Prophet Asrat Abula's Ministry

Prophet Asrat Abula's Ministry Jesus is the way, the truth and the life.

በዐውሎ ነፋስም የተነዱ ደመናዎች ናቸው...........2ኛ ጴጥሮስ 2¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹⁵ ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ፤ የባሶርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከተሉ፤ እርሱ የዓመፃን ደመወዝ ወደ...
15/07/2025

በዐውሎ ነፋስም የተነዱ ደመናዎች ናቸው...........

2ኛ ጴጥሮስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ፤ የባሶርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከተሉ፤ እርሱ የዓመፃን ደመወዝ ወደደ፥
¹⁶ ነገር ግን ስለ መተላለፉ ተዘለፈ፤ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነቢዩን እብድነት አገደ።
¹⁷ ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው እነዚህ ውኃ የሌለባቸው ምንጮች በዐውሎ ነፋስም የተነዱ ደመናዎች ናቸው።
¹⁸ ከንቱና ከመጠን ይልቅ ታላቅ የሆነውን ቃል ይናገራሉና፥ በስሕተትም ከሚኖሩት አሁን የሚያመልጡትን በሥጋ ሴሰኛ ምኞት ያታልላሉ።
¹⁹ ራሳቸው የጥፋት ባሪያዎች ሆነው፦ አርነት ትወጣላችሁ እያሉ ተስፋ ይሰጡአቸዋል፤ ሰው ለተሸነፈበት ለእርሱ ተገዝቶ ባሪያ ነውና።
²⁰ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።
²¹ አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና።
²² ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ፦ የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል።

06/01/2022

*****************
እንኳን የጌታችን የመዳንታችን
የእየሱስ ክርስቶስ
የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
-----------------------------
⁶ ሕፃን ተወልዶልናልና፤ ወንድ ልጅ ተሰጥቶናል፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል። ስሙም፣ ድንቅ መካር፣ ኀያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም ልዑል ይባላል።
⁷ ለመንግሥቱ ስፋት፣ ለሰላሙም ብዛት ፍጻሜ የለውም፤ ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣ መንግሥቱን በፍትሕና በጽድቅ ይመሠርታል፤ ደግፎ በመያዝም ያጸናዋል። በዳዊት ዙፋን ይቀመጣል፤ አገሩንም ሁሉ ይገዛል፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቅናት ይህን ያደርጋል።
ኢሳይያስ 9 (አዲሱ መ.ት)

************************************************ታላቁ የበጉ ሰርግ ጥሪ ደርስዋል እንዘጋጅ ቅዱሳን--------------⁷ የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ፣ የእርሱም ሙሽራ...
31/12/2021

*************************
***********************
ታላቁ የበጉ ሰርግ ጥሪ ደርስዋል
እንዘጋጅ ቅዱሳን--------------

⁷ የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ፣ የእርሱም ሙሽራ ራሷን ስላዘጋጀች፣ ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ ክብርም እንስጠው።
⁸ የሚያንጸባርቅና ንጹሕ፣ ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ እንድትለብስ ተሰጣት።” ከተልባ እግር የተሠራው ቀጭን ልብስ የቅዱሳን የጽድቅ ሥራ ነው።
⁹ መልአኩም፣ “ ‘ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው’ ብለህ ጻፍ” አለኝ፤ ቀጥሎም፣ “እነዚህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃሎች ናቸው” አለኝ።
ራእይ 19 (አዲሱ መ.ት)

13 በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤ 14 በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እን...
26/11/2021

13 በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤ 14 በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል፤ 15 የምንለምነውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ የለመነውንም ነገር እንደ ተቀበልን እናውቃለን።
16 ማንም ሰው ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይጸልይ፤ እግዚአብሔርም ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ላደረጉት ሕይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃም ኀጢአት አለ፤ ስለዚህኛው ግን ይጸልይ አልልም። 17 ዐመፅ ሁሉ ኀጢአት ነው፤ ለሞት የማያበቃም ኀጢአት አለ። 18 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአት እንደማያደርግ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሚጠብቀው፣ ክፉውም እንደማይነካው እናውቃለን። 19 እኛ ከእግዚአብሔር እንደሆንን፣ መላው ዓለምም በክፉው ሥር እንደሆነ እናውቃለን።
20 የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ፣ እውነተኛ የሆነውን እርሱን እንድናውቅ ማስተዋልን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነተኛ በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።
21 ልጆች ሆይ፤ ራሳችሁን ከጣዖቶች ጠብቁ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version (Addisu Medebegna Tirgum)TM Copyright © 2001 by Biblica, Inc. Used by permission. All rights reserved worldwide.
www.Biblica.com
New Amharic Standard Version (Addisu Medebegna Tirgum)TM, Audio Edition Copyright ℗ 2017 by Biblica, Inc. Used by permission of Biblica, Inc. All rights reserved worldwide.

For more than 200 years, Biblica, the International Bible Society, has helped millions of people access and experience God's Word.

26/11/2021

1ኛ) ዮሐንስ 5:1-12
1 ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፤ አባትንም የሚወድ ሁሉ ልጁንም እንደዚሁ ይወዳል። 2 እግዚአብሔርን ስንወድና ትእዛዛቱን ስንፈጽም የእግዚአብሔርን ልጆች እንደ ምንወድ በዚህ እናውቃለን፤
3 እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዛቱን መፈጸም ነውና። ትእዛዛቱም ከባድ አይደሉም፤ 4 ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሸንፈውም እምነታችን ነው። 5 ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው?
6 በውሃና በደም የመጣው ይህ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በውሃና በደም እንጂ በውሃ ብቻ አልመጣም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፤ መንፈስ እውነት ነውና። 7 ስለዚህ ሦስት ምስክሮች አሉት። 8 እነርሱምa መንፈሱ፣ ውሃውና ደሙ ናቸው፤ ሦስቱም ይስማማሉ። 9 የሰውን ምስክርነት ከተቀበልን፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ከዚያም ይልቃል፤ ይህ ስለ ልጁ የሰጠው የእግዚአብሔር ምስክርነት ነውና። 10 በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ሁሉ በልቡ ምስክር አለው፤ ማንም እግዚአብሔርን የማያምን ሁሉ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። 11 ምስክርነቱም ይህ ነው፤ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት ሰጠን፤ ይህም ሕይወት ያለው በልጁ ነው። 12 ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።

02/11/2021

መዝሙር 46 (Psalms)
5፤ እግዚአብሔር በመካከልዋ ነው አትናወጥም፥ እግዚአብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል።
6፤ አሕዛብ ተናወጡ መንግሥታትም ተመለሱ፤ እርሱ ቃሉን ሰጠ፥ ምድርም ተንቀጠቀጠች።
7፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።
8፤ የእግዚአብሔርን ሥራ፥ በምድር ያደረገውንም ተኣምራት እንድታዩ ኑ።
9፤ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ጦርነት ይሽራል። ቀስትን ይሰብራል፥ ጦርንም ይቈርጣል በእሳትም ጋሻን ያቃጥላል።
10፤ ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤ በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።
11፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።

02/11/2021

መዝሙር 91 (Psalms)
1፤ በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል።
2፤ እግዚአብሔርን፡— አንተ መታመኛዬ ነህ፡ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ።
3፤ እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና።
4፤ በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል።
5፤ ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥
6፤ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም።
7፤ በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም።
8፤ በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ።
9፤ አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ።
10፤ ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም።

መዝሙር 119 1 መንገዳቸው ነቀፋ የሌለበት፣በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው።2 ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤3 ዐመፅን አያደርጉም፤ነገር ግን በመን...
20/10/2021

መዝሙር 119

1 መንገዳቸው ነቀፋ የሌለበት፣
በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው።
2 ምስክርነቱን የሚጠብቁ፣
በፍጹምም ልብ የሚሹት የተባረኩ ናቸው፤
3 ዐመፅን አያደርጉም፤
ነገር ግን በመንገዱ ይሄዳሉ።
4 ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ፣
አንተ ሥርዐትን አዘሃል።
5 ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣
ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ!
6 ወደ ትእዛዛትህ ስመለከት፣
በዚያን ጊዜ አላፍርም።
7 የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣
በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ።
8 ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤
ፈጽመህ አትተወኝ።
ቤት
9 ጒልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል?
በቃልህ መሠረት በመኖር ነው።
10 በሙሉ ልቤ ፈለግሁህ፤
ከትእዛዛትህ ፈቀቅ እንዳልል አድርገኝ።
11 አንተን እንዳልበድል፣
ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
12 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ቡሩክ ነህ፤
ሥርዐትህን አስተምረኝ።
13 ከአንደበትህ የሚወጣውን ደንብ ሁሉ፣
በከንፈሬ እናገራለሁ።
14 ሰው በሀብቱ ብዛት ደስ እንደሚለው፣
ምስክርነትህን በመከተል ደስ ይለኛል።
15 ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤
ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ።
16 በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤
ቃልህንም አልዘነጋ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prophet Asrat Abula's Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Prophet Asrat Abula's Ministry:

Share