃቤዎችስ ሲደነፉ ተመልክተሽ አታውቅምን? የባለ ውቃቤዎች ድንፋታ ደግሞ ቁርጥ እዋኽ፣ እዋኽ እየተባለ የሚዘፈነውን ባህላዊ ዘፈን ይመስላል፡፡ ፍከራው ቀረርቶውና በየብሄረሰብ የምትመለከትመለከቺው ዘፈንና ጭፈራ ብትመረምሪ ከዚህ የቀረበ መመሳሰል አናጣበትም፡፡ ቅዱስ ሐዊ እንደተናገረው ‹‹ዘፈንና ዳንስ ከሰይጣን የተገኘ›› ነውና፡፡

(መጽ.ሐዊ አን. 50):: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ደግሞ ከማዘዝ አልፎ ዘፈንን እንተው ዘንድ "ዘፈንን ትተዉ ዘንድ እማልዳችሗለሁ፤" በማለት ይማጸናል:: (ተግ.ዘዮሐ.አፈ.28) ዘፈንን አንተውም ላሉ ደግሞ መጽሐፈ ሐዊ "በዘፈን ጸንተው የሚኖሩ
ይፈረድባቸዋል" በማለት ሲያስጠነቅቅ እናገኛለን:: (መጽ.ሐዊ.አን. 12)
ከመጨረሴ በፊት አንድ ታሪክ ልንገርሽ ከእለታት በአንድ ቀን አንድ ጎልማሳ ልጅ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቀርቦ እንዲህ በማለት ጠቃቸው፡፡"አባ በተክሊል እንዳላገባ ስጋዊ ድንግልና የለኝምና በዓለማዊ ዘፈን ባገባስ?" ሲላቸው ቅዱስ ዮሐንስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፡፡"ልጄ በዘፈን ሰይጣንን ከምትጠራ በዝማሬ መላዕክትን ጥራ" ብለው መለሱለት፡፡ ስለዚህ በዘፈን ሰይጣንን አንጂ ፈጣሪን የሚባርኩንን እንደማንጠራ ግልፅ ባለ አንደበቱ አስተምሮናል::አሁን የኢትዮጵያን ዘፋኞችና ተወዛዋዦች ስልጣኔ እየመሠላቸው ራቁታቸውን ካልሆኑ በስተቀር መቀረፅ አይፈልጉም፡፡በዕውነት ልቦና ይስጣቸው፡፡ይህ አሁን በየቻናሉ የምንመለከተው ለመንፈሳዊና ለአይን ትውልድን የሚያበላሹ ናቸውና ለአይናችንም ጭምር ልንጠነቀቅ ያስልጋል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251902377516

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when IT-EL 46 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to IT-EL 46:

Share