25/07/2026
ሐምሌ 18፣ 2018 ዓ.ም | አርባምንጭ
ቀን 3 - የመጨረሻው ቀን | ለአሰራር ስርዓት ለውጥ እንቅስቃሴ እና ፖሊሲ ሙግት (Advocacy & Policy Engagement) ላይ የተሰጠ ስልጠና እና የስትራቴጂ ዝግጅት ‼️
በሕብረት አሊያንስ (Hibret Alliance) የተዘጋጀው ለሶስት ቀናት "በአሰራር ስርዓት ለውጥ እንቅስቃሴ እና ፖሊሲ ሙግት" ላይ ያተኮረው ስልጠና እና የስራ ስትራቴጂ ዝግጅት፣ በስልጠናው የተገኙ እውቀቶችን ወደ ተግባራዊ የእንቅስቃሴ ስትራቴጂዎች እና የድርጊት መርሃ-ግብሮች በመቀየር ላይ ትኩረት በማድረግ በታላቅ ስኬት ተጠናቋል።
የመጨረሻው ቀን ስልጠና የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ያካተተ ነበር፡-
🔹 የኢትዮጵያ የፖሊሲ ሙግት/የተሳታፊነት ምህዳር
🔹 የእንቅስቃሴ/የሙግት ስትራቴጂዎች – የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሙግት እና ፖሊሲ ሂደቶች ላይ እንዴት በብቃት መሳተፍ እንደሚችሉ መመርመር
🔹 ጥረት/ጥቅምን ማስተባበር (Coalition Building) – ለአሰራር ስርዓት ለውጥ የጋራ ትብብርን እና የተቀናጀ እንቅስቃሴን ማጠናከር
🔹 የእንቅስቃሴ ስትራቴጂ ዝግጅት – ውጤታማ የእንቅስቃሴ ስትራቴጂዎችን ማዘጋጀት ያለውን አስፈላጊነት እና የዝግጅት ሂደቱን መረዳት
🔹 ሁኔታዎችን መተንተን (Situational Analysis) – ከእንቅስቃሴው ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን ሁኔታዎች፣ መልካም አጋጣሚዎች እና ባለድርሻ አካላትን መገምገም
የቀኑ ዋና ትኩረት ለአሰራር ስርዓት ለውጥ የሚሆን የክልላዊ እንቅስቃሴ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ-ግብር ማዘጋጀት ላይ የተደረገው የቡድን ስራ እና የሃሳብ ማቅረቢያ (presentation) ነበር። ሶስት ቡድኖች በስልጠናው ያገኙትን እውቀት፣ ክህሎት እና ተግባራዊ ግንዛቤ በማንፀባረቅ የየራሳቸውን ክልላዊ የእንቅስቃሴ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ-ግብር በብቃት አዘጋጅተው አቅርበዋል።
ይህ የሶስት ቀን ስልጠና ለትምህርት፣ ልምድ ለመለዋወጥ፣ ለትብብር እንዲሁም የተሳታፊዎችን አቅም በማጎልበት ለጋራ እና ዘላቂ የአሰራር ስርዓት ለውጥ በሙግት እና ፖሊሲ ሂደቶች ላይ በብቃት እንዲሳተፉ የሚያስችል ትልቅ መድረክ ሆኖ አልፏል።
ይህን ጠቃሚ ተግባር እውን እንዲሆን የገንዘብ ድጋፍ እና እገዛ ያደረገውን ካሪታስ ኦስትሪያን (Caritas Austria) ከልብ እናመሰግናለን። በተጨማሪም ይህን ስልጠና ላዘጋጀው እና ላመቻቸው ሕብረት አሊያንስ (Hibret Alliance)፣ እንዲሁም ስልጠናውን በጥሩ ሙያዊ ብቃት፣ አያያዝ እና ተግባራዊ እውቀት ላቀረቡት ከሴንተር ኦፍ ኤክሰለንስ ኢንተርናሽናል ኮንሰልት (Center of Excellence International Consult) ለመጡት አማካሪ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
----------------------------------
25th July 2026 | Arbaminch
Day 3 – Final Day | Training and Strategy Development on Advocacy & Policy Engagement for Systems Change
The third and final day of the three-day Training and Strategy Development on Advocacy & Policy Engagement for Systems Change, organized by the Hibret Alliance, was successfully completed with a strong focus on translating learning into practical advocacy strategies and action plans.
The final day covered key areas including:
🔹 Ethiopia's Policy Engagement Landscape
🔹 Advocacy Strategies – exploring how Civil Society Organizations (CSOs) can effectively engage in advocacy and policy processes
🔹 Coalition Building – strengthening collaboration and collective action for systems change
🔹 Advocacy Strategy Development – understanding the importance and process of developing effective advocacy strategies
🔹 Situational Analysis – assessing the context, challenges, opportunities, and stakeholders relevant to advocacy efforts
A key highlight of the day was the group work and presentation on Developing a Regional Advocacy Strategy and Action Plan for Systems Change. Three groups successfully developed and presented their respective Regional Advocacy Strategies and Action Plans, demonstrating the knowledge, skills, and practical insights gained throughout the training.
The three-day training provided a valuable platform for learning, experience sharing, collaboration, and strengthening the capacity of participants to engage effectively in advocacy and policy processes for collective and sustainable systems change.
We sincerely thank Caritas Austria for its generous funding and support, which made this important initiative possible. Our appreciation also goes to the Hibret Alliance for organizing and facilitating this valuable training, and to the consultant from Center of Excellence International Consult for delivering the training with excellent expertise, facilitation, and practical insights.
Caritas Österreich