Ephesons Christ Church

Ephesons Christ  Church 27Peace I leave with you, my peace I give unto you: not as the world giveth, give I unto you. Let not your heart be troubled, neither let it be afraid."

(John 14:27)

12/01/2026



የኒቂያ ጉባኤ
(THE COUNCIL OF NICEA)

የኒቂያ ጉባኤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን በ325 ዓ.ም የተደረገ የቤተክርስቲያን ጉባኤ ነው። ይህን ጉባኤ የሰበሰበው ንጉሰ ነገስቱ አፄ ቆስጠንጢኖስ ሲሆን፤ የዚህ ጉባኤ ዋና ዓላማ ከአሌክሳንድሪያ የመጣው አርዮስ የሚባል ቄስ ኢየሱስ (ወልድ) ዘላለማዊ እንዳልሆነ እና ከአብ ጋር እኩል እንዳልሆነ አስተማረ። “ወልድ ያልነበረበት ጊዜ ነበር” በማለት ተናግሯል። ይህ ትምህርት የክርስቲያን ትምህርት ስላልሆነ አባቶች ሊያወግዙት ተሰበሰቡ። አርዮስም ተወገዘ፤ ይህንን ትምህርትም የያዙ ሰዎች "አርዮሳውያን" ተብለው ተጠሩ።

በዚህ ጉባኤ ላይም አርዮስ የራሱን ሙግት እንዲያቀርብ ተጠርቶ ነበር፤ የእርሱም ሙግት፡ "ወልድ በአብ የተሾመ ፍጡር ነው፤ አብ ወልድን ከፈጠረው በኋላ ወልድ ሁሉን እንዲፈጥር ስልጣንን ሰጠው" በማለት ያስቀምጣል። ይህ አስተምህሮ ስሕተት መሆኑን የተረዱት እስክንድርያ እና አትናቲዮስ ለአርዮስ ጥያቄዎችን መሰንዘር ጀመሩ።

አትናቲዮስም እንዲህ ብሎ ተናግሮ ነበር:-
"ኢየሱስ የደህንነቴ ዋስትና ነው፤ ለማዳን የበቃው አምላክ ስለሆነ ነው" በማለት ተናግሯል።

በአጭሩ አርዮስ ወልድ እርሱ ዘላለማዊ አምላክ ሳይሆን አብ በሂደት የፈጠረው ሁሉንም እንዲፈጥር ሥልጣንን የሰጠው ፍጡር ነው በማለት አስተምሯል። እንዲሁም እርሱ ከአብ ጋር እኩል አይደለም በማለት የወልድን መለኮትነት ይክዳል።

በኒቂያ ጉባኤ ላይ የክርስቶስ ኢየሱስ አምላክነት እንዲሁም ዘላለማዊ ልጅነቱ ተረጋግጦል። እንዲህም በማለት ተወስኗል:-

"ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ በተወለደ የአብ አንድያ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን። ከብርሃን በተገኘ ብርሃን፣ ከእውነተኛ አምላክ በተገኘ እውነተኛ አምላክ፣ የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል፣ ሁሉ በእርሱ የሆነ፣ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳንም ከሰማይ የወረደ፣ በመንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሰው የሆነ፣ ሰውም ሆኖ በጴንጤናዊው በጵላጦስ ዘመን ስለ እኛ የተሰቀለ፣ የታመመ፣ የሞተ፣ የተቀበረም፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ የተነሳ፣ በቅዱሳት መፅሐፍት እንደ ተፃፈ በክብር ወደ ሰማይ የዐረገ፣ በአባቱም ፍፃሜ የለውም።"

ማጠቃለያ:-

የዚህ ጉባኤ ድንጋጌ የክርስቶስን ፍፁም አምላክነት፤ እርሱ ከአብ የማይተናነሰ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ልጅ፤ በሥልጣን ከአብ ጋር እኩል የሆነ፤ መለኮት መሆኑን በደንብ አረጋግጦልናል።

ብሩካን ናችሁ!!!

 #ኢየሱስ አምላክ ሆኖ  እንዴት ያማልዳል አዋርደህ ዝቅ አድርገህ አማላጅ ነው እንዴት ትላለህ ይሉናል  #ኢየሱስን አማላጅ ነው ማለት የስድብ ጥግ ነው ማዋረድ ነው ማሳነስ ነው ይሉናልታዳያ ...
22/07/2025

#ኢየሱስ አምላክ ሆኖ እንዴት ያማልዳል አዋርደህ ዝቅ አድርገህ አማላጅ ነው እንዴት ትላለህ ይሉናል

#ኢየሱስን አማላጅ ነው ማለት የስድብ ጥግ ነው ማዋረድ ነው ማሳነስ ነው ይሉናል

ታዳያ እምላክ ሰው መባሉ ክብር ነውን?
በሰው እጅ መገረፉ መተፋቱ, በጥፊ መመታቱ ክብር ነውን?

በሰው ተገርፎ በመስቀል እርቃኑን መሰቀሉ ክብር ነውን?
በፈጠራቸው እጆች የስቃይ ሞት ማስተናገዱ ለኢየሱስ ክብር ነውን?

ይህን ከተቀበላችሁ አማላጅነቱን መቀበል ለምን ከበዳችሁ?

በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ ማስታረቅ እና ማማለድ ውርዴት ከሆነ የመስቀል ሞት, መተፋት, መገረፍ, አምላክ ሰው መሆን እንዴት ክብር ሊሆን ይችላል?

ለነገሩ እኛ ሀገር ማጣላት ማባላት እንጂ ማስታረቅ ውርዴት ነው ጀግንነት እኛ ሀገር ማጣላት ማባላት ነው፡፡

#ኢየሱስ እግዚአብሔር አይደለም እንደ ወደ ማነው የምማልደው የምሉ ሰዎች ፍፁም ሰውነቱን የካዱ ሰዎች ናቸው!!!
ኢየሱስ አዎ እርሱ እግዚአብሔር ነው
ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክም ነው!!!

በአምላክነቱ ከአምላክ ጋር በሰውነቱ ከሰው ጋር መግባባት የምችል ብቸኛ አስታራቅ፤ አማላጅና መካከለኛ ኢየሱስ ብቻ ነው፡፡

“ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥3

#ምድር ላይ እያለ ነው ያማላደው አሁን አያማልድም ይሉናል ደሞ
#ኢየሱስ ያድናል ግን እንዴት ነው የሚያድነው? ኢየሱስ ያዳነን በመስቀል ሞቶልን ነዋ።
#እሽ ጥሩ ታዲያ በመስቀል ያዳነን በምድር እያለ ነው ወይስ አሁን ነው? #በምድር እያለም አሁንም ያድናል!
#ታዲያ በምድር እያለ በመስቀል ሞት አድኖህ ዛሬም አዳኝ ነው ካልክ ዘንዳ በምድር እያለ አማልዶ ዛሬም አማላጅ ነው ማለት ስለምን ከበደህ?

!!
1ኛ -ሰው መሆን ያስፈልጋል ዕብ 5፥1
2ኛ- ወንድ መሆን ያስፈልጋል ኢሳ 9፥6
3ኛ- ልቀ ካህናት መሆን አለበት ዕብ 5፥3
4ኛ- ነውር የሌለበት መሆን አለበት ዕብ 7፥26
5ኛ- የሚያቀርበው ብቁ መሰዋዕት ያለው መሆን አለበት ዕብ 8፥3
6ኛ- የማይሞትና ዘላለማዊ መሆን አለበት ዕብ 7፥23-24

#ይህንን መጽሐፍ ቅዱስ መሰፈርት ይዘን ያማልዳሉ የተባሉትን መልአክትን፤ ጻድቃንና ሰማዕታትን ስንሰበስባቸው ይህን መሰፈርት ማሟላት የምችል አንድ እንኳ የለም፡፡
#ይህን መሰፈርት ማሟላት የምችለው አንድ ኢየሱስ ብቻ ነው
በአምላክነቱ ከአምላክ ጋር በሰውነቱ ከሰው ጋር መግባባት የምችል ብቸኛው አስታራቅ፤ አማላጅና መካከለኛ ኢየሱስ ብቻ ነው፡፡

ኢሳ 53÷12
!!
“ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”
— ኢሳይያስ 53፥12

..
“የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።” ሮሜ 8፥34

!!
#ማንም አስታራቅ ሆኖ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የመግባት አቅም ያለው ፍጥረት የለም አራት ነጥብ፡አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ኢየሱስ ብቻ ነው።

03/05/2025
03/05/2025

(ማጽናናትህ Live album) ጸጋው የራሱን ጽድቅ ላቆመ ደህና ነኝ ለሚለው ሰው፣ጸጋው ምኑ ነው?ምህረቱስ መች ገብቶት ሊያደንቀው፤ ልምምዱ ላስመሰካው ሥርዐት መፈጸሙ፣ጸጋው ምኑ ነው?ኃጢአቱስ መ....

03/05/2025

✅ አሳዛኝ ዜና 🙆‍♂️
የማይደፈረውን የደፈሩት ጀግናው አባታችን በስተመጨረሻም አመታትን ባስተማሩበት ተከብረው በኖሩበት በየትኛውም የተዋህዶ ደብር እንዳይገኙ ታገዱ🥲
#ወንጌላችን ግን አይታገድም የኢየሱስን አዳኝነት ቤዛነትና አማላጅነት ገና ለአለም እንሰብካለን🙌
አባታችንም ከእኛ ጋር አብረው ኢየሱስን ብቻ ይሰብካሉ #ተገላገሉ😎
ከአባታችን ጎን ነን

03/05/2025

አሜን በማለት ይፀልዮ፡-

1. አባት ሆይ ፣ በህይወቴ ውስጥ ስላደረግኸው የማያቋርጥ መገኘት እና ጣልቃ ገብነት አመሰግንሃለሁ።

2. ጌታ ሆይ እርዳታህን በምፈልግበት በህይወቴ ውስጥ ጣልቃ ግባ።

3. አባት ሆይ ከጠላት እቅድ ሁሉ ጠብቀኝ።

4. ጌታ ሆይ፣ የማይቻል በሚመስሉ ቦታዎች ላይ ስኬቶችን ስጠኝ።

5. አባት ሆይ፣ በመለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ኃይልህ በሕይወቴ ይገለጥ።

6. ጌታ ሆይ ጠላት የሰረቀኝን ሁሉ መልስልኝ።

7. አባት ሆይ ማንም የማይዘጋውን በሮች ክፈትልኝ።

8. ጌታ ሆይ፣ በጊዜው ጣልቃ ገብነትህ እምነቴን አጠናክር።

9. አባት ሆይ፣ አጥብቆ እንድጸልይ እና ያለማቋረጥ ፊትህን እንድፈልግ እርዳኝ።

10. አቤቱ ህይወቴ ለታላቅነትህ እና ለክብርህ ምስክር ትሁን።

ትንቢታዊ አዋጅ፡-

1. ከዛሬ ጀምሮ በሚያጋጥሙህ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እግዚአብሔር ጣልቃ ይገባል።

2. መለኮታዊ ጥበቃ ህይወትህን ከማንኛውም ጉዳት እና አደጋ ይጠብቃል ።

3. የተዘጋው በር ሁሉ በእግዚአብሔር ይከፈታል።

4. ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ለውጥ ለማምጣት እግዚአብሔር ወደ ሁኔታህ እየገባ ነው።

5. በመለኮታዊ ጣልቃገብነት በህይወትህ ውስጥ ያለው ማንኛውም ገደብ እየፈረሰ ነው።

6. እግዚአብሔር ከመከራም ሁሉ ያድንሃል።

7. መለኮታዊ ተሀድሶ ወደ እያንዳንዱ የጠፉ ወይም የተሰበረ የህይወት ቦታህ እየመጣ ነው።

8. እግዚአብሔር በህይወታችሁ ውስጥ ጣልቃ ይገባል ከዚህ በፊት ታይተው የማያውቁ ስኬቶችን ታገኛላችሁ።

9. የእግዚአብሔር ጣልቃገብነት ምስክርነትህ ሌሎች በእርሱ እንዲታመኑ ያነሳሳል።

10. የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት ኃይል በሕይወታችሁ ውስጥ ዘላቂ ሰላም እና ድልን ያመጣል።

ዘወትር እሁድ ጠዋት በአዲስ አበባ ትምህርቱ ይሰጣል።

በአለም ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ሰዎችን የማረከ በክርስቶስ ወንጌል የጠራ እንደ ፕሮቴስታንት አለ ብዬ አላስብም። ምሁራን ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣ገበሬዎች ፣ነጋዴዎች ፣ሴቶች ፣ ወንዶች .....
03/05/2025

በአለም ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ሰዎችን የማረከ በክርስቶስ ወንጌል የጠራ እንደ ፕሮቴስታንት አለ ብዬ አላስብም። ምሁራን ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣ገበሬዎች ፣ነጋዴዎች ፣ሴቶች ፣ ወንዶች ....ወደ እዚህ ተቋም በፍጥነት ወደ እዚህ ተቋም እየተቀላቀሉ ነው ። ምንም አይነት ችግር የለም ብዬ ባላስብም ግን ከማንም በተሻለ በመፅሐፍ ቅዱስ
መሰረት ላይ የቆመ ተቋም ነው ። ይህ እንዳለ ሆኖ በሰፊው ወደ ፊት ልንተነትነው የምንችል ቢሆንም ጴንጤነት ( ፕሮቴስታንት ) በአለም አቀፍ እና በሃገር አቀፍ ደረጃ የፈጠራቸውን ተፅዕኖ በተመሰነ መንገድ ወንድም Giruum Fidaa እንዲህ ፅፎታል (የተወሰኑ ጭማሪዎች እኔ አድርጌያለሁ )

ማሳሰቢያ ጴንጤነት እና ፕሮቴስታንት የተሳሰሩ ቢሆኑም በተወሰነ ደረጃ የትርጉም ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል ወይም በቀላሉ ጴንጤዎች ሁሉ ፕሮቴስታንት ናቸው ።ፕሮቴስታንት ውስጥ ግን ጴንጤ ያልሆኑ የተወሰኑ ጎራዎች አሉ ። ነገር ግን አጠራሩ በተለመደበት መንገድ እንቀጥላለን ።

👇
የፕሮቴስታንታዊነት ክርስትና በአለምአቀፍ ደረጃም ይሁን በአህጉራዊ ደረጃ ያስቀመጠው አመርቂ አሻራ አንድ አንዶች አቅልለው እንደሚናገሩት አይደለም። ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በአውሮፓ የተከሰተው የተሐድሶ እና የአብርሆት እንቅስቃሴዎች ናቸው ዛሬ ሳናውቅ የምንተነፍሰውን የአኗኗር ቀመር የተውልን። ይህ ዘመን ለመፅሐፍ ቅዱስ እውነት ለፍትህ ለመብት ለእውነት እና ለሰፊው ምስኪን ማሕበረሰብም መብት መከበር ካቶሊክን ተቃውመው በብዙ ስቃይ እና መከራ ውስጥ ፀንተው የቆሙ አባቶች የተነሱበት ዘመን ነው ። ብዙዎች በእሳት የተቃጠሉ ለእስር የተዳረጉ የሞቱ እንዳሉ ልብ ይሏል ።

የኢንደስትሪው አብዮት ፣ የሰዎች መብት መከበር ፣ የስነምግባር ፍልስፍናዎች፣ ጸረ ባርያ ንግድ ፣ እኩልነት ፣የሥራ ባዕል ፣ በጎ አድራጎት፣ ወዘተ. የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ ትሩፋን ናቸው። ለአብነት ያክል የሳይንቲስቶች እና የቴክኖሎጂ ሰዎችን ስም እየዘረዘርኩ ከማደክማችሁ፤ በአለማችን ላይ አሉ የሚባሉት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ኦክስፎርድን እና ሀርቫርድን ብቻ ብንመለከት የፕሮቴስታንት የነገረ መለኮት መማርያ ስፍራዎች ነበሩ።

እነ ቶም ሆላንድ እንዳሉት አለም የራሱ እየመሠለው እየተነፈሰው ያለው አየር የዚህ የክርስትና ስጦታ ነው። መሠረቱም የክርስቶስ ትምህርት ነው። ሌሎች የክርስትና ቅርንጫፎች የዚህ ገጸ በረከት አካል አይደሉም እያልኩ ሳይሆን ከፕሮቴስታንት ውለታ ጋር ትከሻ ለትከሻ የሚቆም የለም ማለቴ ነው።

አንድ አንዴ ፕሮቴስታንት መሆን እንደ መጤነት እና እንደ አላዋቂነት ይታያል። በተለይ በሃገራችን ለማሸማቀቅ ይህን ቃል ይጠቀማሉ ።እውነታው ግን አለም ምተነፍሰው ከዚህ እንቅስቃሴ የተነሳ ነው። እነደውም ወደ ነገረ መለኮቱ ስንመጣ ሌላውን ትታችሁት ፕሮቴስታንቶች አያውቁም በሚባሉት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና ነገረ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሌሎቹንም አብያተ ክርስቲያናት ጨምሮ የምንጠቀማቸውን መጻሕፍት የተረጎሙለን፤ ምንጭ አድርገን የምንጠቀመው

የጆአኪም ጄሬማያን ፣ የነ ፈርጉሰንን የነ ላይትፉትን የነ ዋርፊልድን የነ ፍሊፕ ሻፍን ስራዎች እኮ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የተረጎሙልን ሳይቀር እነ ቲንዴል ፣ ዊክሊፍ ፣ ኪንግ ጀምስ ፣ ኤራስመስ ወዘተ ናቸው። ታዲያ የነሱ ስራ ላይ ቆመው ሳያስተውሉት ሲቀር ያሳዝናል።

በአገራችን ኢትዮጵያ እንኳን በግብርናው መስክ አቮካዶ፣ አፕልን ጨምሮ ብዙ አትክልቶች እና ፍራፍሬዎች ፣በትምህርቱ መስክ ሜጋ ማተመያን ጨምሮ ብዙ ሕትመት ቤቶች ፣ ቤተ መጻሕፍት እና አስቋላ /ት/ት ቤቶች በንጉሱ ዘመን በፕሮቴስታንት ሚሲዮናውያን የተከ

የኤማሁስ መንገደኛ የሆንን ማነን ? ከኢየሱስ ሞት በኋላ ደቀመዛሙርቱ እና ሌሎች ተከታዮቹ ተስፋ ቆርጠው በብዙ ኃዘን ውስጥ ነበሩ።   የኤማሁስ መንገደኞችም ከኢየሩሳሌም ወደ ኤማሁስ መንደር ...
21/04/2025

የኤማሁስ መንገደኛ የሆንን ማነን ?
ከኢየሱስ ሞት በኋላ ደቀመዛሙርቱ እና ሌሎች ተከታዮቹ ተስፋ ቆርጠው በብዙ ኃዘን ውስጥ ነበሩ። የኤማሁስ መንገደኞችም ከኢየሩሳሌም ወደ ኤማሁስ መንደር እየጠወለጉ ይጓዙ ነበር።

ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ በመንገድ ከእነሱ ጋር ቀርቦ ይጓዝ ነበር እነርሱ ግን አላወቁትም አይናቸውም ተይዞ ነበር።

ብዙ ከተጓዙ በኋላ ቀኑ መሽቷል ከእኛ ጋር እደር ብለውት ከእነርሱ ጋር ሊያድር ገብቶ ማዕዱንም ባርኮ ከቆረሰ በኋላ ነበር አይናቸው ተከፍቶ እርሱ መሆኑን የተረዱት።

#መልዕክት
ታዲያ ይህ ንጉስ ማን እንደሆነ በማወቅ እና ምን እንዳደረገለን በመረዳት አይኖቻችን ተከፍተዋልን ?
ሁሌም ከእኛ ጋር እንዳለና የሚያስብልን እንደሆነ እናስተውላለን ?
ከእርሱ ጋር ህብረት አለን ምላሹ ለራሳችን ይሁን !

#ሉቃስ 24 31-32
ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።
እርስ በርሳቸውም። በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን? ተባባሉ።
Ephesons Christian Media Network-ECMN

29/11/2024
29/11/2024

ፕሬዘደንት ትራምፕ አሜሪካ አዘቅት ዉስጥ ገብታለች የሚታደጋት አዳኝ ያስፈልጋታል ያም አዳኝ እኔ አይደለሁም ከኔ እጅግ በጣም ከፍ ያለ ነዉ እሱም “ጌታ ኢየሱስ”ነዉ ብለዉ ሲናገሩ ከዚቀደም ግብፅ ግድቡን ልታፈርስ ትችላለች ሲሉ ይዉረዱ ብዬ በፀለይኩበት አፌ በምንተፍረቴ ባስቸኳይ ወደስልጣን ይመለሱ ብዬ ወጥሬ ፀለይኩ አይ የሰዉ ነገር😂😂
በጣም ደስብሎኛል ስለተመለሱ።በተመሳሳይ ፆታ ጋብቻና ፆታን በማስቀየር ላይ ያላቸዉ ደንዳና አቋም በተለይ የአሜሪካ ህፃናትን የሚታደግ በመሆኑ አጥብቀን ልንፀልይላቸዉ ይገባል።እግዚአብሔር ቀሪ ዘመናቸዉን ይባርክ!

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ephesons Christ Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share