St. Mary's Condominium youth spiritual Unity

St. Mary's Condominium youth spiritual Unity የተዋህዶ ዕምነት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማገዝ በቦሌ ቡልቡላ ማሪያም ኮንዶሚንየም ወጣቶች የተቋቋመ ማህበር ነው፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በቦሌ ቡልቡላ ማሪያም ኮንዶሚንየም አጥቢያ ባሉ የወጣቶች ስብስብ ተመስርቶ ወጣቶችን ለቤተክርስቲያን ጥቅም በማደራጀት የተዋህዶ ዕምነት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማገዝ የተቋቋመ ማህበር ነው፡፡

በ፪፱፲፯  ዓ.ም  አስበን የተሳካ ሞክረን የተበላሸ  በህይወት ያጣናቸው በግል ያሳካናቸው ስህተት ሆነው የተማርንባቸው ብዙ የህይወት ምስቅልቅሎችን አሳልፈን ለዚች ቀን ያደረሰን ቸሩ መድኃኔዓ...
10/09/2025

በ፪፱፲፯ ዓ.ም አስበን የተሳካ ሞክረን የተበላሸ በህይወት ያጣናቸው በግል ያሳካናቸው ስህተት ሆነው የተማርንባቸው ብዙ የህይወት ምስቅልቅሎችን አሳልፈን ለዚች ቀን ያደረሰን ቸሩ መድኃኔዓለም ይክበር ይመስገን ሁሉን ያደረገ እሱ ነውና።

መጪውን ፪፱፲፰ በኛ ፍላጎት ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃዱ የሰላም የአንድነት በመንፈሳዊ ህይወታችን ምንበረታበት ወደ ንስሃ ምንቀርብበት በቤቱ ምንጸናበት
ለስጋወደሙ እንዲያደርሰን የሱ ፈቃድ ይሁን ።

እንኳን ከዘመነ ዮሀንስ ወደ ዘመነ ማርቆስ አደረሰን ቤተሰቦች።

መልካም በዓል🌻

27/08/2025

የ2018 አመት ምህረት የደመራ በዓላችን ዝግጅት እንደቀጠለ ነው

እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።  † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አ...
15/07/2025

እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🕊 † አቡነ ኪሮስ ጻድቅ † 🕊

† የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል::

አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው [ታላቁ ቴዎዶስዮስ] በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ [ገዳመ አስቄጥስ] መጡ::

እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ ገብረ ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ አቡነ በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል::

ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል::

አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ::

ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ፴ [30] ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር::

ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ፶፯ [57] ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ [ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና] በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ::

ቅዱስ ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም።

እንኳን ለአግአዚተዓለም ቅድስት ሥላሴ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ
14/07/2025

እንኳን ለአግአዚተዓለም ቅድስት ሥላሴ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ

እንኳን ለገናናው መላአክ ቅዱስ ሚካኤል በሰላም አደረሳቹ
19/06/2025

እንኳን ለገናናው መላአክ ቅዱስ ሚካኤል በሰላም አደረሳቹ

ህያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።ሉቃ ፳፬ ÷ ፭እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳቹ
19/04/2025

ህያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
ሉቃ ፳፬ ÷ ፭
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳቹ

19/04/2025

Big shout-out to my newest top fans! Wendmagegn Taye, እኔ የማርያም ልጅ ነኝ

ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስጥር ፲፯ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ምየሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣስዮስ የተባለ ከቀጰዶቅያ ሀገር የሆነ መስፍን ነው፡፡ እናቱም ቴዎብስታ የተባለች ፍልስጥዔማ...
26/01/2025

ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ

ጥር ፲፯ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም

የሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣስዮስ የተባለ ከቀጰዶቅያ ሀገር የሆነ መስፍን ነው፡፡ እናቱም ቴዎብስታ የተባለች ፍልስጥዔማዊ ናት፤ ይህም ቅዱስ በሕፃንነቱ አባቱ ዐረፈ፡፡

ዕድሜውም ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሄደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡ ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ፤ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች ሰጠ፤ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው፡፡

ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ፡፡ ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡ ለመስማት እንኳ የሚያስጨንቅ ሥቃይን አሠቃየው፤ ጌታችን ግን ያጸናዋል፤ ቍስሉንም ያድነዋል፤ ሦስት ጊዜም እንደሚሞት እርሱም እንደሚአስነሣው በዐራተኛውም የምስክርን አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው፡፡ ቃል ኪዳንም ሰጠው፤ ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው፡፡

ንጉሡም ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለመታዘዙና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ፡፡ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ታላቅ ሥራየኛ አመጣ፡፡ እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ መልቶ አስማት ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው፡፡ ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር፡፡ ቅዱሱም ያንን ጽዋ ጠጣው፤ ምንም ጉዳት አልደረሰበትም፡፡

ያ መሠርይም በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ፡፡ ከእርሱም ጋር ሌሎች ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት ሙተው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ፤ ቁጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ ነፍስ ነው፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን አሉት፡፡ በዚያን ጊዜ ጸለየ፤ እንዳሉትም አደረጋቸው፤ ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ቍጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ በጌታችን አመኑ፡፡

ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ አቃጥለው አሳርረውም ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ በተኑት፡፡ ይህም የሆነው ጥር ፲፰ ቀን ነው፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው፡፡ ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ስም ሰበከ፡፡ ቍጥር የሌላቸው አሕዛብ አይተው አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ፡፡

ነገሥታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታሥነሣ አምላክህ ዕውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ በእርሱም እናምናለን አሉት፡፡ ቅዱሱም ጸለየ፤ ከጒድጓድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶችን ጐልማሶችንም አስነሣላቸው፤ እነዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ስም አስተማሩ፤ የገሃነምንም ወሬ ተናገሩ፤ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው ዐረፉ፡፡

ከሀድያን ነገሥታት ግን ሙታንን ያስነሣህ አይደለም፤ የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ፡፡ ከዚያም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሣ ከአንዲት ድኃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት፤ እርሷም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች፤ የእግዚአብሔርም መልአክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ ማዕድን አቀረበለት፡፡ የዚያች መበለትም የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ፡፡

ያቺም መበለት በተመለሰች ጊዜ የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ስለ ማዕዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደ

ረድኤት በረከቱ ይደርብን
12/01/2025

ረድኤት በረከቱ ይደርብን

እንኳን አደረሳችሁ
07/01/2025

እንኳን አደረሳችሁ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when St. Mary's Condominium youth spiritual Unity posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share