የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association

የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association ይህ ፔጅ የኸውፉሏህ ወጣት ጀመዓ የሚሰራቸውን ስራዎች እና ዲናዊ ጉዳዮች የሚለቀቁበት ነው!

ከሀገራዊ ምክክር መድረክ የተገፋው ሙስሊም ማህበረሰብ•••••••••••••••••••••••••••••የኢትዮጵያ ሙስሊም ታሪክ ባለቤት የሆነ፣ ሀገር ስትሰራ አብሮ የሰራ፣ በአራቱም አቅጣጫ ታሪክ...
01/08/2026

ከሀገራዊ ምክክር መድረክ የተገፋው ሙስሊም ማህበረሰብ
•••••••••••••••••••••••••••••
የኢትዮጵያ ሙስሊም ታሪክ ባለቤት የሆነ፣ ሀገር ስትሰራ አብሮ የሰራ፣ በአራቱም አቅጣጫ ታሪክ እሴት ያለው፣ ለሀገር ሰላም እና ልማት ቅድሚያ ሰጥቶ መስዋእትነት ሲከፍል የኖረው ነባሩ ሙስሊም ሱፍይ ማህበረሰብ ሀገራዊ ኮሚሽን ከተቋቋመበት ቀን ጀምሮ ለበርካታ ጊዜያት እንደ ሀገር እንደ ሙስሊም ማህበረሰብ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ያላቸውን ጥያቄዎች ለኮሚሽኑ በደብዳቤ በአካላዊ ውይይትም አቅርቧል።

ሀገራዊ ምክክር መድረክ ሲጀመር በዋናነት ተሳታፊ እንዲሆን ማድረግ ግዴታ መሆን የነበረበት ሙስሊም ማህበረሰብ ስልታዊ በሆነ መንገድ ከመድረኩ ተገፍቷል። በአንፃሩ በኢትዮጵያ ሙስሊም ታሪክ ከ40 አመት የዘለለ ሚና የሌላቸው፣ ነባር የሙስሊሙ ማህበረሰብ ታሪክ እና እሴቶች ለፖለቲካዊ ፍጆታ ካልሆነ የኔ ነው ብለው የማያምኑ፣ መጅሊሱን በመጠቀም ነባሩን ታሪክ እና እሴት ለማጥፋት ሌት ተቀን የሚሰሩ፣ የብዙሃኑ ሙስሊም ማህበራዊ ውክልና የሌላቸው እስር እና ሚድያ ያገነናቸው ሰዎች በሙስሊሙ ወካይነት ከመድረኩ ተሰይመዋል።

ያለፈውን የሚረሳ የወደፊቱን ይረሳል እንደሚባለው የታሪክ ባለቤት የሆነው ነባሩ ሱፍይ ሙስሊም ማህበረሰብ ያገለለ የምክክር መድረክ ስንኩል እንደሚሆን ሳይታለም የተፈታ ነው። ይህ ዋናው እና የኢትዮጵያን ሙስሊም በቅጡ የሚወክል ህዝብ ከምክክር መድረኩ ገለል እንዲል የተፈለገው ለምንድነው? ይህ ህዝብ ለሰላም ዘብ ከመሆን ለሀገር ቅድሚያ ሰጥቶ ህመሙን ታቅፎ ከመኖር የዘለለ ምን በደል ፈፅሞ ነው የተገፋው? እውን በዚህ ልክ የታሪክ ባለቤት የሆነውን ሙስሊም ማህበረሰብ ገፍቶ ሀገራዊ አንድነት ማምጣት ይቻላል?

የምክክር ኮሚሽኑ ከሃይማኖት ተቋማት ማህበረሰብን የሚወክሉ ሰዎች የመረጠው ሰላም Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር ነው ቢልም ኮሚሽኑ ነፃ እና ገለልተኛ እንደመሆኑ ተገፍተናል ብዙ መከራ እና ስቃይ እየተፈፀመብን ነው ችግራችንን እወቁልን ብሎ በመድረኩ አሳትፉን ብሎ በተደጋጋሚ የጠየቀውን ማህበረሰብ መርሳት እና ጉዳዩን ወደ ሌላ መንግስታዊ ተቋም ማላከክ ተገገቢም ፍትሃዊም አይደለም።

ሰላም ሚኒስትር ሐይማኖታዊ ጉዳዮችን በሚመለከት ትኩረት
ስለሚሰጥ ነባሩ ሙስሊም ሱፍይ ማህበረሰብ እየደረሰበት ያለውን መገፋት እና ስቃይ ከተገቢው በላይ በቂ መረጃ እና ማስረጃ ያለው ቢሆንም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሙስሊም ሹመኞች አፍቃሪ ወሀብያ በመሆናቸው የሱፍዩ ማህበረሰብ ጥያቄ ወደ ላይኛው የመንግስት አካል እንዳይቀርብ አፍነው ከጠረጴዛቸው ሥር በማስቀመጥ በአንፃሩ የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃዎችን ለበላይ አለቆቻቸው በማቅረብ ሱፍይ ሙስሊሙ እየበደሉ እንደሆነ እናውቃለን። እንደ አንድ መንግስታዊ ተቋም መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ለበላይ የመንግስት አካላት ማሳወቅ ሲገባቸው ሙስሊም ሹመኞቹ ከመጅሊሱ ጋር እጅና ጓንት በመሆን የመጅሊሱን በደል መሰወር መርጠዋል።

ነባሩ ሙስሊም ማህበረሰብ እየተፈፀመበት ያለውን የተቀናጀ በደል እና ጭቆና ተገንዝቦ ትግሉን ከዚሁ አንፃር ማስኬድ ይጠበቅበታል። እውነት ትቀጥናለች እንጂ አትበጠስም ዛሬ
ቀኑ ቢጨልም ነገ ብርሃን ይሆናል። ዝንተ ዓለም የዘለቀ የጭቆና ቀንበር የለም በደል ፈፃሚውን ይቀብራል።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

ማህበራችን ነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው አገራዊ የምክክር መድረክ ላይ፣ በተለይም በቀጥታ እኛን በሚመለከተው "4ኛው አጀንዳ (የሃይማኖት ጉዳዮች)" ላይ ተሳታፊ ለመ...
17/07/2026

ማህበራችን ነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው አገራዊ የምክክር መድረክ ላይ፣ በተለይም በቀጥታ እኛን በሚመለከተው "4ኛው አጀንዳ (የሃይማኖት ጉዳዮች)" ላይ ተሳታፊ ለመሆንና የማህበረሰባችንን ድምፅ ለማሰማት ለኮሚሽኑ ይፋዊ የጥያቄ ደብዳቤ አስገብቶ ነበር።

ነገር ግን ከኮሚሽኑ የተሰጠን ምላሽ “በስሩ ያሉ ማህበራትን ለይቶ መጥራትና ዝርዝር ማቅረብ የሰላም ሚኒስቴር ኃላፊነት ነበር” የሚል ነበር። ሰላም ሚንስትርም እንድንሳተፍ አላደረገም። በአሁኑ ሰዓት ይህ የዕርቅ ፕሮግራም እየተካሄደ ቢሆንም ከአምስት አመት በላይ ለሰላም ሚንስትር የ"መብት አስከብሩልን" እና የ"ድረሱልን" ደብዳቤ ሲያጎርፍ የነበረውና በሁሉም አቅጣጫ አሰቃቂ በደል እየደረሰበት የቆዬው የሱፍያ ማህበረሰብ የህዝብን ሰላም አስከብራለሁ ብሎ በተመሰረተው ተቋም ተዘንግቶ ሳይወከል ቀርቷል።

ሀገራዊ ምክክሩ "ሁሉንም ያካተተ" መድረክ ነው እየተባለ፣ በተግባር ግን እንደ ነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር ያሉ በማህበረሰቡ ውስጥ ጥልቅ መዋቅርና ተሰሚነት ያላቸውን ተቋማት በቀጥታ ማስተናገድ አለመቻሉ የምክክሩን አካታችነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ነው። በተለይም የሰላም ሚኒስቴር ሰፊ ተደራሽነት ያለንን ማህበራት ለይቶ ወደ መድረኩ የመጥራት ኃላፊነቱን በአግባቡ አለመወጣቱ እና ይህንን ትልቅ ክፍተት መፍጠሩ እጅግ ያሳዝናል። በቀጥታ እኛን በሚመለከት የሃይማኖት ነጻነት፣ ሴኩላሪዝም እና ታሪካዊ መገፋት/ዕርቅ በሚባሉ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ እንዳንሳተፍ መደረጉ፣ በውይይቱ ላይ ሊንጸባረቅ የሚገባውን የህዝብ ድምፅ የሚያሳጣ ነው።

ይህንን ተጨባጭ ሁኔታ ለውድ አባሎቻችን እና ደጋፊዎቻችን እያሳወቅን፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆኑ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እንዲህ ያሉ የአሰራር ማነቆዎችን ፈትሸው ማስተካከያ ሊያደርጉ እንደሚገባ እናሳስባለን። ማህበራችን ለሀገር ሰላምና ለፍትህ የሚያደርገውን ጉዞ በሌሎች መንገዶች ሁሉ አጠናክሮ ይቀጥላል!

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር
Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር

የሁለት መጅሊስ ጥያቄ ለመንግስት ቀረበ•••••••••••••••••••••••••••••••••ከሀገር አቅፍ አህለሱና ወልጀማዓ አቤቱታ አቅራቢ ኮሚቴለ Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴ...
08/07/2026

የሁለት መጅሊስ ጥያቄ ለመንግስት ቀረበ
•••••••••••••••••••••••••••••••••
ከሀገር አቅፍ አህለሱና ወልጀማዓ አቤቱታ አቅራቢ ኮሚቴ

ለ Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር
ጉዳዩ :- በዕለተ-መውሊድ የተመሰረተው ተቋማችን እንዲመለስልን እና ህገመንግስታዊ የእምነት ነፃነታችን ለማስጠበቅ ተቋም እንድናደራጅ እገዛ እንዲደረግል ስለመጠየቅ

በቀደሙት እልፍ ዘመናት በገጠር የሊቃውንት ማዕከላት/ሃሪማዎች በስልጡን ሀገር-በቀል የተማከለ አደረጃጀት በመላ ሀገሪቱ የእውቀትን ቁንጮዎቹን እየተከተለ በሚዟዟር መናገሻ በኡለማ-መራሹ ሰንሰለታዊ የአመራር መተካካት (ስርዎ ኺላፋ) ለሀገሪቱ አሰባሳቢ ብሔራዊ ማንነት እየፈጠረ በቅብብሎሽ ለትውልዱ የደረሰው ኢስላማዊ አደራ ዘመኑን በዋጀ የትይዩ አደረጃጀት እንዲጠናከር ታልሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጉባኤ መጅሊስ በሚል መጠሪያ ከግማሽ መቶ ዓመት በፊት፣ በዕለተ-መውሊድ፣ በወርሃ-መጋቢት፣ በብሔራዊው የአንዋር መስጅድ የመውሊድ ክብረ-በዓል ላይ የመላው ህዝበ-ሙስሊም የእምነት አስተዳደር ተቋም ሆኖ ተመሰረተ፡፡ በእነ ሐጅ ሙሐመድሳኒ እና በምክትላቸው ተተኪነት እስከተመራበት 1985 ድረስ የህዝበ ሙስሊሙን አደራ ተሸክሞ ከፈተና ጋር የተቻለውን አሳክቷል፤ ያልቻለውን በጥበብ አለዝቦ ተሻግሯል፡፡

በ1987 ዓ•ል ወሃቢ-መር ቡድኖችና ማህበራት እንዲሁም በያኔው ኡስታዝ ሰኢድ አህመድ (አሁን ላይ ሸህ) ከሚመራው ንቅናቄ (ሙነዘማ) እና ከሸሪዓ ፍ/ቤት የአዋጅ አጥኚ ኮሚቴ (ከእነ ግራዝማች ሐዲስ ኑርሁሴን) ጋር በመቃቃሩ በወርሃ የካቲት 1987 የተፈጠረውን መጅሊስ-መርና መንግስት-አገዝ ደም አፋሳሽ እልቂትን ወልዶ የአ/አ ህዝበ-ሙስሊም ለሰቆቃ እንዲዳረግና በመላ ከተማዋ የሚገኙ የአምልኮ ተቋማቱ (ሁሉም መሳጂድ) በተሰናባቹ የሽግግር መንግስት ውሳኔ ለቀናት እንዲዘጉ ሰበብ ሆኖ የታሪክ ጠባሳ በማሳረፉ ማህበረሰቡ በድህረ-ክስተቱ ለመጅሊስ ግድ-የለሽ እንዲሆን ጋብዞ የተዳከመ የሃይማኖት አስተዳደር ተቋም እንዲኖረን መደላድል ፈጥሯል፡፡

ለቅድመ-ለውጡ የዘመነ-ኢህአዴግ የትግበራ ሳንካዎች፣ ለዘመነ-ደርግ ለህግ-ማዕቀፍ ክፍተቶች፣ ለሥርዓተ-አጼው አግላይ በደሎች ስር-ነቀል ህክምና እንዲሰጥ ታልሞ በወርሃ ሰኔ 2012 ለመጅሊስ የተሻለ የህግ ሰውነት የለገሰ ህግ ታውጆ ብስራቱን አጣጥመን ነበር፡፡ ይሁንና ከመንግስትና ከምዕመኑ እሳቤ ውጭ አዋጁ ላልተደነገገለት ተቃራኒ የጥቅለላ/የድፍጠጣ አላማ ውሎ ወታደራዊም ሃይማኖታዊም መንግስት ካልሆነ በስተቀር ሴኩላራዊ ዲሞክራሲያዊ መንግስት ማውጣት የማይችላቸውን የንጥቂያና የሰብኣዊ መብት ገደብ ህግጋትን “ህገ-መጅሊስ” ብለው በሰየሙት ሰነድ የአህለሱና ሱፍይ ሙስሊም ማህበረሰብ የእምነት ነፃነት እየተነጠቀ ይገኛል። ከሐምሌ 11/2014 ጀምሮ ባለው በድህረ-ተቋማዊ ወረራው የጭቆና ፈቃጅ ሆነው ላለፉት አራት ዓመታት ያስተናገድናቸው በደሎች በሰለሞናዊው ሥርወ-መንግስትም ጭምር ያላጣናቸውን የቤት-ለቤት አምልኮንና ትምህርትን እንዲሁም የገጠር ሐሪማ ህልውና እና የበአል አክብሮትን የመሰሉ ነጻነቶች እና ተፈጥሯዊ መብቶች ገፍፈውናል።

የመደበኛውን ህዝበ-ሙስሊም እሴቶች የሚንድ፣ ሀገሪቱን በዱዓና በዒባዳቸው እድሜ ዘመኗን ዋልታና ማገሯ ሆነው ከፈጣሪ ጥበቃ ጋር ያስተሳሰሯት ሀገር-በቀል ኢስላማዊ የብህትውናና የትምህርት ማዕከላትን ህልውና የሚቀለብስ፣ ሁሉንም እስላማዊ የአምልኮ ተቋማት ባለቤትነት ከሉዓላዊ ምዕመናን ዜጎች የሚነጥቅ እና ለ1400 አመታት የቆየውን የሱፍዮችን እምነት በመጅሊሱ አምሳል ወሀቢዝም ለመጠፍጠፍ፣ ሀገራዊ መልክና ቁመና የተላበሰ እሳቤን አክስሞ ለመጤ ባይተዋር እሳቤዎችና ለፈርጀ-ብዙ ብሔራዊ ስብራቶች የሚዳርግ የመጅሊስ ህግ ተዘጋጅቶ አህለሱና ሱፍይ ማህበረሰብ በደል እየተፈፀመበት ይገኛል።

በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ደፍጣጭ እና ጠቅላይ የሆነው መጅሊስ ማህበረሰባችን ላይ እየፈፀመ ያለው ኢ-ህገመንግስታዊ የመብትና የእምነት ነፃነት ጥሰት በርካታ ነው።
የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

09/05/2026

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

በለፉት ረጅም ዓመታት በኑር መስጂድ ውሰጥ መስጂዱን በተለያዩ ዘርፎች ይካድሙ የነበሩት ሸይኽ ኸድር ኡመር ወደ አኼራ ተሻግረዋል።አላህ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለመላው ማህበረሰብ መፅናናትን ይወፍቅልን።እሳቸውምንም አላህ በሰፊው ፊርደውሰል ጀና ይቀበልልን 🙏😥

ሰበር መረጃ•••••••••የአዲስ አበባ መጅሊስ በአዲስ መልክ አርቅቆ ያዘጋጀው ህገ መጅሊስ ለሱፍያው ማህበረሰብ ከባድ አደጋ ያዘሉ አንቀፆችን ማካተቱ ለማወቅ ተችሏል። የአዲስ አበባ መጅሊስ ...
23/04/2026

ሰበር መረጃ
•••••••••
የአዲስ አበባ መጅሊስ በአዲስ መልክ አርቅቆ ያዘጋጀው ህገ መጅሊስ ለሱፍያው ማህበረሰብ ከባድ አደጋ ያዘሉ አንቀፆችን ማካተቱ ለማወቅ ተችሏል። የአዲስ አበባ መጅሊስ የሱፍያውን ማህበረሰብ ህልውና ለማክሰም ቆርጦ ተነስቷል። በህገ መጅሊሱ የተካተቱ እና የሱፍያው ማህበረሰብ ለማጥቃት የተዘጋጁ አንቀፆች ከታች በፎቶው ውስጥ ጥቂቶቹ የተቀመጡ ሲሆን በአጭሩ ሲገለፁ

1) መስጂድ ውስጥም ሆነ ከመስጂድ ውጭ የሚገኙ መድረሳ እና የሒፍዝ ማእከላት በመጅሊሱ ሥር ይካተታሉ ይላል

2) ከኢማም እና ከሙአዚኖች ውጭ ያሉ የመድረሳ ኡስታዞች በመጅሊሱ ቁጥጥር ስር ሆነው ያስተምራሉ የመጅሊሱን ትእዛዝ የማክበር ግዴታ አለባቸው ይላል

3) ዑለማዎች ኡስታዞች እና ዱዓቶች የሚያስተምሩትን ትምህርት የሚቀረፀው ወይስ ከሪክለሙ የሚዘጋጀው በመጅሊሱ ነው ይላል

4) ወቅፍ ሆነ በናዚርነት የሚተዳደሩ መስጂድና መድረሳዎች መጅሊሱ በፈለገ ሰአት ናዚርነታቸው እንዲሻር አድርጎ መስጂድና መድረሳውን በመጅሊሱ ቁጥጥር ስር ማድረግ መብት አለው ይላል

እነዚህ እና መሰል ሱፍያውን ማህበረሰብ በቀጥታ ለማጥቃት ታስቦባቸው የተዘጋጁ አንቀፆች የሱፍያውን የእምነት ነፃነት በመንጠቅ ህገ መንግስታዊ መብቱን ለመቀማት የተዘጋጀ ህገ መጅሊስ ነው። በመሆኑም ሱፍያው ማህበረሰብ ይህ ኢ-ህገመንግስታዊ የሆነ ህገ መጅሊስ እንዳይፀድቅ ድምፁን ማሰማት የሚገባው ሲሆን መስጂድ እና መድረሳወን ከምንጊዜውም በበለጠ ነቅቶ በመጠበቅ የእምነት ነፃነቱን ማስከበር ይኖርበታል።

መንግስት እና ይህ ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታችሁ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የአዲስ አበባ መጅሊስ ያረቀቀው ህገ መጅሊስ የሙስሊሙን ማህበረሰብ አንድነት የሚበትን፣ በሙስሊሙ መሀከል ሁከትና ብጥብጥ የሚያስነሳ፣ መስጂድና መድረሳዎች የሁከት ማእከል እንዲሆኑ የሚያደርግ እና የዜጎችን የእምነት ነፃነት የሚከለክል በመሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በማን አለብኝነት ወሀቢዝምን በግድ ለማጥመቅ የተዘጋጀውን የአዲስ አበባ መጅሊስ ገደብ ይበጅለት ዘንድ አጥብቀን እንጠይቃለን
Abiy Ahmed Ali
Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር
Ethiopian Federal Police
Addis Ababa Police
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር
የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

20/04/2026

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን😭
የመስጂዳችን መስራችና ኢማማችን የነበሩት ታላቁ ሸኽ ሙሀመድ ሸሪፍ ወደ አኼራ ሄደዋል😭 አላህ ይዘንላቸው🤲🤲🤲
ቀብር ዙሁር ላይ ቱሉዲምቱ መቃብር

አቃቂ ቃሊቲ የሚገኘው የሲኤምሲ ቅርንጫፍ መድረሳ ታሸገ••••••••••••••••••••••••••••••በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቶታል አካባቢ የሚገኘው ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኘው የሲኤምሲ...
27/03/2026

አቃቂ ቃሊቲ የሚገኘው የሲኤምሲ ቅርንጫፍ መድረሳ ታሸገ
••••••••••••••••••••••••••••••
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቶታል አካባቢ የሚገኘው ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኘው የሲኤምሲ አዳሪ የቁርአን ሂፍዝ ማእከል በዛሬው እለት ከቀኑ 8 ሰአት ላይ ታሽጓል። የቁርአን ሂፍዝ ተማሪዎች ለኢድ በዓል እረፍት ቤተሰብ ለመጠየቅ በሄዱበት በዚህ ሰአት መድረሳው መታሸጉ የመስጂዱ ኮሚቴ መድረሳውን ለመዝጋት አጋጣሚዎችን አድብቶ ሲጠብቅ እንደነበረ ያረጋግጣል። መድረሳው ከተመሰረተ ብዙ አመታት ቢሆንም ወሀቢያ መራሹ መጅሊስ የሾማቸው የመስጂድ ኮሚቴዎች መድረሳው በወሀቢዝም እምነት ካልተጠመቀ መዘጋት አለበት ብሎ በመወሰኑ መድረሳውን በዛሬው እለት አሽገውታል።

ይህ ድርጊት ፍፁም ህገወጥ ከመሆኑ ባሻገር ዜጎች ህገ መንግስቱ ያጎናፀፋቸውን የእምነት ነፃነት የሚፃረር ተግባር በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ፍትህ እንዲያረጋግጡ እንጠይቃለን።

መረጃውን ሼር በማድረግ መድረሳውን ከመዘጋት እናድነው!

ለመላው ጀመዓ በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌙✨መልካም ዒድ! 🕌 🦋عيدكم مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمالكل عام وأن...
19/03/2026

ለመላው ጀመዓ በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
🌙✨መልካም ዒድ! 🕌

🦋عيدكم مبارك
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
كل عام وأنتم بخير🦋

“‘በኒ አደም’ ማለት አደም ብቻ ማለት ነውን ?”🟢 ቁርኣን:- ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር መሆኑን ነው የሚያስተምረው ‼️    አንዳንዶች “ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ይላሉ። ግን ቁ...
26/02/2026

“‘በኒ አደም’ ማለት አደም ብቻ ማለት ነውን ?”

🟢 ቁርኣን:- ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር መሆኑን ነው የሚያስተምረው ‼️

አንዳንዶች “ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ይላሉ። ግን ቁርኣን ግልፅ ቃል አለው፦
📖 «وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ» (ኢስራእ 17:70)
“እኛም የአደምን ልጆች ክብር ሰጠናቸው…”
እዚህ ላይ አላህ “አደምን” አላለም፤ “በኒ አደም” አለ — ይህ ሁሉንም የሰው ዘር ልጆችን ነው የሚያካትተው።

ሙእሚን ብቻ አይደለም፤ ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር ነው።

አደምን ብቻ ቢሆን ኖሮ እንደ «يَا آدَمُ» (2:35) በስሙ ብቻ ይጠራ ነበር።
📖 «يَا نُوحُ» (11:46)
📖 «يَا مُوسَى» (20:11)
📖 «يَا إِبْرَاهِيمُ» (37:104)
እነዚህ አንድ ነቢይን ብቻ ገላጭ ሲሆኑ፤
“بني آدم”ግን የሰው ልጆችን ሁሉን ይገልፃል።

🟢 የመላእክቶቹ ጉዳይም ይህንን ያጠናክራል
📖 (በቀራ 2:30)
መላእክት “ብክለት የሚያስፋፋ ሰው ትፈጥራለህ?” ሲሉ
አላህም እንዲህ አለ፦
«إِنِّي أَعْلَمُ مَا لَا تَعْلَمُونَ»
“እኔ እናንተ የማታውቁትን አውቃለሁ”
ማለትም፦
– ከዚህ ዘር ነቢያት ይመጣሉ
– ሷሊሃን ባሮች ይመጣሉ
– አላህን በነፃ ምርጫ የሚያመልኩ ፍጥረታት ይኖራሉ
ከዚያ በኋላ አደምን ስሞችን አስተማረው (2:31)
መላእክትም ሱጁድ አደረጉ (2:34) — ይህ የሰው የተለየ ክብር ነው።

🟢 እንግዲህ ልዩነት የት ነው?
📖 (ሁጁራት 49:13)
«إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ»
ሰዎች በመሰረታዊ ሰውነት ክቡር ናቸው፤
ግን በተቅዋ ደረጃ ይለያያሉ።
✔ ፍጥረታዊ ክብር → ለሁሉም ሰው
✔ የደረጃ ልዩነት → በእምነትና በተቅዋ
🔎 መደረሻ
“ሰው በሰውነቱ ብቻ ክብር የለውም” ማለት
«وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ» ከሚለው ግልፅ አያ ጋር አይጣጣምም።

ሰው በመፈጠሩ ክቡር ነው፤
በተቅዋ ክብሩ ይጨምራል፤
በክፉ ስራ ደረጃው ይወርዳል —
ግን መሰረታዊ የሰዉነት ክብሩ አይሰረዝም።

#ቁርኣን #በኒአደም #እስልምና

ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋርقال عبد الله بن عباس رضي الله عنهما:"كان رسولُ اللهِ ﷺ أجودَ الناس، وكان أجودَ ما يكونُ في رمضان حين يلقا...
22/02/2026

ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋር
قال عبد الله بن عباس رضي الله عنهما:
"كان رسولُ اللهِ ﷺ أجودَ الناس، وكان أجودَ ما يكونُ في رمضان حين يلقاه جبريل، وكان جبريل يلقاه في كل ليلة من رمضان فيدارسه القرآن، فلرسول الله ﷺ حين يلقاه جبريل أجودُ بالخير من الريح المرسلة."
— رواه محمد بن إسماعيل البخاري
ومسلم بن الحجاج“

የአላህ መልእክተኛﷺ ከሰዎች ሁሉ በጎ እጅግ ለጋስ ነበሩ። በተለይም በረመዳን ወር፣ ከጂብሪል ጋር ሲገናኙ ከሁሉ ይበልጥ ለጋስ ይሆኑ ነበር። ጅብሪልም በረመዳን ሁሉ ሌሊት ይመጣቸው ነበር እና ቁርአንን አብረው ይመላልሱ (ይደጋገሙ) ነበር። እንግዲህ መልእክተኛው ﷺ ጅብሪልን በሚገናኙበት ጊዜ ከተላከ ነፋስ ይልቅ በበጎ እጅግ ይለግሱ ነበር።”
…......….......…....…...….............
በየአመቱ ረመዳን ወር መምጣቱን በማስመልከት" ረመዳንን ከሚስኪኖች ጋር " በሚል መፈክር የሚዘጋጀው ለሚስኪኖች የአስቤዛ እና የፆም ማፍጠሪያ የማጋራት መርሀ ግብር ተከናወነ።

የእደላ መርሀ ግብሩ በአል ዒምራን የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም እና በአል ዒምራን መስጂድ ወጣት ጀመዓ አማካኝነት የተከናወነ ሲሆን።

በእደላው በአካቢቢው የሚገኙ200 ቤተሰቦችን ማዳረስ ተችሏል ።

መሰል መርሀ ግብሮች የእለታዊ ፍጆታን ለቤተሰቦቹ ከማቅረብ በተጨማሪ የማህበረሰብን እርስ በርስ መደጋገፍ እና መተሳሰብ የሚያጠናክር ተግባር ነው

በመሆኑም ይህ የዘንድሮ ዓመት የሁለተኛ እደላ እንደመሆኑ ቀጣይ መርሀ ግብሮች ላይ ሁሉም ማህበረሰብ ይሳተፍ ዘንድ ጥሪ ለማቅረብ እንወዳለን።
አል-ዒምራን Cmc የቁርአን እና ኢስላማዊ ትምሕርት ተቋም

Address

Saris, Bhere Tsige
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኸውፉሏህ መስጂድ ወጣት ማህበር-Khewfullah Mosque youth Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share