21/04/2026
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ከ19 ወራት ቡሃላ የመጀመሪያ ንግግራቸውን አድርገዋል። እርሳቸው እንደተናገሩት ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አድርገዋል። የሀሩን ሚዲያ ዘገባ እንደሚያመላክተው ደግሞ ስለጨቋኙ መመሪያ የተናገሩት ነገር የለም።
አሁንም ጥያቄያችን ግልፅ ነው። መጅሊስ ሀላፊነቱን በአግባቡ ይወጣ። የተበደሉ ተማሪዎች አስፈላጊው ካሳ ይሰጣቸው። ጨቋኙ መመሪያ ይሻሻል።
ጥያቄ አለን _ መልስም እንፈልጋለን!!!
AAU - Muslim Students Union