Bete Mariam - ቤተ ማርያም

Bete Mariam - ቤተ ማርያም ይህ ገጽ የኢትዮጵያዊት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ሥርዓትን የጠበቀ ትምህርት የሚተላለፍበት ነው። (አርጋኖን ዘሠሉስ)

፩ ኑ እንግዲህ ይህችን ንጽህት በግ እናክብራ፣ እናግናት፣ የደኀነታችን መሥዋዕት የሚሆነውን በግ ወልዳልናለችና።
፪ ንጹሑን የዝናብ ውሃ የተሸከመችልን የብርሃን ደመና እርሷን እናግናት ፤ እናትነትን ከድንግልና አስተባብራ የያዘች እርሷን ኑ እናመስግናት።
፫ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የአብርሃም ልጆች መመኪያ የሆነች እርሷን ኑ ክብሯን ገናንነቷን እንናገር። ጌታን የወለደችልን ሰማይና ምድር የማችሉትን እሱን የወለደችልን እመቤታችን ድንግል ማርያም ክብርና ውዳሴ ይድረሳት አሜን!!!

በሃይማኖት ላይ የተመሠረተ ጭፍን ጥላቻ፣ የአርሲው በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ዘግናኝ ጭፍጨፋ፣ ግድያከመቶ ዓመታትን የተሻገረው የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ እንዲሁም የመድኃኔ ዓለ...
03/06/2026

በሃይማኖት ላይ የተመሠረተ ጭፍን ጥላቻ፣ የአርሲው በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ዘግናኝ ጭፍጨፋ፣ ግድያ
ከመቶ ዓመታትን የተሻገረው የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ እንዲሁም የመድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዝርፊያ፣ የበርካታ ክርስቲያኖች ስደት.....
ሰዎች በሃይማኖትና በብሔር ልዩነት ምክንያት ብቻ በሌላው ላይ የጭካኔ እና የጥላቻ በትረ-ሙሴ የሚያነሱት ለምንድን ነው? ይህ ዓይነቱ ጥላቻ ከሰው ልጅ ሰብዓዊነት መውረድ፣ ከጽንፈኝነት እና ሌላውን ወገን ለመጨቆን እንዲሁም ለማስፈራራት ከማሰብ የሚመነጭ የድንቁርና ጥግ ነው ብዬ አምናለሁ። ሰው ሆኖ በሰው ሕይወት ላይ መጨከን ሌላ ምን አንድምታ ይኖረዋል?!
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች ብbእንጹሃን ኦርቶዶክሳዊያን እንዲሁም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ጥቃት ልብ ሰባሪ ነው። የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬያቸው መፈናቀላቸው በእጅጉ የሚያዝንና ልብ የሚሰብር ድርጊት ነው። ዘመናት በፍቅር እና በሰላም አብሮ በኖረው ሕዝብ መካከል እንዲህ ያለውን የጥፋት ዘር መዝራት፣ የጋራ ማኅበራዊ እሴቶቻችንን እና ሰብዓዊነታችንን የሚንድ እኩይ ተግባር ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
ይህ በእምነት ማዕቀፍ ውስጥ የማይወድቅ፣ ሰላማዊ ሰዎችን ለሞትና ለስደት የዳረገው አሰቃቂ ጥቃት የነቢዩ ዳዊትን መዝሙር ያስታውሰናል፦
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪) (መዝ. 78፥2)
የቅዱሳን እና የንጹሐን ደም በግፍ ሲፈስ፣ ታሪካዊ መቅደሶች ሲፈርሱ ዝምታው ሊያበቃ ይገባል። ሃይማኖትም ሆነ ሰብዓዊነት ንጹሐንን መግደልንና የእምነት ቦታዎችን ማውደምን አያስተምሩም። ይህንን አስነዋሪ ድርጊት ሁላችንም በአንድ ድምፅ ልናወግዘው እና ለተጎዱ ወገኖቻችን ከጎናቸው ልንቆም ይገባል።
"ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፏል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት!።” ማቴ. ፳፩÷፲፫ (ማቴ. 21፥13) ያለው ክርስቶስ የበቀል ጅራፉን ያንሳ እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል!!!
ለተጎዱትና ውድ ሕይወታቸውን ላጡት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስን እንዲሁም መጽናናትን፣ ለሀገራችን ደግሞ ዘላቂ ሰላምን እመኛለሁ!

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት...
03/06/2026

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው። የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው። የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል። በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ምንጭ፦ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት/EOTC His Holiness Secretariat Office

ትላንት በምሥራቅ አርሲ ዞን እንደተለመደው የኦርቶዶክስ  ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ወገኖቻችን ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ተደረጐባቸዋል። አብያተ ክርስትያናት ተቃጠለዋል፣ ወድመዋልም። የተረፉት ወገኖ...
02/06/2026

ትላንት በምሥራቅ አርሲ ዞን እንደተለመደው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ወገኖቻችን ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ተደረጐባቸዋል። አብያተ ክርስትያናት ተቃጠለዋል፣ ወድመዋልም። የተረፉት ወገኖቻች ቤት ንብረታቸው ጥለው እግራቸው ወዳመጣላቸው ጫካ ተሸሽገዋል። እኛም የነሡን ሞት ለምንደነው ይሄን 'ያህል ሰው ሞተ' ብለን ወደ ቁጥር እንቀይራቸዋለን። እነዚህ ዜጐች የሚከላከልላቸው እና የሚጠብቃቸው አካል የሌላቸው አቀመ ቢስ ናቸው። አንጀት የሚበሉ ምስኪኖች፤ ሞት ደጃቸው አድፍጦ ተራ በተራ የሚወስዳቸው ለሰማዕትነት የታጩ። ከዚህ ሁሉ ደግሞ ከማዘን እና ከመቆጨት ባለፈ ምንም ማድረግ አለመቻል ልብን ይሰበራል። እግዚአብሔር አምላክ የሰማዕታትን ዋጋ ያድላቸው። 😰😰😰

31/05/2026
ደብረ ምጥማቅግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በ...
29/05/2026

ደብረ ምጥማቅ

ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።
እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም። ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል። አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ።
ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል ።
ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው። ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል። ሁለተኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ።
ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር።
እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳዪኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች። ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል።
እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል። ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ።

የእመቤታችን ረድኤት እና በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን 🙏 መልካም በዓል!

ግንቦት ፲፪አቡነ ተክለ ሃይማኖት(ፍልሠታቸው)በዚችም ቀን የመነኰሳት ሁሉ አለቃ ሐዋርያና ሰማዕት የታላቁ መምህር የክቡር አባታችን ተክለ ሃይማኖት የሥጋው ፍልሰት ሆነ ። የፍልሰቱም ምክንያት ...
20/05/2026

ግንቦት ፲፪

አቡነ ተክለ ሃይማኖት(ፍልሠታቸው)

በዚችም ቀን የመነኰሳት ሁሉ አለቃ ሐዋርያና ሰማዕት የታላቁ መምህር የክቡር አባታችን ተክለ ሃይማኖት የሥጋው ፍልሰት ሆነ ። የፍልሰቱም ምክንያት በሃምሳ ስድስት ዓመት ከዋሻ ውስጥ ወደ አነፁልህ መቃብር ያፈልሱታል ብሎ እግዚአብሔር የነገረው ዘመን በደረሰ ጊዜ ያን ጊዜም ተአምር ተደርጎ ዕውራን አዮ አንካሶችም ተስተካከሉ ። ይህም በወራሴ መንበሩ በአባ ሕዝቅያስ ዘመን ሆነ ዕለቱም ግንቦት ዐሥራ ሁለት ነው።
ለእግዚአብሔ ምስጋና ይሁን፣ እኛንም ተጋዳይ በሆነ ሰው በጻድቁ አባታችን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ሁሉ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ግንቦት ፲፪

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ግንቦት ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን በኢየሩሳሌም ሀገር ወደሚኖር ነቢይ ዕንባቆም የመላእክት አለቃ ሚካኤልን እግዚአብሔር ላከው እርሱም የማሳውን እህሎች ለሚያጭዱ ምሳ ሊወስድ ወዶ ተሸክሞ ሳለ ።

ቅዱስ ሚካኤልም ዕንባቆምን ምግብን እንደተሸከመ በአናቱ ጠጉር ይዞ ወደ ባቢሎንም አገር አድርሶ ዳንኤል ወደ አለበት የአንበሶች ጒድጓድ አስገባው ዳንኤልንም ከዚያ ምግብ መገበው ከዚህም በኋላ ዕንባቆምን ከምግቡ ጋራ ወደ ይሁዳ ምድር መልሶት ወዲያኑ እህሉን በሚያጭዱት ዘንድ ቆመ። ስለዚህ ለከበረ መልአክ ለመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በየወሩ መታሰቢያውን እንድናደርግ የቤተክርስቲያን መምህራን አዘዙን፤ አማላጅነቱ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

ምንጭ ስንክሳር ዘግንቦት

ግንቦት ፩ልደታ ለማርያም ድንግልአንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተባረከ የግንቦት ወር መዓልቱ ዐሥራ አራት ሰዓት ነው ከዚህም ይጨምራል ።በግንቦት አንድ በዚችም ቀን...
09/05/2026

ግንቦት ፩

ልደታ ለማርያም ድንግል
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተባረከ የግንቦት ወር መዓልቱ ዐሥራ አራት ሰዓት ነው ከዚህም ይጨምራል ።

በግንቦት አንድ በዚችም ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኀነት የሆነባት ናት ። ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ ። ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቅበሉም ነበርና ።

እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር ። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ኀሳባቸውን ተመለከተ ።

ክቡር እያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኀነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው ።

በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ።

የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች ። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች። ስሟንም ማርያም ብላ ሰየመቻት። ትርጓሜውም እመቤት ነው፤ ደግሞም ሀብትና ስጦታ ማለት ነው።
እውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ናት፣ ሁላችሁም በርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፣ የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን፣ በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ፣ ፍቅሯ፣ ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን አሜን።

ምንጭ፣ ስንክሳር ዘወርሃ ግንቦት
ይቆየን!

ሚያዝያ 30ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊአንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሠላሳ በዚች ቀን ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳት አለቃ የሆነ ወንጌልን የጻፈ ሐዋርያው...
08/05/2026

ሚያዝያ 30

ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሠላሳ በዚች ቀን ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳት አለቃ የሆነ ወንጌልን የጻፈ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት አረፈ ።

የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አርስጦቡሎስ ነው እርሱም ከአምስቱ አገሮች የሆነ የእናቱም ስም ማርያም ነው እርሷም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ተጽፋለች እርሱም አስቀድሞ ስሙ ዮሐንስ ነው ። በግብረ ሐዋርያት ማርቆስ በተባለ በዮሐንስ እናት ቤት ሐዋርያት ይጸልዩ ነበር ተብሎ እንደ ተጻፈ ። እርሷም ባለጸጋ ነበረችና የዮናናውያንን የሮማይስጥን የዕብራይስጥን ትምህርት ለልጅዋ ለማርቆስ አስተማረችው ።

በአደገም ጊዜ በርናባስ ወንጌልን ለመስበክ ከጳውሎስ ጋራ ሲሔድ ይዞት ሔደ በእነርሱም ላይ የሚደርስባቸውን መከራ አይቶ በጵንፍልያ ከተማ ሳሉ ትቷቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ።

ሐዋርያትም በተመለሱ ጊዜ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አሕዛብ እንደ ተመለሱ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ላይ ድንቅ ተአምራትን እንዳደረገ ተናገሩ ። ይህ ብላቴና ማርቆስም ከእርሳቸው ስለ መለየቱ አዘነ ተጸጸተ ።

ከዚያም አብሮአቸው ሊሔድ ፈለገ አስቀድሞ ትቷቸው ስለተመለሰ ጳውሎስ ሊአስከትለው አልወደደም በርናባስ ግን ወሰደው አጎቱ ነውና ። በርናባስም ከአረፈ በኋላ ወደ ሮሜ አገር ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሒዶ ለእርሱ ደቀ መዝሙሩ ሆነ በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስ የተረጐመለትን ወንጌልን ጻፈ በሮሜ አገርም አስተማረበት ። ከዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝና በሐዋርያትም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ ። በውስጥዋም የከበረ ወንጌልን አስተማረ ደግሞም በአፍራቅያና በአምስቱ አገሮች በርቃ በሚባልም አገር ወደ እስክንድርያ ከተማ በገባ ጊዜ ጫማው ተቆረጠ ።

በዚያም በከተማው መግቢያ ጫማ ሰፊ ነበረ ። ቅዱስ ማርቆስም እንዲሰፋለት ለርሱ ሰጠው ሲሰፋም ጣቱን ወግቶ ሰነጠቀው ከእርሱም ደም ፈሰሰ በዮናኒም ቋንቋ ኢታስታዖስ አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው ። ቅዱስ ማርቆስም ስሙን የምትጠራው አውቀኸው ነውን አለው እንጠራዋለን እንጂ አናውቀውም አለ ።

እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ አባታችን አዳም ትእዛዙን እንደተላለፈ የጥፋት ውኃም እንደ መጣ ሙሴንም እንደላከውና እስራኤልን ከግብጽ እንዳወጣቸው ሕግንም እንደ ሠራላቸው ናቡከደነጾርም ወደ ባቢሎን ማርኮ እንደወሰዳቸውና ከሰባ ዓመት በኋላ ወደ አገራቸው ኢየሩሳሌም እንደ ተመለሱ ክርስቶስ ሥጋ በመልበስ ወደ ዓለም ስለ መምጣቱ ነቢያት ትንቢት እንደ ተናገሩ ያስተምረው ዘንድ ጀመረ ።

ከዚያም በኋላ ወደ ምድር ምራቁን ትፍ ብሎ ጭቃ አድርጎ ጣቱን ቀባው ወዲያው ዳነ በጌታችንም አመነ ። ያም ሰፊ ስሙ አንያኖስ ነው ። ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወስዶ ልጆቹን ዘመዶቹንም ወደ ርሱ አቀረበ እሱም አስተምሮ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ ሰዎች በብዙ ጊዜ የቅዱስ ማርቆስን ዜና ሰምተው የአገር ሰዎች ሊግድሉት ተሰበሰቡ፣ እርሱም አንያኖስን ኢጲስቆጶስ አድርጎ ሾሞ ልጆቹን ቄስና ዲያቆናት አድርጎ ከዚያም ወደ አምስቱ አገሮችም ወጥቶ አስተማረ። በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው። በእርሳቸውም ዘንድ ሁለት ዓመት ኖረ ኤጲስቆጶሳትን ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው። ይህ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ሊገድሉት ከሀዲያንም በብዙ ድካም ፈለጉት፣ ባገኑትም ጊዜ ከሀዲያኑ በአንገቱ ውስጥ ገመዶች አድርገው በከተማው ሁሉ ጎተቱት ብዙም መከራ አጸኑበት፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ግን ቅዱስ ማርቆስን አጽናናው፣ ቃልኪዳንም ሰጠው። ከሀዲዎቹ በማግስቱም ሁለተኛው ገመዶችን በአንገቱ አድርገው በሀገሮች ሁሉ ጎተቱት፤ በቀኑም መጨረሻ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
ከሀዲዎችም ታላቅ እሳትን አንድደው የቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ከውስጡ ጨመሩ። በክብር ባለቤት በጌታችን ፈቃድም ንውጽውጽታ ጨለማ ቀዝቃዛ ነፋስ መብረቅና ነጎድጓድ ሆነ። ፀሐይም ጨለመ። ከሀዲዎችም ሸሹ። መእመናንም መጥተው የሐዋርያው የቅዱስ ማርቆስ ሥጋ ወሰዱ፣ ምንም ጥፋት ሳይደርስበት ደኅና ሆኖ አገኙት። በምልካም ልብስም ገንዘው በጥሩ ቦታ አኖሩት መታሰቢያውንም አደረጉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ማርቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

ምንጭ ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ

"ማንስ ነው ከቅዱሳን ሁሉ በላይ እንደሆነች ያላስተዋለ? እግዚአብሔር ለአገልጋዮቹ የሚልቅ ጸጋን ከሰጠና የሚነኩት ሁሉ ከበሽታው ከተፈወሰ፣ ጥላቸው ያረፈበት ተአምር ከተፈፀመለት፣ ጴጥሮስ በጥ...
29/04/2026

"ማንስ ነው ከቅዱሳን ሁሉ በላይ እንደሆነች ያላስተዋለ? እግዚአብሔር ለአገልጋዮቹ የሚልቅ ጸጋን ከሰጠና የሚነኩት ሁሉ ከበሽታው ከተፈወሰ፣ ጥላቸው ያረፈበት ተአምር ከተፈፀመለት፣ ጴጥሮስ በጥላው ካዳነ (የሐዋ 5÷15)፣ የጳውሎስ የልብሱ ጨርቅ ዕራፊ መናፍስትን ካወጣ (የሐዋ 19÷11)፤ ለእናቱማ ምን አይነት ስልጣንና ኃይል ተሰጥቷት ይሆን? ለቅዱሳኑ ይኽን ያኽል ድንቅ እንዲያደርጉ ባለሟልነትን ከሰጣቸው ወልዳ ላሳደገችው እናቱማ ምን ያኽል ይሰጣት ይሆን? በምን አይነት ስጦታ አስጊጧት ይሆን? ጴጥሮስ "ክርስቶስ አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ " ስላለው ብፁዕ ከተባለና የመንግሥተ ሰማያት ቁልፍ ከተሰጠው (ማቴ16÷16-19)፤ እርሷ ከሁሉም ይልቅ እንዴት የተባረከች (ብፅዕት) አትሆን? (ሉቃ1÷45)፤ ጳውሎስ ታላቅ ክብር ያለውን የክርስቶስን ስም በመሸለሙ "ምርጥ ዕቃ" ከተባለ (የሐዋ 9÷15)፤ የአምላክ እናትማ የምእመናን ምግብ የኾነ መናውን ሳይሆን የሕይወት ሰማያዊ እንጀራን ያስገኘች እርሷ ምን ዓይነት ልዩ ዕቃው ትሆን? ነገር ግን ስለ እርሷ ብዙ እናገራለሁ ብዬ ስለ ክብሯ ጥቂት በመናገር እራሴን በኅፍረት ውስጥ እንዳልጨምር እፈራለሁ ስለዚህ ካሁን ወዲህ የንግግሬን መልህቅ ስቤ በዝምታ ወደቤ ላይ ማረፍን መርጫለሁ"
(ቅዱስ ባስልዮስ)

"ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ እስመ ወለድኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን።"
✧ ቅዳሴ ማርያም ዘአባ ሕርያቆስ ✧
✦ትርጉም✦
"ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን ከፍ ከፍም እናደርግሻለን እውነተኛ የጽድቅ መብልንና እውነተኛ የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና ።"
✦ ✢◦✞◦✢ ✦
የሚቀበለው የልመናዋ ክብር ፍፁም የሆነ የረድኤቷ ኃብት ጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሞላ የተወደደ የልጅዋ ቸርነት በእዉነት ከሁላችን ጋራ ይሁን ለዘልአለሙ አሜን። ቸሪቱ አማላጂቱ ቅድስት ሆይ ልጅሽ ይቅር ይለን ዘንድ ለምኝልን።

ሰባቱ የመስቀል ላይ ጩኸቶችጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ በይሁዳ አማካይነት ተላልፎ ከተሰጠበት ሐሙስ ምሽት ጀምሮ ስቃይ ሲያጸኑበት ቆይተዋል፡፡ በዕለተ ዐርብም ይሰቅሉት ዘን...
10/04/2026

ሰባቱ የመስቀል ላይ ጩኸቶች

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ በይሁዳ አማካይነት ተላልፎ ከተሰጠበት ሐሙስ ምሽት ጀምሮ ስቃይ ሲያጸኑበት ቆይተዋል፡፡ በዕለተ ዐርብም ይሰቅሉት ዘንድ አስከ ቀራንዮ መስቀል አሸክመው የተለያዩ ጸዋትወ መከራ እያጸኑበት ወስደውታል፡፡ በመሰቀል ላይ በሁለቱ ወንበዴዎች መካከል ከተሰቀለበት ሰዓት ጀምሮም የተናገራቸው ቃላት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ሰባቱ የመስቀል ላይ ጩኸቶች ወይም “ሰባቱ አጽርሐ መስቀል” በማለት ሰይማ ታስባቸዋለች፡፡ እነርሱም በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱ ሲሆን ቀጥለንም በዝርዝር እንመለከታቸዋለን፡-

፩ኛ. “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማሰበቅታኒ፤ አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ”፡–

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በዘጠኝ ሰዓት የተናገረው ቃል እንደሆነ በወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ “በዘጠኝ ሰዓትም ጌታችን ኢየሱስ ኤሎሄ ኤሌሄ ላማሰበቅታኒ ብሎ በታላቅ ቃል ጮኸ፡፡ይኸውም አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? ማለት ነው፡፡ በዚያም ቆመው የነበሩት በሰሙ ጊዜ ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ” (ማቴ.፳፯፥፵፭) እንዲል፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ ብሎ የተናገረበት መሠረታዊ ሐሳብ፡- ያችን የድኅነት ቀን ከአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በኋላ ያለችውን ዕለተ ዓርብ በተስፋ ይጠባበቅ የነበረውን አዳምን ወክሎ እንደሆነ አበው ያስረዳሉ፡፡ (ማቴ.፳፯፥፵፭ አንድምታ ትርጓሜ)፡፡ በመሆኑም አምላኬ አምላኬ ያለው በአዳም ተገብቶ እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ እንዲሁም አምላኬ አምላኬ ያለው ሰውነቱን ሲገልጥ ነው፡፡ ይህም ፍጹም አምላክነቱንና ፍጹም ሰውነቱን ማለት ነው፡፡

፪ኛ. “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ”፡–

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደል ሳይኖርበት እንደ በደለኛ ተቆጥሮ በሁለት ወንበዴዎች መካከል ነበር የተሰቀለው፡፡ “ከእርሱ ጋርም ሁለት ወንበዴዎችን አንዱን በቀኙ አንዱን በግራው ሰቀሉ፡፡ መጽሐፍ ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ ያለው ተፈጸመ” (ማር.፲፭፥፳፯) ይላልና፡፡

በቀኝ በኩል የተሰቀለው ወንበዴ ጌታችንን “አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ›” አለው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ እንዲህ አለው “እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ፡፡” (ሉቃ.፳፫፥፵፫)፡፡

፫ኛ. “አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ”፡–

“ያን ጊዜም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድምጹን ከፍ አድርጎ አባት ሆይ ነፍሴን በአንተ እጅ አደራ እሰጣለሁ ብሎ ጮኸ፤ ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ” (ሉቃ.፳፫፥፵፮)፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ “አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ” በማለት የተናገረው ቃል የተሰቀለው እርሱ እግዚአብሔር ወልድ እንደሆነና የአብ የባሕርይ ልጁ እንደሆነ ያሳያል፡፡

፬ኛ. “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው”፡–

ምንም በደል ሳይኖርበት አይሁድ በክፋት ተነሳስተው መከራ አጸኑበት፤ ያን ሁሉ የግፍ ግፍ በጭካኔ የተሞላ መከራ ሲያደርሱበት ልባቸውን ዲያብሎስ ስላደነዘዘው የሚራራ ልብ አጡ፡፡በዚያንም ጊዜ መምህረ ይቅርታ ቸሩ አምላካችን ለሠቃዮቹ “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ” (ሉቃ.፳፫፥፴፬)፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደለኞች ይቅርታን ያገኙ ዘንድ ይቅር በላቸው አለ፡፡ ልመናውንም ያቀረበው ወደ ባሕርይ አባቱ ነው፡፡ ከባሕርይ አባቱ ጋር ደግሞ በባሕርይ፣ በሕልውና፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ አንድ ናቸው፡፡ እንዲሁም የሰውን ባሕርይ ባሕርይ አድርጎ ፍጹም ሰው እንደሆነ ሲያስረዳ ነው፡፡ይህም በደለኞችን ከራሱ ጋር ያስታረቀበት የፍቅር ድምጽ ነው፡፡

አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅርበላቸው ማለቱ አባት ሆይ ብሎ የባሕርይ ልጅነቱን ከመግለጹ በተጨማሪ ይቅር በላቸው ማለቱ ጠላትን ይቅር ማለት የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ የመሆኑ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ምክንያቱም ጠላቶቻችሁን ውደዱ ብሎ ያስተማረ እርሱ ብቻ ነውና፡፡

፭ኛ. “እነሆ ልጅሽ፤ እናትህ እነኋት”፡–

“ጌታችን መድኀኒታችንን ኢየሱስም እናቱንና የሚወደውን ደቀ መዝሙሩን ቆመው ባያቸው ጊዜ እናቱን ‘አንቺ ሆይ እነሆ ልጅሽ’ አላት፡፡ ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩን ‘እናትህ እነኋት’ አለው፡፡ ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ተቀብሎ ወደ ቤቱ ወሰዳት” (ዮሐ.፲፱፥፳፮)፡፡ ደቀ መዝሙሩ ተብሎ የተጠቀሰው ጌታችን ይወደው የነበረ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊው ነው፡፡ ይህንንም የጻፈው እርሱ ነው (ዮሐ.፳፩፥፳፬)፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቢሆንም ሐሙስ ማታ እረኛው ሲያዝ ከተበተኑት በጎች ጋር አብሮ አልሸሸም፡፡ በዚያች በአስጨናቂዋ ሰዓት ከጌታችን ጋር እስከ እግረ መስቀሉ ተጓዘ፡፡የክርስቶስ ፍቅር ፍርሃቱን ሁሉ አርቆለት የአይሁድን ቁጣና ዛቻ ሳይፈራ ጸንቶ በመቆሙ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለእኛ ሁሉ እርሱ በኩል ተሰጠችን፡፡ እናታችን ድንግል ቅድስት ማርያም ሁል ጊዜም ቢሆን ከእግረ መስቀሉ ሥር ለሚገኙ፣ ልባቸው ቀራንዮን ለሚያስብ ሁሉ እናት እንድትሆን እነርሱም ልጆቿ እንዲሆኑ በቅዱስ ዮሐንስ በኩል ተሰጥታናለች፡፡

በመሆኑም “እነሆ ልጅሽ፤ እናትህ እነኋት” የሚለው የመስቀሉ ቃል በመስቀል ላይ የተከፈለልንን ዋጋ አስበን በእርሱ አምነን በምግባር ታንጸን እንደ ፈቃዱ በምንኖር ክርስቲያኖችና ለድኅነታችን ምክንያት በሆነች በእመ አምላክ በቅድስት ድንግል ማርያም መካከል የእርሷ እናትነት፣ የእኛ ልጅነት የተመሠረተበት የፍቅር ቃል ነው፡፡

፮ኛ. “ተጠማሁ”፡–

“ከዚህም በኋላ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ሁሉ እንደ ተፈጸመ ባየ ጊዜ የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ‘ተጠማሁ’ አለ” (ዮሐ.፲፱፥፳፰)፡፡

ውኆችን በእፍኙ የሰፈረ፣ የባሕር አሸዋን የቆጠረ፣ ውኆችንም ጠርቶ በምድር ፊት ላይ የሚያፈሳቸው፣ የባሕር ጥልቀትንና ዳርቻን የወሰነ፣ የኤርትራን ባሕር እንደ ግድግዳ ያቆመ አምላክ “ተጠማሁ” ብሎጮኸ፡፡ (ኢሳ.፵፥፲፪፣አሞ.፱፥፮)፡፡

“የተጠማ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ በእኔም የሚያምን መጽሐፍ እንደ ተናገረ የሕይወት ውኃ ምንጭ ከሆዱ ይፈልቃል” (ዮሐ.፯፥፴፯) በማለት እርሱ የሕይወት ውኃ እንደሆነ ተናገረ፡፡ አምላክ ሲሆን “ተጠማሁ” ብሎ መጮኹ ስለ ምንድንነው ብለን ቅዱሳት መጻሕፍትን ስንመረምር፡- አንደኛ የመከራውን ጽናት፣ ከሚነገረው በላይ መከራውን እንዳጸኑበት የሚያሳይ ሲሆን፤ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ እርሱ የተጠማው የሰውን መዳን ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በዚያን ወቅት እንኳ ከክፉ ሥራው ተመልሶ የሚጸጸት፣ የሚራራ፣ ንስሓ የሚገባ ሰው በማጣቱ መድኃኒት እርሱ ቀርቦ ሳለ የሰው ልጅ ባለማስተዋሉ ወደ እርሱም በፍቅር ባለመቅረቡና ባለመመለሱ ተጠማሁ አለ፡፡

፯ኛ. “ሁሉ ተፈጸመ”፡–

”ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስም ሆምጣጤውን ቀምሶ ሁሉ ተፈጸመ አለ፡፡ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን ሰጠ” (ዮሐ.፲፱፥፴)፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕተ ዐርብ በመስቀል ላይ ሳለ ‘ተፈጸመ’ ብሎ መናገሩ ብዙ ትርጉም ያለው ቃል ነው፡፡ እነርሱም፡-

በነቢያት ስለ እኔ የተነገረው ትንቢት፣ የተመሰለው ምሳሌ፣ በቅዱሳን አበው የተቆጠረው ሱባኤ፣ ጊዜው ደርሶ የአዳም ተስፋ ተፈጸመ፡፡

የሰው ልጅ በዲያብሎስ አገዛዝ በሞትና በጨለማው ሥልጣን፣ በአጋንንት ወጥመድ ታስሮ የሚኖርበት የፍዳ ዘመን አለቀ ተፈጸመ፡፡

በእግዚአብሔርና በሰው፣ በመላእክትና በሰው፣ በሰማይና በምድር መካከል ቆሞ የነበረው የጥል ግድግዳ ፈረሰ፣ የተጻፈው የዕዳ ጽሕፈት ተደመሰሰ፣ የሰው ልጅ ዕዳ በደል ተከፈለ በአምላክ የቤዛነት ሥራ ሁሉ ተፈጸመ ማለት ነው፡፡

እነዚህ ከአንድ እስከ ሰባት የጠቀስናቸው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መራራውን መከራ እየተቀበለ የተናገራቸው የመጨረሻ ቃላቶቹ ናቸው፡፡ ወደዚህ ዓለም ሰው ሆኖ የመጣበትን ዓላማ አከናውኖ ሲጨርስ በመጨረሻ “ተፈጸመ ኵሉ” በማለት ነፍሱን ከሥጋው ለየ፡፡ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶም በሲኦል ባርነት ለነበሩት አዳምና ልጆቹ ነጻነትን ሰበከላቸው፡፡ በአካለ ሥጋ ደግሞ ወደ መቃብር ወርዶ ሙስና መቃብርን አጠፋል።

በመስቀል ላይ በከፈለው የሕይወት ዋጋ የኢትዮጵያን መከራዋን፣ ሰቆቃዋንና ችግሮቿን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያስወግድላት። አሜን! መልካም የትንሳዔ በዓል ይሁንልን።

የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን አሜን፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን

Address

Adama
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bete Mariam - ቤተ ማርያም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Bete Mariam - ቤተ ማርያም:

Share