03/01/2026
🎯እምነት ምሰሉአቸው🎯
“የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው
ምሰሉአቸው።” (ዕብ.13፥7)
........✝️የሣራ እምነት✝️.......
“ሣራም ተስፋ የሰጠው የታመነ እንደሆነ ስለ ቈጠረች፥ ምንም እንኳን መካን ብትሆን፥ ዕድሜዋ እንኳ ካለፈ በኋላ
ዘርን ለመፅነስ ኃይልን በእምነት አገኘች።” (ዕብ. 11፡ 11)
አብርሃም “ዘርህ እንደ ሰማይ ከዋክብት እንዲሁም እንደምድር አሸዋ ይበዛል” የሚለው ተስፋ በተሰጠው ጊዜ
ሚስቱ ሣራ መካን ነበረች።
ነገሩን የበለጠ ከባድ ያደረገው ደግሞ ተስፋው ለመፈጸም ጊዜ ሲወስድ የመውለጃዋ እድሜ እያለፈ መሆኑ ነበር።
እናም ሣራ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ተስፋ በተጠራጠረች ጊዜ ከአገልጋይዋ ከአጋር አብርሃም እንዲወለድ
ሁኔታዎችን አመቻቸች።
እግዚአብሔር ግን የራሱን ዕቅድ የሚተገብርበት ጊዜ ነበረው። ታዲያ ልጅ የመውለጃዋ ጊዜ ደርሶ ከመለኮት የዛሬ
አመት ልጅ እንደምትወልድ መልዕክት ሲመጣ ሣራ “ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል” ብላ ሳቀች። ለማመን ከበዳት።
“አብርሃምና ሣራም በዕድሜአቸው ሸምግለው ፈጽመው አርጅተው ነበር፥ በሴቶች የሚሆነውም ልማድ ከሣራ
ተቋርጦ ነበር። ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች፦ “ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም
ፈጽሞ ሸምግሎአል።” እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ “ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን
ሳቀች? በውኑ ለጌታ የሚሳነው ነገር አለን? የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ እመለሳለሁ፥ ሣራም ልጅን
ታገኛለች።” ሣራም ስለ ፈራች፦ “አልሳቅሁም” ስትል ካደች። እርሱም፦ “አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ” አላት።” (ዘፍ.
18፡ 11-15) ይገርማል!
ምንም እንኳን ሣራ በመጀመሪያ በጥርጣሬ የሳቀች ቢሆንም “በውኑ ለጌታ የሚሳነው ነገር አለን?” የሚለው ቃል
ምነት ሆናት። ተስፋ የሰጠው የታመነ እንደሆነ ስለ ቆጠረች፣ ለመፀነስ ኃይልን በእምነት አገኘች።
እኛም እንደ ሣራ እግዚአብሔርን በመጠራጠር ለብዙ ኪሳራ ተዳርገን ቢሆን እርሱ ትላንት እንዲህ ነበራችሁ
በማለት ተስፋ አይቆርጥብንም፤ ድካማችንንም በማስተዋል እምነታችንን የሚያበረታን ቃል ይሰጠናል። በእርሱም
ብንታመን እኛም እንደ ሣራ በእምነት ኃይልን እናገኛለን።
ከሣራ እምነት በመነሳት እግዚአብሔርን ስለ እምነት በጸሎት ምን ትጠይቁታላችሁ ?
የፀሎት ርዕሳችሁን ከዚህ🛐
በታች ዘርዝሩና ቀኑን ሙሉ በልመና መንፈስ ይዋሉ።
.......P/john............
t.me/borforiconn
t.me/yekal_sink