የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association

የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association ይህ ፔጅ የኸውፉሏህ ወጣት ጀመዓ የሚሰራቸውን ስራዎች እና ዲናዊ ጉዳዮች የሚለቀቁበት ነው!

09/05/2026

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

በለፉት ረጅም ዓመታት በኑር መስጂድ ውሰጥ መስጂዱን በተለያዩ ዘርፎች ይካድሙ የነበሩት ሸይኽ ኸድር ኡመር ወደ አኼራ ተሻግረዋል።አላህ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለመላው ማህበረሰብ መፅናናትን ይወፍቅልን።እሳቸውምንም አላህ በሰፊው ፊርደውሰል ጀና ይቀበልልን 🙏😥

ሰበር መረጃ•••••••••የአዲስ አበባ መጅሊስ በአዲስ መልክ አርቅቆ ያዘጋጀው ህገ መጅሊስ ለሱፍያው ማህበረሰብ ከባድ አደጋ ያዘሉ አንቀፆችን ማካተቱ ለማወቅ ተችሏል። የአዲስ አበባ መጅሊስ ...
23/04/2026

ሰበር መረጃ
•••••••••
የአዲስ አበባ መጅሊስ በአዲስ መልክ አርቅቆ ያዘጋጀው ህገ መጅሊስ ለሱፍያው ማህበረሰብ ከባድ አደጋ ያዘሉ አንቀፆችን ማካተቱ ለማወቅ ተችሏል። የአዲስ አበባ መጅሊስ የሱፍያውን ማህበረሰብ ህልውና ለማክሰም ቆርጦ ተነስቷል። በህገ መጅሊሱ የተካተቱ እና የሱፍያው ማህበረሰብ ለማጥቃት የተዘጋጁ አንቀፆች ከታች በፎቶው ውስጥ ጥቂቶቹ የተቀመጡ ሲሆን በአጭሩ ሲገለፁ

1) መስጂድ ውስጥም ሆነ ከመስጂድ ውጭ የሚገኙ መድረሳ እና የሒፍዝ ማእከላት በመጅሊሱ ሥር ይካተታሉ ይላል

2) ከኢማም እና ከሙአዚኖች ውጭ ያሉ የመድረሳ ኡስታዞች በመጅሊሱ ቁጥጥር ስር ሆነው ያስተምራሉ የመጅሊሱን ትእዛዝ የማክበር ግዴታ አለባቸው ይላል

3) ዑለማዎች ኡስታዞች እና ዱዓቶች የሚያስተምሩትን ትምህርት የሚቀረፀው ወይስ ከሪክለሙ የሚዘጋጀው በመጅሊሱ ነው ይላል

4) ወቅፍ ሆነ በናዚርነት የሚተዳደሩ መስጂድና መድረሳዎች መጅሊሱ በፈለገ ሰአት ናዚርነታቸው እንዲሻር አድርጎ መስጂድና መድረሳውን በመጅሊሱ ቁጥጥር ስር ማድረግ መብት አለው ይላል

እነዚህ እና መሰል ሱፍያውን ማህበረሰብ በቀጥታ ለማጥቃት ታስቦባቸው የተዘጋጁ አንቀፆች የሱፍያውን የእምነት ነፃነት በመንጠቅ ህገ መንግስታዊ መብቱን ለመቀማት የተዘጋጀ ህገ መጅሊስ ነው። በመሆኑም ሱፍያው ማህበረሰብ ይህ ኢ-ህገመንግስታዊ የሆነ ህገ መጅሊስ እንዳይፀድቅ ድምፁን ማሰማት የሚገባው ሲሆን መስጂድ እና መድረሳወን ከምንጊዜውም በበለጠ ነቅቶ በመጠበቅ የእምነት ነፃነቱን ማስከበር ይኖርበታል።

መንግስት እና ይህ ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታችሁ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የአዲስ አበባ መጅሊስ ያረቀቀው ህገ መጅሊስ የሙስሊሙን ማህበረሰብ አንድነት የሚበትን፣ በሙስሊሙ መሀከል ሁከትና ብጥብጥ የሚያስነሳ፣ መስጂድና መድረሳዎች የሁከት ማእከል እንዲሆኑ የሚያደርግ እና የዜጎችን የእምነት ነፃነት የሚከለክል በመሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በማን አለብኝነት ወሀቢዝምን በግድ ለማጥመቅ የተዘጋጀውን የአዲስ አበባ መጅሊስ ገደብ ይበጅለት ዘንድ አጥብቀን እንጠይቃለን
Abiy Ahmed Ali
Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር
Ethiopian Federal Police
Addis Ababa Police
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር
የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

20/04/2026

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን😭
የመስጂዳችን መስራችና ኢማማችን የነበሩት ታላቁ ሸኽ ሙሀመድ ሸሪፍ ወደ አኼራ ሄደዋል😭 አላህ ይዘንላቸው🤲🤲🤲
ቀብር ዙሁር ላይ ቱሉዲምቱ መቃብር

አቃቂ ቃሊቲ የሚገኘው የሲኤምሲ ቅርንጫፍ መድረሳ ታሸገ••••••••••••••••••••••••••••••በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቶታል አካባቢ የሚገኘው ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኘው የሲኤምሲ...
27/03/2026

አቃቂ ቃሊቲ የሚገኘው የሲኤምሲ ቅርንጫፍ መድረሳ ታሸገ
••••••••••••••••••••••••••••••
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቶታል አካባቢ የሚገኘው ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኘው የሲኤምሲ አዳሪ የቁርአን ሂፍዝ ማእከል በዛሬው እለት ከቀኑ 8 ሰአት ላይ ታሽጓል። የቁርአን ሂፍዝ ተማሪዎች ለኢድ በዓል እረፍት ቤተሰብ ለመጠየቅ በሄዱበት በዚህ ሰአት መድረሳው መታሸጉ የመስጂዱ ኮሚቴ መድረሳውን ለመዝጋት አጋጣሚዎችን አድብቶ ሲጠብቅ እንደነበረ ያረጋግጣል። መድረሳው ከተመሰረተ ብዙ አመታት ቢሆንም ወሀቢያ መራሹ መጅሊስ የሾማቸው የመስጂድ ኮሚቴዎች መድረሳው በወሀቢዝም እምነት ካልተጠመቀ መዘጋት አለበት ብሎ በመወሰኑ መድረሳውን በዛሬው እለት አሽገውታል።

ይህ ድርጊት ፍፁም ህገወጥ ከመሆኑ ባሻገር ዜጎች ህገ መንግስቱ ያጎናፀፋቸውን የእምነት ነፃነት የሚፃረር ተግባር በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ፍትህ እንዲያረጋግጡ እንጠይቃለን።

መረጃውን ሼር በማድረግ መድረሳውን ከመዘጋት እናድነው!

ለመላው ጀመዓ በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌙✨መልካም ዒድ! 🕌 🦋عيدكم مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمالكل عام وأن...
19/03/2026

ለመላው ጀመዓ በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
🌙✨መልካም ዒድ! 🕌

🦋عيدكم مبارك
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
كل عام وأنتم بخير🦋

“‘በኒ አደም’ ማለት አደም ብቻ ማለት ነውን ?”🟢 ቁርኣን:- ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር መሆኑን ነው የሚያስተምረው ‼️    አንዳንዶች “ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ይላሉ። ግን ቁ...
26/02/2026

“‘በኒ አደም’ ማለት አደም ብቻ ማለት ነውን ?”

🟢 ቁርኣን:- ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር መሆኑን ነው የሚያስተምረው ‼️

አንዳንዶች “ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ይላሉ። ግን ቁርኣን ግልፅ ቃል አለው፦
📖 «وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ» (ኢስራእ 17:70)
“እኛም የአደምን ልጆች ክብር ሰጠናቸው…”
እዚህ ላይ አላህ “አደምን” አላለም፤ “በኒ አደም” አለ — ይህ ሁሉንም የሰው ዘር ልጆችን ነው የሚያካትተው።

ሙእሚን ብቻ አይደለም፤ ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር ነው።

አደምን ብቻ ቢሆን ኖሮ እንደ «يَا آدَمُ» (2:35) በስሙ ብቻ ይጠራ ነበር።
📖 «يَا نُوحُ» (11:46)
📖 «يَا مُوسَى» (20:11)
📖 «يَا إِبْرَاهِيمُ» (37:104)
እነዚህ አንድ ነቢይን ብቻ ገላጭ ሲሆኑ፤
“بني آدم”ግን የሰው ልጆችን ሁሉን ይገልፃል።

🟢 የመላእክቶቹ ጉዳይም ይህንን ያጠናክራል
📖 (በቀራ 2:30)
መላእክት “ብክለት የሚያስፋፋ ሰው ትፈጥራለህ?” ሲሉ
አላህም እንዲህ አለ፦
«إِنِّي أَعْلَمُ مَا لَا تَعْلَمُونَ»
“እኔ እናንተ የማታውቁትን አውቃለሁ”
ማለትም፦
– ከዚህ ዘር ነቢያት ይመጣሉ
– ሷሊሃን ባሮች ይመጣሉ
– አላህን በነፃ ምርጫ የሚያመልኩ ፍጥረታት ይኖራሉ
ከዚያ በኋላ አደምን ስሞችን አስተማረው (2:31)
መላእክትም ሱጁድ አደረጉ (2:34) — ይህ የሰው የተለየ ክብር ነው።

🟢 እንግዲህ ልዩነት የት ነው?
📖 (ሁጁራት 49:13)
«إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ»
ሰዎች በመሰረታዊ ሰውነት ክቡር ናቸው፤
ግን በተቅዋ ደረጃ ይለያያሉ።
✔ ፍጥረታዊ ክብር → ለሁሉም ሰው
✔ የደረጃ ልዩነት → በእምነትና በተቅዋ
🔎 መደረሻ
“ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ማለት
«وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ» ከሚለው ግልፅ አያ ጋር አይጣጣምም።

ሰው በመፈጠሩ ክቡር ነው፤
በተቅዋ ክብሩ ይጨምራል፤
በክፉ ስራ ደረጃው ይወርዳል —
ግን መሰረታዊ የሰዉነት ክብሩ አይሰረዝም።

#ቁርኣን #በኒአደም #እስልምና

ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋርقال عبد الله بن عباس رضي الله عنهما:"كان رسولُ اللهِ ﷺ أجودَ الناس، وكان أجودَ ما يكونُ في رمضان حين يلقا...
22/02/2026

ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋር
قال عبد الله بن عباس رضي الله عنهما:
"كان رسولُ اللهِ ﷺ أجودَ الناس، وكان أجودَ ما يكونُ في رمضان حين يلقاه جبريل، وكان جبريل يلقاه في كل ليلة من رمضان فيدارسه القرآن، فلرسول الله ﷺ حين يلقاه جبريل أجودُ بالخير من الريح المرسلة."
— رواه محمد بن إسماعيل البخاري
ومسلم بن الحجاج“

የአላህ መልእክተኛﷺ ከሰዎች ሁሉ በጎ እጅግ ለጋስ ነበሩ። በተለይም በረመዳን ወር፣ ከጂብሪል ጋር ሲገናኙ ከሁሉ ይበልጥ ለጋስ ይሆኑ ነበር። ጅብሪልም በረመዳን ሁሉ ሌሊት ይመጣቸው ነበር እና ቁርአንን አብረው ይመላልሱ (ይደጋገሙ) ነበር። እንግዲህ መልእክተኛው ﷺ ጅብሪልን በሚገናኙበት ጊዜ ከተላከ ነፋስ ይልቅ በበጎ እጅግ ይለግሱ ነበር።”
…......….......…....…...….............
በየአመቱ ረመዳን ወር መምጣቱን በማስመልከት" ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋር " በሚል መፈክር የሚዘጋጀው ለሚስኪኖች የአስቤዛ እና የፆም ማፍጠሪያ የማጋራት መርሀ ግብር ተከናወነ።

የእደላ መርሀ ግብሩ በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም እና በአል ዒምራን መስጂድ ወጣት ጀመዓ አማካኝነት የተከናወነ ሲሆን።

በእደላው በአካቢቢው የሚገኙ200 ቤተሰቦችን ማዳረስ ተችሏል ።

መሰል መርሀ ግብሮች የእለታዊ ፍጆታን ለቤተሰቦቹ ከማቅረብ በተጨማሪ የማህበረሰብን እርስ በርስ መደጋገፍ እና መተሳሰብ የሚያጠናክር ተግባር ነው

በመሆኑም ይህ የዘንድሮ ዓመት የሁለተኛ እደላ እንደመሆኑ ቀጣይ መርሀ ግብሮች ላይ ሁሉም ማህበረሰብ ይሳተፍ ዘንድ ጥሪ ለማቅረብ እንወዳለን።
አል-ዒምራን Cmc የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም

አዲስአበባ እና አካባቢዋ የ1447 ዓ.ሂየ2018 ዓ.ል ረመዳን የሱሁር፣ የኢፍጣር እና የሰላት ሰዓዕ ፕሮግራም
18/02/2026

አዲስአበባ እና አካባቢዋ የ1447 ዓ.ሂ
የ2018 ዓ.ል ረመዳን የሱሁር፣ የኢፍጣር እና የሰላት ሰዓዕ ፕሮግራም

ረመዳን ሙባረክ 🌙 🌙 🌙 🌙 ተራዊህ ዛሬ ይጀመራል!!!በራህመቱ ከዚህ ከተባረከ ወር ደርሰናል። ከኸይራቶቹ ሁሉ እንቋደስ ዘንዳ አሏህ እድሜን ሰጥቶናል። ሷልሆች እንደፆሙት እና እንዳሳለፉት ም...
17/02/2026

ረመዳን ሙባረክ 🌙 🌙 🌙 🌙

ተራዊህ ዛሬ ይጀመራል!!!

በራህመቱ ከዚህ ከተባረከ ወር ደርሰናል። ከኸይራቶቹ ሁሉ እንቋደስ ዘንዳ አሏህ እድሜን ሰጥቶናል።

ሷልሆች እንደፆሙት እና እንዳሳለፉት ምንፆም ምናሳልፍ አሏህ ያርገን።
በድጋሚ ለዚህ ተናፋቂ ወር በሰላም አደረሳችሁ።

የርዝቅ የፈረጃ የፈትህ የሰላም የበረካ ወር አሏህ ያርግልን።

17/02/2026

ስለ ረመዷን እና የተራዊህ ሰላት የተዳሰሰበት ነው!
በኡስታዝ ሸምሰዲን ሀምዛ ሀፊዘሁሏህ
ረመዷናችን ራህመቱን መጝፊራውን ዒትቁ ሚነ ናር የምናገኝበት ያድርግልን🤲
የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association

የታላቁ ኑር መስጂድ የመግብያ በሮች የመስጂዱ ምልክት እና የበላይ ጠባቂ በሆኑ መሻይኽ ዑለሞች ስም ተሰየሙ። የኑር መስጂድ አሰስተዳደር ኮሚቴ ከኑር መስጂድ ወጣት ጀምዓ ጋር በመተባበር የኑር...
15/02/2026

የታላቁ ኑር መስጂድ የመግብያ በሮች የመስጂዱ ምልክት እና የበላይ ጠባቂ በሆኑ መሻይኽ ዑለሞች ስም ተሰየሙ።

የኑር መስጂድ አሰስተዳደር ኮሚቴ ከኑር መስጂድ ወጣት ጀምዓ ጋር በመተባበር የኑር መስጂድ መግብያ በሮችን በመስጂዱ እና በሃገረችን ታላላቅ መሻይኾች በሆኑት በክብር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር ኢድሪስ አላህ ይዘንላቸው እና በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሃመድ ዑመር (ሰብዩ) ተስይሞዋል ። በዚህ መሰረት የኑር መስጂድ በር ቁጥር 2 በክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ዑመር እንድሪስ የተሰየመ ሲሆኑ እኚህ ታላቅ አሊም ይህንን በር ላለፉት 50 አመታት ወደ መስጂዳችን በሚገቡበት ወቅት ይጠቀሙበት የነበረ በር መሆኑን የተገለፀ ሲሆን እንዲሁም በተመሳሳይ መልኩ በር ቁጥር 4 ደሞ እንዲሁም አላህ ሀያታቸውን ያቆይልን የመስጂድዳችን ምልክት በሆኑት ታላቁ ዐሊም ሸይኽ ሙሀመድ ዑመር ( ሰብዩ ) የተሰየመ ሲሆን ይህ በርም ታላቁ ዓሊም ሸኽ ሞሃመድ ኡመር (ሰብዩ) ወደ መስጂድ በሚገቡበት ወቅት የሚጠቀሙበት በር መሆኑን በመግለፅ እነዚህ ሁለት በሮች ከዑለሞቹ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው እና ለነሱ ማስታወሻ ይሆኑ ዘንድ መሰየማቸውን በፕሮግራሙ ላይ ተገልፆዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የመስጂዳችን ኢማሞች ሙአዚኖች ሸይኽ ሙሀመድ ሰብዩ የክቡር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር ልጆች ቤተሰቦች እንዲሁም ደረሶቻቸው በተገኙበት ተከናውኖዋል ።
የኑር መስጂድ ወጣት ጀመዐ

Address

Saris, Bhere Tsige
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share