Anketse Bitsuan

Anketse Bitsuan አንቀጸ ብጹዓን የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብጹዓን ሰንበት ትምህርት ቤት
(1)

12/04/2026
የ2018 ዓም የፋሲካ የበዓል የጥቅል ስጦታ ተከናወነ።ሰንበት ትምህርት ቤቱ በየአመቱ በፋሲካ ሌሊት ነዳያንን ከሚመግበው ውጪ የበዓል የፍቅር ስጦታ በልግስና በሰላም መጠናቁ ተገልጿል።በመርሃግ...
12/04/2026

የ2018 ዓም የፋሲካ የበዓል የጥቅል ስጦታ ተከናወነ።

ሰንበት ትምህርት ቤቱ በየአመቱ በፋሲካ ሌሊት ነዳያንን ከሚመግበው ውጪ የበዓል የፍቅር ስጦታ በልግስና በሰላም መጠናቁ ተገልጿል።

በመርሃግብሩም ከአምስት መቶ በላይ የሚሆኑ አረጋውያን እና ህፃናት በተዘጋጀው ጥቅል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል።
ይኸውም ስጦታ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዲስ በሚገነባው ህንፃ፣በኮዬ ፈጬ በሚገኙ ተረጂዎች፣ እና በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ተከናውኗል።

ተረጂዎቹም ሰንበት ትምህርት ቤቱ በቋሚነት የሚያግዛቸውና ከወረዳ ለተላኩ ወላጆች እገዛ ተደርጓል።

ይህን አገልግሎት በአይነት፣ በገንዘብ እና በጉልበት እንዲሁም በማስተዋወቅ ላገለገላችሁ ተቋማት፣(ዳሸን ባንክ)
ግለሰቦች፣የሚዲያ አጋሮች (ብስራት ኤፍ ኤም 101.1)
በመላው አለም የምትገኙ ምዕመናንን እና
የሰንበት ትምህርት ቤቱን አባላት እንዲሁም አገልጋዮች ሁሉ በነዳያን አምላክ ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን።
የከርሞ ሰው ይበለን።

መልካም የፋሲካ በዓል

🌟 የአንድ ሰው የፋሲካ ምሳ በ200 ብር ብቻ! 🌟የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብጹአን ሰንበት ትምህርት የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለወገኖቻችን ማዕድ ለማጋራ...
11/04/2026

🌟 የአንድ ሰው የፋሲካ ምሳ በ200 ብር ብቻ! 🌟

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብጹአን ሰንበት ትምህርት የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለወገኖቻችን ማዕድ ለማጋራት ሥራ ጀምሯል፡፡

ዓላማችን፡ በሺዎች የሚቆጠሩ አቅመ ደካማ ወገኖችን የትንሣኤ ደስታ ተካፋይ ማድረግ።

የእርስዎ ድርሻ፡ 200 ብር ብቻ (የአንድ ሰው ምሳ) በመለገስና ይህንን መልእክት ለ10 ሰው በማጋራት የደስታው ተካፋይ ይሁኑ::@ትንሣኤ #የትንሣኤውብርሃን

"ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል።" (ምሳሌ 19፡17)በ2018 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል 5,000 አቅመ ደካሞችን ማዕድ ለማጋራት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህ...
11/04/2026

"ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል።" (ምሳሌ 19፡17)

በ2018 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል 5,000 አቅመ ደካሞችን ማዕድ ለማጋራት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ተዘጋጅቷል። የእርስዎ ትንሽ ስጦታ ለወገኖቻችን ታላቅ ደስታ ናት!

🎁 የልግስና ጥቅሎች፦

• 2,500 ብር (ሙሉ ማዕድ)

• 1,500 ብር (ግማሽ ማዕድ)

• 1,000 ብር (ሩብ ማዕድ)

• 200 ብር (የአንድ ሰው ምሳ)

🏦 የባንክ አካውንት (CBE)፦ 1000370068066 (ሰናይት ስሜ / ታምሩ ጥላሁን)

📲 ቴሌ ብር፦ 0911242563 (ታምሩ ጥላሁን)

"የማይራብበት ትንሣኤን አብረን እናክብር!"

# #ኢትዮጵያ ሰው

"የማይራብበት ትንሣኤን አብረን እናክብር!"

#ኢትዮጵያ ሰው

በዚህ ትንሣኤ የሌላውን ማዕድ እናብራ! በራሳችን ቤት ብቻ ሳይሆን፣ በወገናችን ማዕድ ላይ ደስታ ሲፈጠር በዓሉ እውነተኛ በዓል ይሆናል። የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ...
10/04/2026

በዚህ ትንሣኤ የሌላውን ማዕድ እናብራ!

በራሳችን ቤት ብቻ ሳይሆን፣ በወገናችን ማዕድ ላይ ደስታ ሲፈጠር በዓሉ እውነተኛ በዓል ይሆናል። የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ለ5,000 አቅመ ደካሞች ማዕድ ለማጋራት ተዘጋጅቷል።

የእርስዎ ስጦታ የአንዲት እናትን እንባ ያብሳል፤ የአንድን ቤተሰብ ተስፋ ያድሳል።

የልግስና አማራጮች፦

🥇 ሙሉ ማዕድ፦ 2,500 ብር

🥈 ግማሽ ማዕድ፦ 1,500 ብር

🥉 ሩብ ማዕድ፦ 1,000 ብር

እንዴት መለገስ ይቻላል?

🏦 የንግድ ባንክ፦ 1000370068066

📱 ቴሌብር፦ 0911242563

📍 ወረጃ መስጫ ድንኳናችን ድረስ በመምጣት ማበርከት ይችላሉ።

"የእርስዎ ትንሽ ስጦታ፣ ለሌላው ትልቅ ደስታ!" ሼር በማድረግ ለሌሎችም አድርሱ።

#የትንሣኤውብርሃን #ልግስና #ኢትዮጵያ

የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት በዓለ ስቅለት በደብረ ብሥራት ቅዱሰ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ቤተመቅደስ እና በግቢው ውስጥ ካህናት አባቶች እንዲሁም ምዕመናን  መላው ህዝበ ክ...
10/04/2026

የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት በዓለ ስቅለት በደብረ ብሥራት ቅዱሰ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ቤተመቅደስ እና በግቢው ውስጥ ካህናት አባቶች እንዲሁም ምዕመናን መላው ህዝበ ክርስቲያን ምዕመናን በስግደትና በጸሎት እየዘከሩ ይገኛሉ።

10/04/2026

#ሕማት #ዓርብ

‹‹ሐዋርያቲሁ ከበበ እግረ አርዳኢሁ ሐጸበ ኮኖሙ አበ ወእመ ወመሐሮሙ ጥበበ›› የጸሎተ ሐሙስ "ሕጽበተ እግር" ሥርዓት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መላከ ገነት ...
09/04/2026

‹‹ሐዋርያቲሁ ከበበ እግረ አርዳኢሁ ሐጸበ ኮኖሙ አበ ወእመ ወመሐሮሙ ጥበበ››

የጸሎተ ሐሙስ "ሕጽበተ እግር" ሥርዓት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መላከ ገነት መዝገቡ ላቀው መሪነት፤ ካህናት፣ ዲያቆናት ፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት ተከብሯል።

የደብሩ አስተዳዳሪም የጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አርአያ በመከተል የካህናትና የምእመናን ሕጽበተ እግር አከናውነዋል።

ግብዓተ መሬት።የወንድም መውደድ ማሞ ሽኝት ባገለገለበት ደብር በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን አዳራሽ እና ግብዓተ መሬት በአየር ጤና ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቹ፣ወዳጅ ...
09/04/2026

ግብዓተ መሬት።

የወንድም መውደድ ማሞ ሽኝት ባገለገለበት ደብር በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን አዳራሽ እና ግብዓተ መሬት በአየር ጤና ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቹ፣ወዳጅ ዘመዶቹ ፣በአገልግሎት አብረው ያደጉ የአንቀጸ ብፁአን ሰንበት ት/ቤት አባላት እንዲሁም የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ በተገኙበት ከቀኑ በ9:00 ተፈፀመ።

አምላከ ቅዱስ ገብርኤል የገብረህይወትን ነፍስ በዓፀደ ገነት ከቅዱሳኑ ሁሉ ጎን ያሳርፍልን።

Address

Adama
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anketse Bitsuan posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Anketse Bitsuan:

Share