አርዱል ሀበሻ-Ardul habesha

አርዱል ሀበሻ-Ardul habesha አርዱል ሀበሻ የአውሊያዎች, የመሻኢኾች መፍለቂያ

ሸይኽ ዑመር ይማም ኮምቦልቻ ሰሞኑ በአብዱልጀሊል ሸህ አሊ ነብዩን(ሰ.ዐ.ወ) በመስደብ እስልምናን ከሚያንቋሽሽ ግለሰብ ጋር ላይቭ ተወዳጅተዋል በማለት በፌስቡክ ገፁ ያሠራጨዉ ፅሁፍ ፍፁም ዉሸ...
06/01/2026

ሸይኽ ዑመር ይማም ኮምቦልቻ ሰሞኑ በአብዱልጀሊል ሸህ አሊ ነብዩን(ሰ.ዐ.ወ) በመስደብ እስልምናን ከሚያንቋሽሽ ግለሰብ ጋር ላይቭ ተወዳጅተዋል በማለት በፌስቡክ ገፁ ያሠራጨዉ ፅሁፍ ፍፁም ዉሸት ነው ሲሉ ለሚዛን ሚዲያ ገልፀዋል ።

" እኔ ግለሰቡ አይደለም አብሬዉ ልቀመጥ ቀርቶ በቅጡ እንኳ አላዉቀዉም " የተፈበረከ ዉሸት ነዉ:: ማስረጃ ካላዉ ያዉጣ። ሲሉ አክለዋል::

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑንየታላላቆቹ ማለፍ ለኡማው ከባድ ስብራት ነው:: የራያው ሸይኽ በሺር ሸይኽ ዑመር አባቦፋ ወደ አኺራ ሂደዋል። አላህ ከሳሊሆቹ ከሲዲቆቹ ጋር በጀነቱ ያሳርፋቸው::...
03/12/2025

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

የታላላቆቹ ማለፍ ለኡማው ከባድ ስብራት ነው:: የራያው ሸይኽ በሺር ሸይኽ ዑመር አባቦፋ ወደ አኺራ ሂደዋል። አላህ ከሳሊሆቹ ከሲዲቆቹ ጋር በጀነቱ ያሳርፋቸው:: ቤተሰቦቻቸውን እንዲሁም ወዳጆቻቸውን በሙሉ አላህ ሶብር ይስጣቸው::

ፋቲሓ🤲

አንዳንድ እውነታዎች .. ✍️በነሲም- ሐሰን ሁሉም ተቃራኒ ፊርቃዎች ተስማምተው የሚጠሉት ሰው ነው። በእሱ ጉዳይ ያብራሉ። ልዩነታቸውን ሽረው ይጨባበጣሉ። "አን ሙብተዲዕ" "አን ተክፊሪይ" ብ...
16/11/2025

አንዳንድ እውነታዎች .. ✍️በነሲም

- ሐሰን ሁሉም ተቃራኒ ፊርቃዎች ተስማምተው የሚጠሉት ሰው ነው። በእሱ ጉዳይ ያብራሉ። ልዩነታቸውን ሽረው ይጨባበጣሉ። "አን ሙብተዲዕ" "አን ተክፊሪይ" ብለው እንዳልተሞላለጩ ይሆናሉ። ሆኖም ሁሉም የየራሳቸው ምክንያት አላቸው።

° ሰለፊው አብዛሃኛው በሐሰን ትርጉም ስራ ነው አቂዳውን የተማረው። ከኢብኑ ተይሚያህ እና ከኢብኑል ቀዪም እሳቤዎች ጋር የተገናኘው በእሱ ድርሳኖች ነው። ዛሬ ላይ ከትላንት አቋሙ ተመልሶም ስለራሳቸው ድርሳኖች እና አስተምህሮዎች አዳዲስ ነገር የሚያስተዋውቃቸው እሱው ነው። የራሳቸውን መፅሃፍ የሚያነቡት የእሱን ጥቆማዎች ተከትለው ነው። እዳው አለባቸው ሆኖም ግን አሁን ከእነሱ ባለመሆኑ ብቻ ውለታውን በጥላቻ እና ስም ማጥፋት ይከፍሉታል። ስሙን በማጠልሸት ክብሩ ላይ ለመረማመድ ይሻሉ ። ለእነሱ በእንቅርት ላይ ጆሮደግፍ ነው እሱ።(ያው እንቅርቱ አስተምህሯቸው መሆኑ ነው😁)

° ኢኽዋኑ ክፍል የሚዘረዘር ምክንያቱ ብዙ ነው ። አብዛሃኛውን ጊዜ ገፊ ምክንያታቸው ግን ሂስድ እና ቂም ነው። ኢኽዋን ፍልስፍናው እና መሬት ላይ ያለው ትግበራ የተጣሉበት፤ ግማሽ ክ/ዘ በላይ ይህንን መለያየት ለማስታረቅ ቁጭ ያላለ፣ ከትላንት ስህተቱ መማር ያልቻለ፣ በ ምናብ አለም(Utopia) ውስጥ የሚዳክር፣ ስፋት የሚመስል ጥበትን ሲሰተሙ አድርጎ የሚንቀሳቀስ ቆንጆ ህልመኛ ጀመዓ ነው። ትግበራው ላይ ያለ እነሱ እውቅና ማንም ሙስሊም እንዲገን ወይም ከእነሱ ማዕቀፍ ውጪ ማንም ተደማጭ እንዲሆን፣ ቁብ እንዲሰጠው፣ ተከታይ እንዲኖረው አይሹም። ሁሉም መልካም ድርጊት "ክብሩን ኢኽዋነል-ሙስሊሚን ይውሰድ" በሚል ሐረግ መቋጨት አለበት። የሚያራምደው አቋም ግለሰባዊ እምነታቸው ቢሆን እንኳ መነሳቱን፤ መወደሱን፤ መሰማቱን አይወዱትም። ይህን ለመናድ የማይፈነቀል ድንጋይ የማይሸረብ ሴራ፤ የማይለበስ ጭምብል የለም። የሆነ ነገር ትንፍሽ ባለ ቁጥር 'እልህ ነው' ይሉሃል ። እልሁ ገፍቶት ስለፃፈው ወይም ስለተናገረው ሐሳብ ግን ትንፍሽ አይሉም። የፃፈበትን ንያ ከእሱ በላይ እነሱ ያውቁለታል። የተነሳበትን መንደርደሪያ ከራሱ ቀድመው እነሱ ያሰምሩለታል። (የቀልብ አዋቂነት)

"ትኩረት ስለሚፈልግ ነው" ይሉሃል። እነሱ ግን ቀዳሚ ትኩረት ሰጪ ሆነው ታገኛቸዋለህ። ትኩረት በመንፈግ ፍላጎቱን ሲያከስሙት አይታዩም። (ከራስ ጋር መጋጨት)

"አንድነትን የሚሸረሽር" የሚሉ ኢኽ-ሰለፊዎችም አልጠፉም። ሌሎች ኡስታዞች በየሚንበሩ፣ በየሚድያው የአንዱን ወገን እምነት እና እሴት ሲያጠለሹ ግን ቅድስና ነው። "አንድነት" ለእነሱ የራሳቸውን መስመር ከወቀሳ የሚያተርፉበት ጋሻ ነው። አንድነት ለእነሱ አሸማቆ ዝም የማሰኘት ሌላኛው ስሙ ነው። 'አንድነት' ለእነሱ ሁሉም በወሃቢ መንገድ እና ፍላጎት ላይ መስማማቱን ሲገልፅ ነው። 'አንድነት' ለእነሱ ሌላው ሲጠለሽ "ጎበዝ" ማለት ፤ እነሱ የሚከተሉት መንገድ ሲወቀስ "ሙስሊሙን መበታተን" ብሎ ታፔላ መለጠፍ ነው።

- እሱ

እሱ ሐሰን ታጁ ነው። ቁብ የማይሰጣቸው ግን ቁብ የሚሰጡት። 'አትከተሉት' እያሉ የሚከተሉት። 'አታዳምጡት' እያሉ ለንግግሩ ጆራቸውን የሚጥሉለት። 'አታንብቡት' እያሉ ማስታወሻ ይዘው የሚያነቡት፤ ከራሳቸው በላይ የሚያውቃቸው፤ ከሚያነቡት በላይ የሚያነብላቸው፣ ከሚፅፉት በላይ የሚፅፍላቸው የእውቀት ባህረ መዝገብ ነው። ትችት እና ወቀሳ አይሰርጉትም። ስም ማጥፋት እና ዘመቻ አይበግሩትም። ዛቻ እና ስድብ አያሸሹትም። ከሊቅ እስከ ደቂቅ አብረው ቢመጡ ሁሉንም በንቃተ-ህሊናው ልክ ማናገር እና ማስተማር የሚችል የእልፍ ድርሳናት እና ስብዕናዎች ድምር ውጤት ነው።

ታሪክ፣ እውቀት፣ ልምድ አብረው የተከሉት አንኳር ስብዕና 🖤

N:B ፦ ኡስታዝ በታላቁ ኑር መስጂድ ፤ የታላቁን ሰው ﷺ ህይወት የሚዳስሰውን ፤ ታላቁን ድርሳን "አልሺፋ" ደርስ መስጠት ጀምሯል። ዘወትር ጁሙዓ ከመጝሪብ እስከ ኢሻ በኑር መስጂድ ብትታደሙ ታገኙታላችሁ ነ

የአብሬት መውሊድ ሊደርስ ከሁለት ወር  በታች ነው  የቀረው:: በዚ አጭር ግዜ ውስጥ ግንባታው ምንም ፈቅ እንደማይል ለሁሉም ግልፅ ነው:: ለምን መውሊዱ እስኪያልፍ አልተጠበቀም? አላማው መው...
15/11/2025

የአብሬት መውሊድ ሊደርስ ከሁለት ወር በታች ነው የቀረው:: በዚ አጭር ግዜ ውስጥ ግንባታው ምንም ፈቅ እንደማይል ለሁሉም ግልፅ ነው:: ለምን መውሊዱ እስኪያልፍ አልተጠበቀም? አላማው መውሊዱን ማስተጓጎል ያለም ይሆን?

አብሬት ከመስመሩ ውጭ ሊሆን አይችልም ወይ ?...................ርእሱ ሊያስደነግጥ ይችላል። በተለይ ልክ እንደ እኛ ህዝብ የዋህ የሆነ እና ኢስላማዊ ማእከላት አይጠፉም ብሎ የሚያስ...
14/11/2025

አብሬት ከመስመሩ ውጭ ሊሆን አይችልም ወይ ?...................
ርእሱ ሊያስደነግጥ ይችላል። በተለይ ልክ እንደ እኛ ህዝብ የዋህ የሆነ እና ኢስላማዊ ማእከላት አይጠፉም ብሎ የሚያስብ የዋህ በሞላበት "ሀድራችን እስከ መጨረሻ ይቆያል" የሚለው የሸኾቹ ቀውል ሲታከልበት ይህ ጥያቄ ሊያስደነግጥ ይችላል።

ይህንን ከመጠየቅ አልፈን መደምደምም ይቻላል አዎ አብሬት የቁባ አባ ከመሰረቱት ተቃራኒ አስተሳሰብ ሊሰጥበት አልያም ሊቀዛቀዝ ይችላል። ለዚህ ማስረጃው ታሪክ ነው።
የአብሬት ሸኾች ከሀድራቸው ከወጡ በሁዋላ ሀድራው ለአመታት ተቀዛቅዞ እንደነበር እናስታውስ:: መካ ነብዩ አደም አለይሂ ሰላም መጀመሪያ አላህን ያመለኩበት ቦታ ነው የመጀመሪያውም ምድር ላይ አላህ የተመለከበት ቦታ ነው።

ነብዩላሂ ኢብራሂም እና ልጃቸው ነብዩላሂ ኢስማኤል በአላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ትእዛዝ ድጋሚ ገንብተውት አላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ሚመለክበት ቦታ አድርገውት ለዘመናት ቆይቷል።

በሂደት አምር ኢብን ሰህል የተባለ የመካ ነዋሪ ለንግድ በሄደበት የጣኦት አምልኮን አይቶ ይሳብ እና አንድ ጣኦት ይዞ ይመጣ እና ካእባ ፊትለፊት ይተክለዋል የተወሰኑ ሰዎች ቢቃወሙትም ከሰውየው በላይ አቅምም ስልጣንም ተሰሚነትም ስላልነበራቸው ሊያስነሱት አልቻሉም።

በሂደት ቀስበቀስ 360 ጣኦታት በዙሪያው እና በውስጡ ተኮለኮሉ ።

አላህም ምንም አላረጋቸውም ኢብራሂም የሰራው ካእባ ላይ እንዴት ጣኦት ያመልካሉ አላለም ይበልጥ ወደ ጨለማ ገቡ ከዛም ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም መጡ እና ወደ ቅኑ መንገድ መለሱት የአላህ በብቸኝነት ሚመለኩበት ቦታ አደረጉት ።

ከዚህ ታሪክ ልንማር የምንችለው ቦታዎችን መጠበቅ በዘመኑ ያሉ ሰዎች ሃላፊነት መሆኑን እና ከተዘናጉ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አይከብደንም ።

በርካታ ሃሪማዎች ነበሩ የሚባልበት ሃገር ላይ ምንኖረው እናም የምንወደው አብሬት የቁባ አባ የአበራሙዝ አሻራ ያረፈበት አብሬት ትላንትና እንዲህ ነበር ዛሬ እንዲህ ሆኖ እንዳይባል በዚህ ዘመን እንደመገኘታችን መጠየቅ መጠበቅ እና መከላከል የሁላችንም ሃላፊነት ነው ።

የተስፋዬ ካሳ ቀልድ ''ምንም አልጠረጠርኩም''በአንድ ወቅት አንድ ስራ አስኪያጅ ሰራተኞች ይበድላል በሚል ከበላይ ገምጋሚዎች መጥተው ሰራተኛውን ይሰበስቡታል።ሁሉም እየተነሳ በሃላፊው የደረሰበ...
11/11/2025

የተስፋዬ ካሳ ቀልድ ''ምንም አልጠረጠርኩም''

በአንድ ወቅት አንድ ስራ አስኪያጅ ሰራተኞች ይበድላል በሚል ከበላይ ገምጋሚዎች መጥተው ሰራተኛውን ይሰበስቡታል።
ሁሉም እየተነሳ በሃላፊው የደረሰበትን በደል ይናገራል።

አንዲት ቅብጥ ዝንጥ ያለች ወጣት የደረሰባትን በደል ለማውራት እጇን ታወጣ እና እድል ይሰጣታል።

'' አንድ ቀን ቢሮ ነይ ፈልግሻለው አለኝ ምንም አልጠረጠርኩም እና ሄድኩኝ ቁጭ በይ አለኝ እና በሩን ቆለፈው ያኔም ምንም አልጠረጠርኩም ኮትሽን አውልቂው አለኝ ምንም አልጠረጠርኩም እና አወለቅኩ ጉርድሽን አውልቂ አለኝ ምንም አልጠረጠርኩም አወለቅኩ ከዛ ብላ ልትቀጥል ስትል አንዱ ገምጋሚ በቃ በቃ አንቺ ስትወልጂም አትጠረጥሪም አላት።

ይቺ ልጅ ለአለቃዋ ከሙሪድነት አልፋ መሪድ ሆናለች አንዳንዶች እያለማመዱን ያሉት ይህንን ጭፍን ተገዥነት ነው።

ጠቅላይ ቢሮ ያ የሸኾቹ ሀሪማ ስንት አጂላ ኡለማ ወሊይ ጋር የተቀማመጡበት ያ የኛ መሰብሰቢያችን ያ ዳግማዊ አብሬት ያ መገርገቢያ ረመዳን አውራድ ደምቆ የኖረበት መገርገቢያችን የት ደረሰ ፈርሶ ሲበተን ምንም አልጠረጠራችሁም አይደል ? እሱም አሪፍ ነው

ሸኾች በገንዘባቸው ገዝተው የመሰረቱት የወሊሶ መስጅድ ያ ስንት ኡለማ ሚያርፍበት የነበረው መስጅድ ቃጥባሪዮች ሰኞ ኢስነይን አብሬትዮች ማክሰኞ መገርገቢያ ይቀመጡበት የነበረው የወሊሶ መስጅድ ኢማሙ ተባረው ኢስነይኑም መገርገቢያውም ሲበተን አሁንም አብሬት ላይ እየመጣ ያለውን አደጋ አልጠረጠራችሁም አይደል ? ደግ

የሸኾቹ የአብሬቲይ ኪታቦች ሆን ተብለው ተበርዘው ሲታተሙ ሲቀጠፍ ሲጨመርባቸው ምንም አልጠረጠራችሁም አይደል እሱም የቤተሰብ ጉዳይ ነው ብላችሁ አለፋችሁ ይሁና....

ያ የቁባ ሸኾች ከዳና ሲመጡ ስሩ ቁጭ ብለው ያቀሩበት ለልጃቸው ጠሪቃ ልቅና ያሻገሩበት የቀደመው ዘመንን ትዝታ እና ናፍቆት ይዞ የቆመ ህያው ምስክር ሲገነደስም ምንም አልጠረጠራችሁም ?

መቼ ይሆን ከ እንቅልፋችሁ የምትነቁት መቼ ይሁን መሪድነትን ትታችሁ በወል ቅርሳችን ላይ የሚደርሰውን ውድመት የቤተሰብ ሽፋን ሳትሰጡ ምትቆሙት ለነገሩ ስለማትጠረጥሩ መቼም አትነሱም ።

Ambassador/Ustaz Hasen Tajuሸፍጥና ዉሸት በየትኛዉም ቦታና ሁኔታ የእኩይ ስብዕናዎች መገለጫ ቢሆንም በሀይማኖት መስክ ሲሆን የበለጠ ያሳቅቃል፡፡ የአፈንጋጭ አስተሳሰብ ባለቤቶች...
05/11/2025

Ambassador/Ustaz Hasen Taju

ሸፍጥና ዉሸት በየትኛዉም ቦታና ሁኔታ የእኩይ ስብዕናዎች መገለጫ ቢሆንም በሀይማኖት መስክ ሲሆን የበለጠ ያሳቅቃል፡፡ የአፈንጋጭ አስተሳሰብ ባለቤቶች እምነታቸዉን ለማጽናት ከሚጠቀሙባቸዉ ስልቶች መካከል አንዱ በታላላቅ ስብእናዎች ስም መጽሀፍና አባባሎችን መፈብረክ ወይም የታዋቂ ሰዎችን መጽሀፍት መበረዝና መከለስ ነዉ፡፡ ከስነምግባርና ከታማኝነት መርሆዎች ዉጭ የሆነዉ ይህ መንገድ ከሀይማኖቶች ይልቅ ከግብረገብ ከተፋቱ የፖለቲካ አይዲዮሎጂዎች ጋር ያመሳስላቸዋል፡፡

የጥንቶቹ አፈንጋጮች በኢማም አህመድ እብን ሀንበል ስም መጽሀፍትና አባባሎች ፈብርከዉ ማሰራጨታቸዉ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸዉ፡፡ ‹‹አርረድ ዐለል ጀህምያ ወዝዘናዲቃ›› እና ‹‹ሪሳለቱል እስጦኽሪ›› የተሰኙ ኪታቦች በታላቁ ሰዉ ስም ተፈብርከዉ ተሠራጭተዋል፡፡ ኢማም ዘሀቢ ስለኢማም አህመድ አንድ ድርሳን ሲተነትኑ እግረ መንገድ የሁለቱን መጽሀፍት ቅጥፈትነት አስምረዋል፡-

لاَ كَرِسَالَةِ الإِصْطَخْرِيِّ ، وَلاَ كَالرَّدِّ عَلَى الجَهْمِيَّةِ المَوْضُوْعِ عَلَى أَبِي عَبْدِ الله

‹‹በአቡ ዐብደላህ ላይ እንደተቀጠፉባቸዉ ‹ሪሳለቱል እስጦኽሪይ›› እና ‹አርረድ ዐለል ጀህምያ› መጽሀፍት (ይህኛዉ የተቀጠፈ አይደለም)፡፡››[1]

የዑለሞችን ሥራዎች የመበረዝና የመከለስ፣በነርሱ ስም ኪታብ የማተምና የማጭበርበር ልምምድ ወደሀገራችን ተዛምቶ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የተዘጋጀዉ የቅዱስ ቁርአን ትርጉም ተመሳሳይ ወንጀል ተፈጽሞበታል፡፡ በተለይም ወንጀሉ ያተኮረዉ ‹ሲፋቱል ኸበርያ› በሚል ስያሜ በሚታወቁ በአሻሚ የቁርአን ገለጻዎች ላይ ሲሆን፣ በሀገራችን ለምዕተ ዓመታት ሲሰጥ የኖረዉን የአህሉሱና ዐቂዳ መሠረት በማድረግ የተተረጎሙ አንቀጾችን ይዘት በመቀየር ጣኦታዊ ቃና እንዲላበሱ ተደርጎ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የተጅሲም ጣኦታዊነት አቀንቃኝ ተደርገው ተስለዋል። የዚህ ቅጥፈትና ሸፍጥ ባለቤት ‹‹ዳሩ ሰላም አሳታሚና አከፋፋይ›› የተባለ በሳዉዲ ዐረብያ ሪያድ የሚገኝ ድርጅት ነዉ፡፡ የሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብንና የሸኽ ሰይድ ሷዲቅን ስም ተጠቅሞ ባሳተመዉ ‹‹የክቡር ቁርአን መልዕክተ-ትርጉም›› የተሰኘ መጽሀፍ[2] ዉስጥ የበርካታ አንቀጾችን ትርጉም በማዛባት በሸኽ ሙሀመድ ሳኒና በባልንጀሮቻቸዉ ላይ ቅጥፈት ፈጽሟል፡፡ ጥቂት ናሚናዎችን ለማሳየት ያህል፡-

1. ‹‹ዐለል ዐርሽ እስተዋ›› ለሚለዉ ሀረግ ሁለቱ ሊቃዉንት በሁሉም ቦታዎች የሰጡት ትርጉም ‹‹(ልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ›› የሚል መሆኑ ይታወቃል፡፡[3] ይህ ማለት ሁለቱ ሊቃዉንት ለአላህ የመኖሪያ አድራሻና አቅጣጫ ከመስጠት ታቅበዋል ማለት ነዉ፡፡ የትርጉማቸዉ መነሻ የሰለፉ የቁርአን ተንታኝና የተፍሲር ሊቃዉንት ሸኽ የሆኑት የኢማም እብኑ ጀሪር ጦበሪ (እስከ 310 ዓ፣ሂ) ተከታዩ አፈታት መሆኑ ግልጽ ነዉ፡-

علا عليها علوّ مُلْك وسُلْطان، لا علوّ انتقال وزَوال

‹‹በርሷ ላይ የመንቀሳቀስና ስፍራ የመልቀቅ ሳይሆን የንግስናና የስልጣን ከፍታን ከፍ አለ፤››[4]

ጦበሪ ለዚህ አፈታት መሠረት ያደረጉት "ዐላ ወርተፈዐ" የሚለውን የታቢእ ትውልድ ተፍሲር መሆኑ ከኪታባቸው ውስጥ ተመልክቷል። ዳሩ ሠላም ማተሚያ ግን -መነሻዉ ምንም ይሁን ምን- የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒን ትርጉም በየስፍራዉ እየተከታተለ በመለወጥ አጭበርብሯል፡፡ ይህ ተቋም ለዚህ ገለጻ በየቦታዉ ያሰፈረዉ መልእክት እንዲህ ይላል፡-

‹‹ከዐርሹ በላይ ሆነ፤(የርሱን ክብር በሚመጥን መልኩ)፤››[5]

በቀሪዎቹ ተመሳሳይ አንቀጾች ላይም ተመሳሳይ ሸፍጦች ፈጽሟል፡፡ ለአልአዕራፍ 54፣ ለአርረዕድ 2፣ለጦሀ 5፣ለአልፉርቃን 59፣ለአስሰጅዳህ 4 እና ለአልሀዲድ 4 የተሰጡ ትርጉሞችን ከገጽ 226፣352፣445፣521፣594 እና 785 ላይ ይመልከቱ፡፡ የዚህ ጽሁፍ አላማ ሸፍጥና ማጭበርበርን ማሳየት እንጅ ከሁለቱ አስተሳሰቦች የትኛዉ ትክክል ነዉ? ለሚለዉ ጥያቄ መልስ መስጠት አይደለም፡፡ እርሱን የተመለከተ ሰፊ ሥራ ‹‹አል-ዑሉዉ›› በሚል ርእስ የተዘጋጀ በመሆኑ ከዚያ ላይ በስፋት የምታገኙት ይሆናል፡፡

2. አልሙልክ 16ን እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የፈሰሩት እንደሚከተለዉ ነዉ፡-

‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለን (ሠራዊት) በናንተ ምድርን ቢደራርብባችሁ ወዲያዉም እርሷ የምታረገርግ ብትሆን ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?)››

ዳሩ ሰላሞች ግን ‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለን (ሠራዊት)›› የምትለዋን ክፍል ቆርጠዉ በማዉጣት፡- ‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለዉ (አላህ) በምትል ሀረግ ተክተዋታል፡፡[6]

በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ግንዛቤ መሠረት ለአላህ ቦታና አቅጣጫ መስጠት እርሱን ከፍጡራን ጋር ማመሳሰልና የቦታና የአቅጣጫ ከጃይ ማድረግ ስለሆነ አግባብ ባለመሆኑ ‹‹በሰማይ ዉስጥ›› የተባሉት ‹‹የአላህ ሠራዊት ወይም መላእክት›› እንጅ አላህ አይደለም፡፡ ይህን አፈታት የቀዱት ከተዉሂዱ ሊቅ ከኢማም ማቱሪዲ (እስከ 333 ዓ.ሂ)፣ እንዲሁም ከኢማም ቁርጡቢ፣ከኢማም ጀላሉዲን ሱዩጢ፣ ከኢማም መሀሊና መሰል የቁርአን ትንታኔዎች መሆኑ እሙን ነዉ፡፡[7]

በዳሩ ሰላሞች ዐቂዳ መሠረት ደግሞ አላህ ከሰማየ ሰማያት በላይ መሆኑ የእምነታቸዉ መሠረት ነዉ፡፡ እንደፈለጉ ማመን መብታቸዉ ሆኖ እምነታቸዉን በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ስም ማሰራጨት ግን በዕዉቀት ላይ የተፈጸመ ሸፍጥ ነዉ፡፡

3. ‹‹ዐይን›› የሚለዉ ቃል ከአላህ ጋር ተያይዞ በተገለጸባቸዉ ቦታዎች ሁሉ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹ጥበቃ/እንክብካቤ›› በማለት ከአካል ክፍልነት ዉጭ የተረጎሙት ሲሆን የዕምነታቸዉ መሠረት ለአላህ የአካል ክፍሎችና ቅርጽ ማላበስ ጣኦታዊነት በመሆኑ የሚጸየፈዉ የሰለፎች አስተሳሰብ ነዉ፡፡ ኢማም አቡሀኒፋ (እስከ 150 ዓ.ሂ) የሚከተለዉን ዐቂዳ አስተምረዋል፡-

الثَّابِت بِلَا جسم

‹‹(አላህ) ያለ ‹ጅስም… ህልዉናዉ የጸና አምላክ ነዉ፡፡››[8]

ጅስም ማለት ከተለያየዩ የአካል ክፍሎች የተዋቀረ ነገር ማለት ነዉ፡፡[9]

ኢማም ጦሀዊ (እስከ 321 ዓ.ሂ) በርሳቸዉ ዘመንና ከርሳቸዉ በፊት የነበረዉን የሰለፍ አህሉሱና ዐቂዳ ሲያብራሩ ፡-

وَتَعَالَى عَنِ الْحُدُودِ وَالْغَايَاتِ وَالْأَرْكَانِ وَالْأَعْضَاءِ وَالْأَدَوَاتِ

‹‹/አላህ/ ከገደብና ወሰን፣ከአካል ክፍሎችም (ዉቅርነት) የጸዳ ነዉ፤››[10]

በነዚህ ሁለት የሰለፍ ሊቃዉንት የዐቂዳ ትምህርት መሠረት የትኛዉም የቁርአን አንቀጽ በዚህ አግባብ ለአላህ አካላዊ ቅርጽነና ይዘት ከማላበስ በጸዳ መልኩ መፈሰር አለበት ማለት ነዉ፡፡ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ከዚህ የሰለፎች ዐቂዳ በመነሳት ይህንና መሰል አንቀጾችን ከአካላዊ ቅርጽና ገጽታ ዉጭ በሆነ መልኩ የፈቱበት መንገድ ከእብን ዐባስ[11] ቀታዳ[12] ቁርጡቢ[13] ነሰፊም[14] በይዷዊ[15] በገዊ[16] እብን ዐጥያ[17] እና ሌሎች የተፍሲር ሊቃዉንት ገለጻዎች የተቀዳ ነዉ፡፡

ዳሩሰላም የተሰኘዉ ተቋም ግን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን ከአካል ክፍልነት የጸዳ ፍች ቀይሮ ‹‹አይን›› በማለት አካላዊ ትርጉም አላ በነዚህ ዑለሞች ስም አሰራጭቶታል፡፡[18]

4. እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹የዱ ላህ›› እና መሰል ገለጻዎችን የአካል ክፍል በመምሰል ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣዉንና ከዑለሞቻቸዉ የተማሩትን ዐቂዳ የሚጻረር መስሎ በተሰማቸዉ ቦታ ሁሉ ላይ ‹‹የአላህ ሀይል›› ወይም ‹‹እጅ›› ብለዉ በቅንፍ ዉስጥ ‹‹ሀይል›› በማለት ከአካል ክፍል በራቀ መልኩ የተረጎሙት ሲሆን[19] የዳሩሠላም እትም ግን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒን ዐቂዳ ለማጽናት እጅግ ጠቃሚ የሆኑትን በቅንፍ ዉስጥ የተቀመጡ ቃላት በማስወገድ ይዘቱ አካላዊ ገጽታ እንዲላበሱ አድርጓል፡፡[20]

5. ‹‹የሚን›› የሚለዉ ቃል ከአላህ ጋር ተገናኝቶ ሲመጣ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹ሀይል›› ተብሎ የተተረጎመ ሲሆን በዳሩ ሰላም ተቋም ግን ‹‹ቀኝ እጁ›› በሚል ተተክቶ የአካል ክፍል ምስል እንዲይዝ ተደርጓል፡፡[21]

አላህን ከተለያዩ የአካል ክፍሎች የተዋቀረ የሚያስመስሉት የቁርአንና የሀዲስ መልእክቶች በምን አግባብ መቃኘት እንዳለባቸዉ የሚያሳይና ከዚህ ዉጭ በሆነ አፈንጋጭ አቅጣጫ የተደረገዉ የአስተሳሰብ ጉዞ በእስልምና ላይ የለጠፈዉን ነዉር የሚተነትን ‹አል ወሰንያ-በእስልምና ስም የተስፋፋ ጣኦታዊነት›› በሚል ርእስ መጽሀፍ የተዘጋጀ በመሆኑ በቅርቡ ከአንባብያን እጅ የሚገባ ይሆናል፡፡ በመስኩ የተስተዋሉ ብዥታዎችን ያጠራል ተብሎ ይታመናል፡፡

ዳሩ ሰላም በተሰኘዉ ድርጅት አማካይነት በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ የቁርአን ትርጉም ላይ የተፈጸሙ ማጭበርበሮች በርካታ ቢሆኑም ለአብነት ያህል ከላይ የተዘረዘሩት በቂ ናቸዉ፡፡ የማጭበርበሩ ዓላማ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን የቁርአን ትርጉም እነርሱ ከሚያምኑበትና ከኖሩለት የዐቂዳ አስተሳሰብ ዉጭ የሆነ ገጽታ በማላበስ ማህበረሰብን ማደናገርና ስሁት አስተሳሰቦችንና ዐቂዳዎችን በታላላቅ ስብእናዎቻችን ስም ማሰራጨት ነዉ፡፡

ከዉስጥ ከተደረጉ በርካታ ለዉጦችና ማጭበርበሮች በተጨማሪ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ያልሆነ 45 ገጽ ያህል የመግቢያ ሀተታ፣እንዲሁም በየገጹ የነርሱን ዕምነት የሚጻረሩ[22] የግርጌ ማስታወሻዎች ተጨምረዉበታል፡፡[23] ሀተታዉ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን እምነት (ዐቂዳ) የሚጻረር የተዉሂድ ግንዛቤን፣የሸሀዳን ትርጉም፣የኩፍር፣የሽርክና የኒፋቅ ትንታኔዎችን፣እንዲሁም የእየሱስን ማንነትና ተመልሶ መምጣት፣ነብዩ ሙሀመድ በመጽሀፍ ቅዱስና የስቅለት ጉዳይን የተመለከቱ ጭብጦች ተካተዉበታል፡፡ ሀተታዉም ሆነ የግርጌ ማስታወሻዎች ዕዉነትን ከግድፈት የቀላቀሉ ሲሆን፣ መጀመሪያዉኑ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ሥራ ዉስጥ መካተት አልነበረባቸዉም፡፡ መካተታቸዉ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም የአሳታሚ ድርጅቱ ወይም የሌሎች ግለሰቦች ሀሳቦች መሆናቸዉ በማያሻማ ሁኔታ መገለጽ ነበረበት፡፡ ይህ ሳይደረግ መቅረቱ አንባብያን ሀተታዉንና የግርጌ ማብራሪያዎችን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ዕምነትና ሀሳብ አድርገዉ እንዲቆጥሩ እድል ከፍቷል፡፡ ይህ ደግሞ በነኝህ ሊቃዉንት ስም የነርሱ ያልሆነን ሀሳብ በማሰራጨት ማጭበርበር ይሆናል፡፡

በጥቅሉ መጽሀፉም ሆነ ድርጅቱ፣ እንዲሁም መሰል ድርጅቶች ዕምነት የማይጣልባቸዉ ሸፍጠኞች በመሆናቸዉ አስፈላጊዉ ሁሉ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ በዚህ አጋጣሚ ማሳሰብ እወዳለሁ፡፡ የዚህን የቁርአን ትርጉምና የተፈጸሙበትን ሸፍጦች በሙሉ ነቅሶ በማዉጣት በታላላቅ ዑለሞቻችን ስም ነዉሮችና አፈንጋጭ አስተሳሰቦች እንዳይሰራጩ መከላከልና ማህበረሰቡን ማስጠንቀቅ ተገቢ ነዉ፡፡

በሌሎች መጽሀፍት ላይ በተለያዩ ድርጅቶች፣በተለይም መክተበቱ ሻሚላ በተሰኘዉ አፕሊኬሸን አማካይነት የተፈጸሙ ሸፍጦችን ወደፊት የምናይ ይሆናል፡፡ ለማንኛዉም ‹ዳሩ ሰላም› ያለዉ ምርጫ ሁለት ነዉ፡፡ አንደኛዉ ያለአግባብ የለወጣቸዉን አንቀጾች ወደነበሩበት መልሶ መጽሀፉን በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ስም ማሳተም ወይም የነርሱን ስመ ሰርዞ የራሱን አዲስ የትርጉም መጽሀፍ ማሳተም፡፡ አሁን ያለዉ ይዘቱና ድርጊቱ ግን በሰዎች ስም የማያምኑበትን ዐቂዳና አስተሳሰብ የማሰራጨት ወንጀልና በህግ የሚያስጠይቅ አጭበርባሪነት መሆኑ ጥርጥር የለዉም፡፡ አስተሳሰብን በጠንካራ መረጃዎች እንጅ በሸፍጥና ጭበርበር ለማሰራጨት ከመሞከር የበለጠ የሀሳብ ምክነት የለም፡፡

[1] ሸምሱዲን ዘሀቢ፣ሲየር አዕላመ ኑበላእ፣ሙአሰሰቱ ሪሳላ፣ሁለተኛ ዕትም 1985፣ካይሮ፣ 11/286-287

[2] የመጀመሪያ እትም በፈረንጆች 2010

[3] ለአልአዕራፍ 54፣ዩኑስ 3፣አርረዕድ 2፣ጦሀ 5፣አልፉርቃን 59፣አስሰጅዳ 4 እና አልሀዲድ 4 የተሰጡ ትርጉሞችን ይመልከቱ፤

[4] ያለፈዉ ምንጭ

[5] ለዩኑስ 3 የተሰጠ ትርጉም ገጽ 295

[6] ገጽ 821 ለአንቀጹ የተሰጠዉን ትርጉም ይመልከቱ፤

[7] ተፍሲር ማቱሪዲ 10/117፣ተፍሲር ቁርጡቢ 18/215፣ተፍሲር ጀላለይን ገጽ 756

[8] ፊቅሁል አክበር ገጽ 4

[9] አልእቅቲሳድ ፊልእዕቲቃድ ሊልገዛሊ ገጽ 33

[10] ዐቂደቱ ጦሀዉያ ገጽ 5

[11] ተፍሲር እብን ከሲር 4/349

[12] ተፍሲር ቁርጡቢ 11/197

[13] ያለፈዉ ምንጭ 11/196

[14] ተፍሲር ነሰፊ 2/364

[15] ተፍሲር በይዳዊ 4/27

[16] ተፍሲር በገዊ 5/272

[17] ተፍሲር እብን ዐጥያ 4/44

[18] ለጦሀ 39፣ሁድ 37 እና አጥጡር 48 የተሰጡ ትርጉሞችን ገጽ 447፣319፣762 በቅደም ተከተል ይመልከቱ፤

[19] አልፈትህ 10፣ሷድ 75፣ያሲን 71 ለአብነት ይመልከቱ፡፡

[20] ለአልፈትህ 10፣ሷድ 75፣ያሲን 71 የተሰጡ ትርጉሞችን ገጽ 740፣659፣638 ይመልከቱ

[21] ለአዝዙመር 67 የተሰጠዉን ትርጉም ገጽ 671 ይመልከቱ፤

[22] ለምሳሌ ገጽ 804 ህዳግ ቁጥር 1 ይመልከቱ፤

[23] የላቲን ቁጥር ገጽ22-

20/10/2025

💔

መረጃን ስለማጥራት••••••••••••••••ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ ኃይሌ ጋርመንት ዝቅ ብሎ ሰፈራ የሚገኘው ባለ 1000 ካሬ ቅይጥ የመኖሪያ ቦታ የነበረውን ይዞታቸው ወደ መካነ መቃ...
20/10/2025

መረጃን ስለማጥራት
••••••••••••••••
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ ኃይሌ ጋርመንት ዝቅ ብሎ ሰፈራ የሚገኘው ባለ 1000 ካሬ ቅይጥ የመኖሪያ ቦታ የነበረውን ይዞታቸው ወደ መካነ መቃብር እንዲቀየር ሐምሌ 20/2013 ዓ•ል በተፃፈ ደብዳቤ ለአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በጠየቁት መሰረት አስተዳደሩ ነሐሴ 5/2013 ዓ• በተፃፈ ደብዳቤ በሙፍቲ ጥያቄ መሰረት ይዞታውን ከቅይጥ መኖሪያነት ወደ መካነ መቃብርነት ለውጦላቸዋል።

በመሆኑም ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ በዛሬው እለት የቀብር ሥርአታቸው የሚፈፀምበት ቦታ ከ5 አመት በፊት የመቃብር ስፍራ እንዲሆን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህጋዊ ፈቃድ የተሰጠው መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። ስለሆነም ተቀዳሚ ሙፍቲ የሚቀበሩት በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሳይሆን ህጋዊ በሆነ የመቃብር ስፍራ ነው።

ይህን መረጃ ሼር በማድረግ እንተባበር

19/10/2025

ኢና ሊላሂ ወዒና ዒለይሂ ራጂዑን 😭

18/10/2025

Update ‼

ሸይኻችን ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ኡመር እንድሪስ የጤና ሁኔታቸው ሰሞኑን ከነበረበረት ሻል ያለ እና ለውጥ ያላቸው መሆኑን እየገልፅን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሸኻችን እያደረገ ያለውን የዱዓ እና የሰደቃ መርሃግቡርን አለህ ሙሉ በሙሉ አፍያ እስክያደርግልን እንድንቀጥል እና በዱዓ እንድንበራታ በዓለህ ስም ጥሪ እናቀርባለን።

@ኑር መስጂድአሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ። ታላቁ ዓሊም ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ዑመር እንድሪስ የጤና እክል አጋጥሞዋቸው ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ መላው ሙስሊም ማ...
15/10/2025

@ኑር መስጂድ
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ።

ታላቁ ዓሊም ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ዑመር እንድሪስ የጤና እክል አጋጥሞዋቸው ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ መላው ሙስሊም ማህበረሰብ የ ኢትዬጵያ ህዝብ በየ ቤቱ በየ መስጂዱ በየ ሃሪማዎቻችን የያሲን እና የዱዓ ፕሮግራም በማዘጋጀት አላህ አፊያቸውን እንዲመልስልን ዱዓ እንድናደርግ በዓላህ ስም እንጠይቃለን ።

አላህ ሙሉ አፊያቸውን ይመልስልን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አርዱል ሀበሻ-Ardul habesha posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አርዱል ሀበሻ-Ardul habesha:

Share