Waldaa Ortodoksi Tewahido Giddu Gala Biyyatti

Waldaa Ortodoksi Tewahido Giddu Gala Biyyatti No bussiness

02/02/2026
በሀገረ ጀርመን የሚገኙ ካቶሊካውያን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ስጦታ አበረከቱ !የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በኢትዮጵያ ኦ...
09/02/2025

በሀገረ ጀርመን የሚገኙ ካቶሊካውያን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ስጦታ አበረከቱ !

የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተከርስቲያን የጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት የዱስልዶርፍ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ፤ ከካቶሊካውያን የሕንጻ ቤተክርስቲያን ስጦታ ተበርክቶለታል።

ላለፉት 10 ዓመታት የደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ሲገለገሉበት የቆዩት እና የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ንብረት የነበረው የሴንት ኖርበርት ቤተ ክርስቲያን በጋራትህ ከተማ ከሚገኙ የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዱ ሲሆን ባሳለፍነው ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም (Jan 26, 2025) ሙሉ በሙሉ ለደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በስጦታ ተሰጥቷል።

ከ 60 ዓመታት በፊት በተሠራው በዚህ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን የስጦታ መርሐ ግብር ላይ የሁለቱም የሃይማኖት ተከታዮች ካህናት እና ምእመናን በተገኙበት የጋራ ጸሎት ተደርጓል እንዲሁም መዝሙሮች እና የተለያዩ መርሐ ግብሮች ቀርበዋል። የሁለቱ አብያተክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ቤዛ መንግሥቱ እና ቄስ ማርቲን ሩስተር በዝግጅቱ ለታደሙ ምእመናን ስለሁለቱም ሃይማኖቶች ገለጻ አድርገዋል።

በአካባቢው የሚነበበው ራይኒሸፖስት የተባለ ጋዜጣ እንደዘገበው ቄስ ማርቲን ሩስተር የስጦታውን ምክንያት ሲያስረዱ “በአካባቢው ያሉ ምእመናን ቁጥር እየቀነሰ በመምጣቱ እኛ ለረጅም ግዜ ልንሰጠው የማንችለውን ሃይማኖታዊ አገልግሎት መስጠት ይችላሉ እና ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ለመስጠት ወስነናል” ብለዋል።

ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ቤዛ መንግሥቱ በበኩላቸው በውጭ ሀገር የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በውጭ ሀገር ለሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች የእምነት ቦታ ከመሆንም ውጭ ትንሿ ኢትዮጵያ እንደሆነች ገልጸዋል። አክለውም ስለተደረገው ስጦታ ለአስተዳዳሪው ካህንና ለካቶሊክ እምነት ተከታዮች በራሳቸውና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ስም ከታላቅ አክብሮት ጋር ምሰጋናን አቅርበዋል።

በመርሐ ግብሩም የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ስጦታ የሚያረጋግጥ የስጦታ ውል ቄስ ማርቲን ሩስተር ለሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ቤዛ መንግሥቱ በአክብሮት አስረክበዋል። በቦታው ታድመው የነበሩ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን እና ምእመናት በእንባ የታጀበ ደስታቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ቄስ ማርቲን ሩስተርን ጨምሮ በቤተክርስቲያኑ የስጦታ ሂደት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለካቶሊክ እምነት ተከታዮች ከኢትዮጵያ ተዘጋጅተው የመጡ የመስቀል ቅርጽ ምስል ፣ የአንገት ልብስ አንዲሁም የአበባ እቅፍ ከታላቅ አክብሮትና ምስጋና ጋር በሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ቤዛ መንግሥቱ አማካይነት ተበርክቶላቸዋል።

ዘገባው የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚድያ ነው

በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል !!በ3ቱ በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተሰጠ ፍርድ በቅርቡ በቅዱስ ሚካኤል ታቦት እያሾፉ እና እይቀለዱ በቲክ ቶክ ቪዲዮ ለቀው የነበሩት ተማሪ ገመቹ ምትኩ...
03/02/2025

በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል !!

በ3ቱ በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተሰጠ ፍርድ በቅርቡ በቅዱስ ሚካኤል ታቦት እያሾፉ እና እይቀለዱ በቲክ ቶክ ቪዲዮ ለቀው የነበሩት ተማሪ ገመቹ ምትኩ፣ ተማሪ ካሳን አድቬንቸር፣ ተማሪ ጋዲሳ ኢቲና ዛሬ በአምቦ ዳዳቻ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል::

ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጡ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎ...
30/01/2025

ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጡ

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን

28/01/2025
🙏🙏🙏💒 አስተሪዮ ማርያም 💒 #እጅግ አብዝቶ የሚገርመው ሞትለአዳም የተነገረው ቃል የማይፈጸምበት ሰብአዊ ፍጡር የለም፡፡ መሬትነትና ወደ መሬት መመለስ ኃያላን በጉልበታቸው፣ ነገስታት በሰራዊታ...
28/01/2025

🙏🙏🙏

💒 አስተሪዮ ማርያም 💒

#እጅግ አብዝቶ የሚገርመው ሞት

ለአዳም የተነገረው ቃል የማይፈጸምበት
ሰብአዊ ፍጡር የለም፡፡

መሬትነትና ወደ መሬት መመለስ ኃያላን በጉልበታቸው፣ ነገስታት በሰራዊታቸው፣ ሌላው ቀርቶ አማላካችን እግዚአብሔር በቅድስናቸው ከፍ ያደረጋቸው ቅዱሳን ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃንና ሰማዕታት ሁሉ ስጋዊ ሞትን ቀምሰዋል፡፡ እነርሱ ግን በስጋዊ ሞታቸው ወደ ዘለዓለማዊ የክብር እረፍታቸው ነው የሔዱት፡፡ የሕይወትና የሞት ባለቤት እርሱን ወለደችው የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት ግን ከሁሉ ይገርማል፡፡ የአምላክ እናቱ ስትሆን ሞትን ግን ቀምሳለች፡፡ ሞትስ ለሟች ይገባዋል የእመቤታችን የቅድስት ማርያም ሞት ግን አስደናቂ ነው፡፡

በምድር ላይ 64 ዓመት የኖረችው ቅድስት ድንግል ማርያም በአባት በእናቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ ዐሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወራት፤ ከጌታ ስቅለት በኋላ በመስቀል ላይ ሳለ አደራ በሰጠው፣ ጌታ በሚወደው ሐዋርያ፣ በወንጌላዊው በቅዱስ ዮሐንስ ዐሥራ አምስት ዓመታት ኖራለች፡፡ ጌታን የፀነሰችበትን ወራት ስንጨምር እመቤታችን በዚህ ዓለም በሥጋ የቆየችበት ጊዜ ስድሳ አራት ዓመት ይሆናል፡፡

ልጇ ወዳጇ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምታርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ሲነግራት ሞትን መቅመስ እንደማትፈልግ ነገረችው፡፡ እርሱም ስጋን የለበሰ የአዳም ዘር ሁሉ ሞትን እንደሚያይ ነገራት፤ በመላእክት ምስጋና፣ በዳዊት ዝማሬ ቅድስት ነፍሷ ከቅድስት ስጋዋ ተለየች፡፡

የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት በሁለት ምክንያት እንደሆነ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ያስረዳል፡፡ የመጀመሪያው “ዓለሙን ሁሉ ፈጥሮ ለሚገዛው ለመለኮት ማደሪያ ለመሆን የበቃችው ከሰማይ የመጣች ብትሆን ነው እንጂ የሰው ልጅስ አይደለችም፤” በማለት የሚነሱ መናፍቃን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን የሰውን ባሕርይ አለበሰምና ያልተቀበልነው ለዚህ ነው እንዳይሉ ነው፡፡ ሞቷ ግን የሰው ልጅ እጣ ፈንታ የሆነውን ጽዋ እንድትቀበል አድርጓታል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ሲያስረዳ ለዕብራውያን ሰዎች በላከው መልዕክቱ ዕብ 2÷14-15 “የአብርሃምን ዘር ይዟል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም›› አለ፡፡ በዚህም ድንግል ማርያም የአዳም ዘር መሆኗ ታወቀ፡፡

ሁለተኛው ጌታችን በፍርዱ አድልዎ የሌለበት አምላክ መኾኑ ይታወቅ ዘንድ ሥጋ የለበሰ ዅሉ በለበሰው ሥጋ ሞትን ይቀምስ ዘንድ ግድ ነውና ቅድስት ድንግል ማርያም ሞትን ቀመሰች፡፡ ይህን ቅዱስ ያሬድም መስክሯል፡፡ በበዓለ አስተርዕዮ ጥር 21 ቀን ቅድስት ድንግል ማርያም በክብር አርፋለች፡፡

አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት የታየበት፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል።
Waldaa Ortodoksi Tewahido Giddu Gala Biyyatti

Message of His Holiness the Patriarch to all the People of the World.
31/12/2024

Message of His Holiness the Patriarch to all the People of the World.

በኢትዮጵያ ለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ታወጀ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ወረዳ የደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ ሕይወታቸው ላለፉ ዜጎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤ...
26/07/2024

በኢትዮጵያ ለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ታወጀ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ወረዳ የደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ ሕይወታቸው ላለፉ ዜጎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከነገ ጀምሮ ለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን አውጇል።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ።**********************  በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ...
02/08/2023

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ።
**********************

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስትና በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ቁጥር 3 አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ሐምሌ 26ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡

ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን አንድ አድርጋ የሰው ልጆች ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ ተጠምቀው የቤተ ክርስቲያን ልጆች በመሆን ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ስትሆን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤

ምንም እንኳ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደር ጥሰት ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረትና ዐምድ፤ ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረችና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤ ከፍተኛውን ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር በቆመች፣ ከፖለቲካ በጸዳች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊትና ተቋምን የመናድ እንደሁም መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡-

በዚሁ መሠረት፡-

ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ/ም በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም ውስጥ የተፈጸመውን ሕገወጥ የሆነ አስነዋሪ፤ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐምሌ 26ቀን 2015 ዓ/ም አስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡ ይህንኑ በመረዳትም ቅዱስ ሲኖዶስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንት ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያና የህግ ባለሙያዎች አቢይ ኮሚቴ፤ የውጪ ግንኙነት መምሪያ፣ ካቀረቡት ዶግማዊ፣ቀኖናዊ፣ታሪካዊና ትውፊታዊ ሰነዶች በመነሣት የቤተ ክርስቲያንን ልዕልና ለማስከበር ያስችል ዘንድ ጥልቅ ውይ

ቅዱስ ሲኖዶስ  አውግዞ ለይቷችዋል***እንግዲህ እግዚአብሔር በውግዘታቸው ክፍለጊዜ የንሰኃ ዕድሜ ይሰጣቸው ዘንድ እመኛለው።ህገወጥነት ወሊሶም ተካሄደ አክሱም ህገወጡነቱን አይለቅም። ለህገወጥነ...
02/08/2023

ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ለይቷችዋል
***

እንግዲህ እግዚአብሔር በውግዘታቸው ክፍለጊዜ የንሰኃ ዕድሜ ይሰጣቸው ዘንድ እመኛለው።

ህገወጥነት ወሊሶም ተካሄደ አክሱም ህገወጡነቱን አይለቅም። ለህገወጥነት ምንም ምክንያት ቢደረደር ወደ ህጋዊነት አያመጣም።

በእረኝነታቸው ላይ የጨበጡትን የፓለቲካ ብትር ጥለው በትረ አሮንን ይጨብጡ ዘንድ እንመኛለን

በግለሰቦች አለመግባባት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ መፍረድ ነውር ነው።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251947426384

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Waldaa Ortodoksi Tewahido Giddu Gala Biyyatti posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share