Renewal Church - የተሐድሶ ቤተክርስቲያን

Renewal Church - የተሐድሶ ቤተክርስቲያን የተሐድሶ ቤተክርስቲያን 🅡🅔🅝🅔🅦🅐🅛 🅒🅗🅤🅡🅒🅗
The Renewal Church is a fellowship of believers with a vision to see the Gospel Renewed Church of Jesus Christ in Ethiopia

23/08/2026


#እሁድ ...

ነገ_የጌታና_የወንድሞች_ህብረት_ቀን_ነዉ
22/08/2026

ነገ_የጌታና_የወንድሞች_ህብረት_ቀን_ነዉ

20/08/2026


የፕሮግራም ቀናቶች #እሁድ ከማለዳው 4:00-6...

 ?📖  :1-9በህይወታችን  የህይወት ሽግግር ሁሌ ይኖረናል ከልጅነት ወደ ወጣትነት ከጎልማሳነት ወደ ሽምግልና,ከላጤነት ወደ ማግባት ወደ መዉለድ  በጣም በብዙ ነገሮች ዉስጥ እናልፋለን ከስራ...
18/08/2026

?
📖
:1-9
በህይወታችን የህይወት ሽግግር ሁሌ ይኖረናል ከልጅነት ወደ ወጣትነት ከጎልማሳነት ወደ ሽምግልና,ከላጤነት ወደ ማግባት ወደ መዉለድ በጣም በብዙ ነገሮች ዉስጥ እናልፋለን ከስራ ማጣት ወደ ስራ ማግኘት እሄ ሁሉ የሚያቆምበት ጊዜም ደግሞ አለ።ኢኮኖሚዉ ይለዋወጣል ጊዜዉ በፈጠነ መልኩ ቅርፁን ይቀይራል
ብዙ Transition አሉ በጊዜዉ እርግጠኛ መሆን አንችልም
ዉስጥ የማይለዋወጠዉን የእግዚአብሔር እዉነት መያዝ አለብን። ይዘን መዝለቅ ያለብን የማይለወጠዉን እግዚአብሔርን ነዉ
እንደ እኛ የህይወት transition ጊዜ ላይ የነበረ ሰዉ አለ #ኢያሱ
#ለክርስቲያን ስኬት ምንድነዉ? መለኪያዉስ ምንድነዉ? ከኢያሱ ምን እንማራለን
ስኬት ላይ እንዳለን መለኪያዉ ዉጪ መዉጣት ነዉ?ገንዘብ መያዝ ነዉ? ብዙ ልጆች መዉለድ ነዉ?
👉የስኬት መለኪያዉ:- የሚያናዉጥ ነገር እየተፈጠረ ከባድ ነገሮች እንኳን እየሆነ በዉስጣችን ዉስጥ ባለዉ ሰላም,በዉስጣችን ባለዉ እረፍት ነዉ ልንለካዉ የምንችለዉ። 👉ስኬት ማለት የሚያናዉጥ ነገር እያለ አለመናወጥ የሚረብሽ ነገር እናለ አለመረበሽ እሱ የስኬት መለኪያ ነዉ።ሰላም በሌለበት ዉስጥ እኔ ሰላም ነኝ ወይ? እሄን ጥያቄ መጠየቅ አለብን
ስኬታችን ከሰላማችን ጋር ስኬታችን ከደስታችን ጋር የተያያዘ ነዉ።ብዙ ገንዘብ ያላቸዉ ሰላምም ደስታም የላቸዉም የማያሳርፍ ነገር ዉስጣቸዉ ዉስጥ አለ።
👉በክርስቶስ ዉስጥ በመሆን ነዉ ስኬታችንን የምናረጋግጠዉ
ያላረፉ ሰዎች አያሳርፉም ደስታችን ምን ላይ የተንጠለጠለ ነዉ? እረፍታችንስ? ,"በጌታ ደግሞ ደስ ይበላችሁ"
እጅ በብዙ ያየ ሰዉ ነዉ እስራኤልን ከግብፅ ከማዉጣት ጀምሮ ያደረገዉን እያየ ያደገ የእግዚአብሔርን ተአምራት እያየም የመጣ ነዉ በዛዉ ልክ ደግሞ የሕዝብን አመፅም ያየ ሰዉ ነዉ።ኢያሱ የነበረበት ጊዜ የሽግግር ጊዜ ላይ የነበረ ሰዉ ነበር። የሽግግሩ ግዜ ለኢያሱ አስደንጋጭ እንደነበረ ማስረጃዉ በርታ ፅና አይዞህን አትፍራ አትደንግጥ እያለ እግዚአብሔር ያበረታታዋል።
ጨረሰ?
ኢያሱ 1:5 በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ሆንሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፥ አልተውህም።
(1)
ከሙሴ ጋር እግዚአብሔር ነበር በሚገርም ሁኔታ ግን በሙሴ የተኛን ባህር ነበር የተከፈለዉ በኢያሱ ግን ባለፈ ክብር ነበር እግዚአብሔር የተገለጠዉ ኢያሱ ግን እግዚአብሔር አብሮት ከመሆኑ የተነሳ እየወረደ ያለ ዉሃን ነዉ ያስቆመዉ እሄ የሚያሳየዉ የእግዚአብሔርን አብሮነት መኖሩ ማሳያ ነበር የማይሆን ነገር ሆነ።
የእግዚአብሔር አብሮነት ልዮነት ይፈጥራል መንፈስ ቅዱስን በህይወታችን በማሳዘን ግን በዉስጣችን ፀጥ እንዲል ማድረግ የለብንም።
ሃይላችን እንደ እድሜያችን ነዉ ወይ?ለምንድነዉ የምንፈራዉ የምንረበሸዉ
#የእግዚአብሔር አብሮነት በሁለት ይገለጣል (1 )በሃይል ይገለጣል (2) በታምራት ይገለጣል።በእነዚህ ነገሮች አብሮነቱን ያሳየናል
👉የመንፈስ ቅዱስ ፍሬስ በህይወታችን ይገለጣል ዙርያችን ያሉት ሰዎች የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን በእኛ ዉስጥ ያያሉ ወይንስ የሰዎችን ሰላም እናፈርሳለን ሰዎች እንደሚረበሹ እንረበሻለን? የቱ ጋር ነዉ ያለነዉ? በጌታ ቤት እረጅም ጊዜ ኖረናል ግን የምንለይበት ነገር የለንም።ስለዚህ ልዮነት መኖር አለበት እግዚአብሔር በሃይልም በታምራትም ይሰራል
(2)የእግዚአብሔር ቃል አብሬክ እንድወጣ እድገባ ሙሴ የነገረህን የዚህን ፃፈዉ ከእሱ ወደ ግራም ወደቀኝም አትበል ስኬትህ ያለዉ እዚህ ላይ ነዉ ያኔ ይሳካልሃል ይከናወንልሃልም አለዉ።
ነዉ ለኢያሱ እግዚአብሔር የሰጠዉ አንተ ቃሉን ያዝ እኔ ዉጤት እሰጥሃለሁ አለ እግዚአብሔር ።እኛም እያንዳንዱን ነገር በእግዚአብሔር ቃል መመርመር አለብን ዉጤታችን ስኬታችን እሱ ላይ ነዉ።አረማመዳችን ጉዋደኞቻችንን መምረጥ ከቃሉ አንፃር መሆን አለበት።ዉጤታማነታችን በቃሉ ስለሆነ እያንዳንዱን ነገር በእግዚአብሔር ቃል ካደረግነዉ ይሳካልናል።
የምንሰማዉን ሁሉ እንዳንቀበል ማጥለያ የእግዚአብሔር ቃል አለን።
ኢያሱ ምዕራፍ 24 ላይ እግዚአብሔር እንደተናገረ ኢያሱን የዉጤት ሰዉ አደረገዉ ኢያሱም በእግዚአብሔር ያለዉ መተማን ከሁል ጊዜዉ በላይ የበለጠ ሆኖ የምታመልኩትን ምረጡ እኔ እና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን ብሎ በእግዚአብሔር ያለዉን መተማን አሳየ
እንደቃሉ ከሆንን እንደቃሉ እየኖርን ከሆነ ይሳካልናል እንደ እድሜያችን ልክ ዉጤታማ እንሆናልን። #አሜን

16/08/2026


የፕሮግራም ቀናቶች #እሁድ ከማለዳው 4:00-6...

15/08/2026

14/08/2026


#እሁድ ...

 📖   :14_20 #አጋር ዙርያዋ ያለዉን ሁኔታ እንጂ እግዚአብሔር ያየዉን አይደለም ያየችዉ ሁኔታዋ የሚያወራትን ነዉ ያየች በብዙ ተስፋ መቁረጥ ዉስጥ በነበረችበት ዉስጥ እግዚአብሔር የሕፃኑ...
10/08/2026


📖
:14_20
#አጋር ዙርያዋ ያለዉን ሁኔታ እንጂ እግዚአብሔር ያየዉን አይደለም ያየችዉ ሁኔታዋ የሚያወራትን ነዉ ያየች በብዙ ተስፋ መቁረጥ ዉስጥ በነበረችበት ዉስጥ እግዚአብሔር የሕፃኑን የጩኸት ድምፅ ሰማ እግዚአብሔር ትልቅ ሕዝብ አደርገዋለሁ ብሎ ቃል ገባላት።አድጎም ቀስተኛ ሆነ በምድረበዳ ሳሉ ግን እንደዚህ ይሆናል ተብሎም አልታሰበም።
#አምስቱ የስሜት ሕዋሳት የእግዚአብሔርን ነገር ሊነግሩን አይችሉም አጋር በነዚህ ሁኔታዎች ማወቅ አልቻለችም ነገሮች ሁኔታዎች የሚያወሯት እና እግዚአብሔር ያየዉ የተለያየ ነበር
:1_18 ዛቻ ፈርቶ የኤልዛቤልን ፉከራ ሰምቶ. ኤልሳም የተፈጠረዉ ነገር ሞትን እንዲመኝ አስመኘዉ ሁኔታዉ እሄ ነበር።በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ያልተነካ ብዙ ስራ እንዳለ አያዉቅም ነበር ነገር ግን ለብዙዎች መነሳት የመቀባት አጀንዳ ግን ነበር ሁኔታዉ ግን እሄን አያወራም።
#እኛም ጋር አሁን ዙርያችን ያለዉን ነገር የምናይ ከሆነ እግዚአብሔር ያየዉን እንድናይ ላያደርገን ይችላል እግዚአብሔር ያየዉን ማየት ነዉ የሚጠበቅብን።ስሜታችንን አይደለም ማዳመጥ ያለብን እግዚአብሔርን ነዉ ማዳመጥ ያለብን
#የሰራፕታዋ ባልቴት ሴት 1ነገ 17 ኤልያስ እንጀራ በጠየቃት ጊዜ ሁኔታዋ የሚያወራዉን ነገር ለኤልያስ ነገረችዉ።ዛሬ በልተነዉ የምንሞት ነን ብላ የሁኔታዋን ነገር ነዉ ያሳወቅችዉ. ያለችበት ሁኔታ ግን የሚለወጥ አይመስልም, ኤልያስ ግን እሄ አይሆንም አላት።የእራቡ ዘመን እስኪያልቅ ድረስ በቤቷ ጥጋብ ገባ የእግዚአብሔር ዓላማ ለካስ በሕይወት እሷን ማኖር ነዉ።
ዮሐ 11 ማርያም እና ማርታ ወንድማቸዉ አላዛር ሞተ ሁኔታዉ ሃዘን ዉስጥ አስገብቷቸዋል ለኢየሱስም አንተ እኮ እዚህ ሆነህ ቢሆን ኖሮ ወንድማችን ባልሞተ እያሉ ቁጭት ዉስጥ ገብተዉ ነበር።ለካስ ሌላ ታምር ሊሆን መንፈሳዊ ማንነታቸዉን ከፍ ሊያደርግላቸዉቸዉ ነዉ።ለካስ ብዙዎች በኢየሱስ እንዲያምኑ ነበር ሁኔታዉ ግን እሄን ይፈጥራል ብሎ ያሰበ የለም። የኢየሱስ ቃል አላዛርን ከሞተበት አስነሳዉ ብዙዎችም በኢየሱስ አመኑ።
ሉቃ 24 ታላቁ ነብይ ሞቶባቸዉ ወደ ሃገራቸዉ ዝለዉ ደክመዉ እየተመለሱ ነበር።የመጡበት መንገዱ ሁኔታዉ ወሬዉ እሄን አይገልፅም ነበር።በመንገድ መሃል ኢየሱስ አግኝቷቸዉ እቤት እስኪገቡ አብሮዋቸዉ የሚሄደዉን አያዉቁትም ነበር ከሚነገራቸዉ ቃል የተነሳ ግን ልባቸዉ ይነድ ነበር እራት ላይ ግን አይናቸዉ ተከፈተ አይናቸዉ ሲከፈት ግን ድካማቸዉን ዝለታቸዉን እረስተዉ ቀኑን ሙሉ ሲጓዙ የነበረበት መንገድ ኢየሱስን አገኘነዉ ለማለት በዛዉ ምሽት ወጡ።እያለፉበት የነበረበት ህይወት ቀጥሎ እንደሚጓዙ አያሳይም ነበር።ኢየሱስን ከበፉቱ በላይ ገባቸዉ ነብይ ብቻ እንዳልሆነ ገባቸዉ።የነበሩበት ሁኔታ ግን እሄን የሚፈጥር አይመስልም ነበር
3 -26
ብሎ የእግዚአብሔርን ማዳን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው።
እግዚአብሔር ዝም ብሏል ማለት ተኝቷል አያይም ማለት አይደለም። አሁን ያለንበት ሁኔታዎች አሁን ያለዉን እንጂ እግዚአብሔር ለእኛ ያለዉን ወይም ያየዉን አይነግሩንም።
እግዚአብሔር ያለዉን መስማት ይሁንልን።

ድንቅ አምልኮ
09/08/2026

ድንቅ አምልኮ

የፕሮግራም ቀናቶች #እሁድ ከማለዳው 4:00-6...

Address

CMC Road, Shalom Building Ground Floor
Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Renewal Church - የተሐድሶ ቤተክርስቲያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category