Astuecsf Official

Astuecsf Official ""በመታደስ ወደ ክርስቶስ የማደግን ህይወት መለማመድ""

This is Adama Sciences and Technology University Evangelical Christian Students fellowship official page

‎ኋላ ግራ ገብቶኝ ፈዛዛ እንዳልባል‎የምድሩ ሀሳብ ከልቤ እንዲገባ ጥቂት ጠጋ ብትል‎ትንሽ ጥሬ ግሬ እውቀት እስካካብት‎ምናል ተራርቀን ብንቆይ ይቺን ሳምንት‎ብዬ ....ላንተ ያለኝን ትኩረት ...
29/05/2026

‎ኋላ ግራ ገብቶኝ ፈዛዛ እንዳልባል
‎የምድሩ ሀሳብ ከልቤ እንዲገባ ጥቂት ጠጋ ብትል
‎ትንሽ ጥሬ ግሬ እውቀት እስካካብት
‎ምናል ተራርቀን ብንቆይ ይቺን ሳምንት
‎ብዬ ....ላንተ ያለኝን ትኩረት ቀነስ አላረግም
‎የሚመጣው ሁሉ የሚያልፍ ነውና ከቶ አላስነካህም

እያንዳንዱ እርምጃችን ብዙ ሰዎችን አስተዋውቆናል። ነገር ግን ሁሉም ትውውቅ መልካም ፍፃሜ ይኖረዋል ማለት አይደለም። እውነተኛ ጓደኝነት ከምቾት ጊዜ ያለፈ እንደሆነ መፅሐፍ ቅዱስ ያሳስበናል።...
27/05/2026

እያንዳንዱ እርምጃችን ብዙ ሰዎችን አስተዋውቆናል። ነገር ግን ሁሉም ትውውቅ መልካም ፍፃሜ ይኖረዋል ማለት አይደለም። እውነተኛ ጓደኝነት ከምቾት ጊዜ ያለፈ እንደሆነ መፅሐፍ ቅዱስ ያሳስበናል።

“ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳል፤”
ምሳሌ 17፥17

እውነተኛ ጓደኛ በደስታ እና ተድላ ብቻም ሳይሆን በጭንቀት እና እርግጠኝነትን በማጣት፤ በሀዘን እና ጨለማም ባልነው ጊዜያችን አብሮን ይቆያል። እንድናድግ፣ እንድንለወጥ እንዲሁም መልካም ማንነትን እንድንላበስ በመልካም ይቀርፀናል።

“ብረት ብረትን ይስለዋል፥ ሰውም ባልንጀራውን ይስላል።”
ምሳሌ 27፥17

እግዚአብሔራዊ ጓደኝነት ስለፍፅምና ሳይሆን በልበ-ቀናነት እና በታማኝነት አብሮ ስለመጓዝ፣ ድካምን ስለማበርታት እና የወደቀውን ስለማንሳት፣ የተንጋደደውን ደግሞ ስለማቃናት ነው።

ድካማቸው መልካም ዋጋ አለውና አንድ ብቻ ከመሆን ሁለት መሆን ይሻላል።ቢወድቁ አንዱ ሁለተኛውን ያነሣዋልና፤ አንዱ ብቻውን ሆኖ በወደቀ ጊዜ ግን የሚያነሣው ሁለተኛ የለውምና ወዮለት።
መክብብ 4:9-10

ስለሆነም ግንኙነቶቻችን ወደ እውነት እና እድገት ከምንም በላይ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር የሚያስጠጉን እንዲሆኑ ወዳጆቻችንን በጥንቃቄ እንምረጥ።

ልክ በዕለቱ...መክብብ 3÷11 " ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው..."የልባችን መሻት እውን እንዲሆን በመጠባበቅ ላይ ነን? ፣ እግዚአብሔር በቃሉ ለተናገረን በረከቶች ፣ ለዘመናት በ...
11/05/2026

ልክ በዕለቱ...

መክብብ 3÷11
" ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው..."

የልባችን መሻት እውን እንዲሆን በመጠባበቅ ላይ ነን? ፣ እግዚአብሔር በቃሉ ለተናገረን በረከቶች ፣ ለዘመናት በፊቱ ሳንሰለች ላቀረብናቸው ጥያቄዎች ፣ ለእያንዳንዱም መልስ ለሚሹ ጉዳዮቻችን እግዚአብሔር ላይ ያለን እምነት ምን ያህል ነው?
    ሕይወታችን የተሳፈረችው በእግዚአብሔር ላይ ነው። ሳያረፍድ ማንን፣ እንዴት ፣ መቼ  እና የት ማድረስ እንዳለበት እርሱ ራሱ ያውቃል ። በራሳችን የችኮላ ሩጫ እግዚአብሔርን ከጊዜ ሰሌዳው ማፍጠንም ሆነ ማዘግየት አንችልም ። እግዚአብሔር በጊዜው ውስጥ መጠበቅን ፤ በመጠበቅ ውስጥ ትዕግስትን ፤ በትዕግስት ውስጥ ደግሞ ፅናትን ከዚህ ሁሉ ደግሞ የሚበልጠውን እምነታችንን በእኛ ውስጥ ማየት ይፈልጋል። ስለዚህ ጊዜው ሲደርስ የምንቀበለውን መልስ እነዚህን አጉድለን መተላለፍ  እንዳይሆንብን እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛልን::
እግዚአብሔር አምላክ ለኛ ያለውን መልካም ሃሳብ እና እቅድ በራሱ ጊዜ የሚያከናውን ኤልሻዳይ አምላክ ስለሆነ የእርሱን የተወደደች ሰዓት ታግሰን እንጠብቅ :: እግዚአብሔር ነገሮችን በትክክለኛው ጊዜ ማድረግን ጠንቅቆ ያውቅበታልና ::
  በእግዚአብሔር ላይ መታመን ለሕይወት ነው ፤ በእግዚአብሔር መደገፍ ማረፍ ነው ፤ በእግዚአብሔር ፊት ነገርን መጣልም ማትረፍ ነው ። ስለዚህ ነገራችንን በራሳችን ጥረት እና እውቀት ለማስተካከል ከመዳከር እና ከመዛል ይልቅ እምነታችንን በእግዚአብሔር ላይ ለመጣል እንሞክር :: እግዚአብሔር የጣልንለትን ጉዳይ ልክ በዕለቱ አንስቶ ለክብሩም እንደሚሆን  በጊዜውም ውብ አድርጎ ይመልስልናል ።
የኛ ድርሻ በፀሎት እየፀኑ እግዚአብሔርን በመጠበቅ ውስጥ ሊያወርሰን ያሰበው የበረከት ሕይወት ላይ ተስፋ ማድረግ እንጂ መቼ ይሆን የሚሆነው እያልን በሃሳብ መውጠንጠን አይደለም::

ፀሎት : ".. እግዚአብሔር ሆይ የአንተን ትክክለኛ ጊዜ መጠበቅ አድካሚ ቢሆንም በአንተ ላይ እንድታመን አንተ ለእኔ ያለህን እቅድ እያሰብኩም በሀሳብህ ማረፍ እንድችል እርዳኝ..... አሜን""

ውጣ ውረድ ቢበዛ እንኳን ቢጨንቀኝም ማደርገዉ አንተን ትቼ ሌላ አማራጭ መፈለግ አይሆንልኝም ውላችን አይደለም ስኬት ሳይሆንልኝ ግን ልርቅህ በደምህ የተዋጀሁት በቂዬ ነው ማንነትህ        ...
29/04/2026

ውጣ ውረድ ቢበዛ እንኳን ቢጨንቀኝም ማደርገዉ
አንተን ትቼ ሌላ አማራጭ መፈለግ አይሆንልኝም
ውላችን አይደለም ስኬት ሳይሆንልኝ ግን ልርቅህ
በደምህ የተዋጀሁት በቂዬ ነው ማንነትህ

Hana Telke

"በተጋረደው  ጓዳ....."    ከውጭ ለሚያይ  እውነትን  ደብቆ እውነትን መፈለግ ይመስላል፤ በጓዳ አስቀምጦ በአደባባይ የመፈለግን ያህል።በበደላችን  ሙታን እና የቁጣ ልጆች ለነበርን ለእኛ...
27/04/2026

"በተጋረደው  ጓዳ....."

ከውጭ ለሚያይ  እውነትን  ደብቆ እውነትን መፈለግ ይመስላል፤ በጓዳ አስቀምጦ በአደባባይ የመፈለግን ያህል።በበደላችን  ሙታን እና የቁጣ ልጆች ለነበርን ለእኛ ትልቁ የእግዚአብሔር  ፍቅር እና ምህረት በመስቀል መድረክ ተገለጠልን::ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ ከአብ ጋር አስታረቀን። የኪዳኑ ቤተሰብ አደረጎንም በቅዱሳን ወንድሞች ህብረት መካከል ካለው በረከት ተካፋዮች አደረገን: : 
    ይህን ምህረት የተቀበለም አሮጌውን ሰው አስወግዶ አዲሱን ሰው በመልበስ መስቀሉን ተሸክሞ ዕለት ዕለት ይከተላል። በወንድሞች ህብረትም ይህን ፍቅር እና ምህረት ለማወቅ በዚያም ለመኖር ይበረታል።
መፅሐፍ ቅዱሳችን ህብረት መልካም እንደሆነ ይነግረናል ::ግን መልስ የሚያሻው ጥያቄ አለ። እኛ እና እግዚአብሔር እንዴት ነን?  በተጋረደው  ጓዳችንስ ይህን ፍቅር ለማወቅ ብርቱ ነን? ቆም ብለን ይህን ጥያቄ መመለስ ተገቢ ነው።
     የእግዚአብሔር  ቃል ተንኮል የሌለበትን የቃሉን ወተት እንድንመኝ፣ ዕለት ዕለት በውስጣችን ያለው እሳት አንዳይጠፋ በፀሎት እንድንተጋ፣ ከፈሪሳዊያን እርሾም እንድንጠበቅ ያሳስበናል:: ዛሬን ቆም እንበል!! ሩጫችንን ገታ አድርገን እናስተውል!! በጓዳችን እንታጠቅ!! ያን ጊዜ ትጥቃችን አይላላምና :: ለእርሱ መኖር እንድንችል እና እርሱን እንዳንበድል ቃሉን በልባችን እንሸሽግ::በግል እግዚአብሔርን ካላወቅን እውነትን በእጃችን ይዘን እውነትን በአደባባይ የምንፈልግ  ምስኪን ሰውን እንመስላለን!!

መዝሙር 105

³ በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።
⁴ እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።"


ሰውነት ውስጥ ያለየተስፋ ውጣ ውረድ፣ፈተና በሚሉት ግዙፍ ጉም ቢጋረድ፥ከምንም ተነስቶ ፥ ብዙ ምናምኖችመፍጠርን ለቻለ፣ፅናት ያፈገገው ብሩህ ሰማይ አለ!
25/04/2026

ሰውነት ውስጥ ያለ
የተስፋ ውጣ ውረድ፣
ፈተና በሚሉት
ግዙፍ ጉም ቢጋረድ፥
ከምንም ተነስቶ ፥ ብዙ ምናምኖች
መፍጠርን ለቻለ፣
ፅናት ያፈገገው
ብሩህ ሰማይ አለ!

ሀጥያት...ከጠላት አጣምሮ ከአምላክ ለያይቶሀጥያት...ከግኡዝ አጋጭቶ ከሰውም አጣልቶቢመቻች ቢኖር ምቹ ቤቱን ሰርቶማን ይሆን የሚያርፍ በሰላም ተኝቶ!
17/04/2026

ሀጥያት...ከጠላት አጣምሮ ከአምላክ ለያይቶ
ሀጥያት...ከግኡዝ አጋጭቶ ከሰውም አጣልቶ
ቢመቻች ቢኖር ምቹ ቤቱን ሰርቶ
ማን ይሆን የሚያርፍ በሰላም ተኝቶ!

በጸጋው እንንገስባት..መጽሐፍ ቅዱስ ሐጢአትን ከገለጸባቸው ባህሪያት መካከል "በደጅ ማድባት" ወይም "ቶሎ መክበብ" አንዱ ነው። ይህም በሥጋ ለባሹ ላይ ከዚህች በሐጢአት ከተከበበች ዓለም የሚ...
13/04/2026

በጸጋው እንንገስባት..

መጽሐፍ ቅዱስ ሐጢአትን ከገለጸባቸው ባህሪያት መካከል "በደጅ ማድባት" ወይም "ቶሎ መክበብ" አንዱ ነው። ይህም በሥጋ ለባሹ ላይ ከዚህች በሐጢአት ከተከበበች ዓለም የሚደርስበት ዋነኛው ፈተና ነው። ተሸንፎና ከሃሳቡ አውርዶ ሐጢአት ዉስጥ እንዲገባ ወይም ሃሳቡን በማሸነፍ ከሐጢአት መንደር እንዲሸሽ።

በአንድ ወቅት ቃኤል መስዋዕቱ በእግዚአብሄር ፊት ሞገስን ባላገኘና የወንድሙ የአቤል መስዋእት ተሽሎ በተገኘ ጊዜ ወንድሙን የመግደል ሐጢአት በዙሪያው ታደባ ነበር። ይህንም እግዚአብሄር እራሱ ለቃኤል ሲያሳውቀው በመጽሃፍ ቅዱስ እንመለከታለን። በዚያን ጊዜም እግዚአብሄር ለቃኤል የሰጠው መመሪያ አንድ ነበር። እንዲነግስባት !! እሷ ወዳሰበችው መንገድ ከመመራት ይልቅ እሷን አሸንፎ ከራሱ እንዲያባርር። በስተመጨረሻ ግን ቃኤል እግዚአብሄር ከጠቆመው መፍትሔ ስቶ በሕይወት ዘመኑ እርግማን ወዳ'ተረፈበት እርምጃ ሲጓዝ እናያለን ።

ዛሬም በአዲስ ኪዳን ዘመን የሐጢአት ባህሪይዋ ያው ፣ የእግዚአብሄር የመፍትሔ አማራጭም ተመሳሳይ ነው። እንደ አንድ ስጋ ለባሽና በዚህች ዓለም እንዳለ ሰው ራሳችንን ካጋለጥንበት ሁኔታና አከባቢ መነሻነት ሐጢአት በእኛ መስተናገድን ፈልጋ በደጃችን ስታደባ ወይም ዙሪያችንን ቶሎ ስትከበን እናገኛት ይሆናል። ወይ ልትነግስብን አሊያም ደግሞ እንድንነግስባት ። በዚህ  ጊዜ በአዲስ ኪዳንም ከእግዚአብሄር የተሰጠን የመፍትሄ አማርጭና መመሪያ ተመሳሳይ ነው። ነገር ግን ከብሉይ ኪዳኑ መመሪያ በተለየ በአዲስ ኪዳን ለመንገስ የምንዋጋው ለብቻችንን ሳይሆን እንድንነግስ ሊያደርገን በሚችል ከእግዚአብሄር ጸጋ ጋር ነው። ስለዚህ በማንኛውም አጋጣሚና ሁኔታ ሐጢአት በደጃችን ስታደባ ወይ ቶሎ ስትከበን የእግዚአብሄር ፈቃድ በእርሱ ጸጋ አማካኝነት በሃጢአት ላይ ነግሰን ከእኛ እንድናርቃት ነው። በጸጋው እንንገስባት !!

“እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”
  — ዕብራውያን 12፥1-2




INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዐል በሰላም አደረሳችሁ።🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉እንደሚታወቀው የተሰቀለው ማነው በሚል ርዕሰ ዲጂታል ሚሽን ላለፉት 15 ቀናት ስ...
12/04/2026

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዐል በሰላም አደረሳችሁ።

🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉

እንደሚታወቀው የተሰቀለው ማነው በሚል ርዕሰ ዲጂታል ሚሽን ላለፉት 15 ቀናት ስንሰራ ነበር እናም ይህ ሀሳባችን ዛሬ ማሳረጊያውን ያገኛል፤ይህም ማሳረጊያ የተሰቀለው ጌታችን ተሰቅሎ አና ሞቶ አልቀረም የተሰቀለው ጌታችን ከሞት ተነስቷል።
----------------------------------------

የተሰቀለው ተነስቷል።

1 ቆሮ 15:3-4
'....ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈውም በሦስተኛው ቀን ተነሣ'
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ለክርስትና እምነት እጅግ ማዕከል (ልብ) ነው፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማዳን ኃይል የተገለጠበት በመሆኑ ነው። እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሙታን በማስነሳት በሕይወትና በሞት ላይ ያለውን ፍጹም ሉዓላዊነት አሳይቷል፤ ይህም ኃጢአትን ለማሸነፍ፣ ሞትን ድል ለማድረግ እና የዘላለም ሕይወትን ለመስጠት እርሱ ብቻ ሥልጣን እንዳለው ያረጋግጣል።

ትንሣኤው ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የተስፋው መሲሕ እና የዓለም አዳኝ ነኝ በማለት የተናገረውን ቃል ያረጋግጣል፤ ይህም የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን እና እርሱ ራሱ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ ብሎ የተናገረውን ትንቢት ያጸናል። ይህም የእርሱን ከኃጢአት የጸዳና መለኮታዊ ባሕርይ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ስለ ሰው ልጅ ኃጢአት ያቀረበው መስዋዕትነት በእግዚአብሔር ዘንድ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት ማግኘቱን ያሳያል፤ እንዲሁም ለሚያምኑት ሁሉ ይቅርታንና መዳንን ያረጋግጣል።

ኢየሱስ “ትንሣኤና ሕይወት” በመሆኑ፣ የእርሱ ድል የአማኙ ድል ይሆናል—ይህም ፍርሃትን ወደ ተስፋ፣ መከራን ወደ ዓላማ፣ ሞትንም ወደ ዘላለም ሕይወት ይለውጣል። ለሚነሱት ሁሉ “በኩራት” (መጀመሪያ) እንደመሆኑ መጠን፣ ክርስቶስ ለክርስቲያኖች መቃብር መጨረሻ እንዳልሆነ ያረጋግጥላቸዋል፤ እርሱ ከሞት እንደተነሳ አማኞች ከሞቱ በኋላ የማይበሰብሰውን ስጋ ለብሰው ይነሳሉ ፤ይህም አሁን በእምነታቸው ፀንተው እንዲኖሩ ብርታትን ይሰጣል፣ ድካማቸውም ሆነ እምነታቸውና ተስፋቸው ከቶ ከንቱ እንዳልሆነ እምነትን ያሳድራል።




DS

INSTAGRAM | YOUTUBE | TIKTOK

📌  ትንሣኤ እና ሕይወት ነው።ዮሐ 11:25"ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤"በመስቀል በኩል የተገለጠው የመጨረሻው አስደሳች ተስፋ ከክርስቶስ ...
10/04/2026

📌  ትንሣኤ እና ሕይወት ነው።

ዮሐ 11:25
"ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤"
በመስቀል በኩል የተገለጠው የመጨረሻው አስደሳች ተስፋ ከክርስቶስ ጋር የሚኖረው የዘላለም ሕይወት ነው። ኢየሱስ በእሱ ብቻ የሚያምኑትን ከሚመጣው ፍርድ ሊያድንና ከሞት በኋላ ከእርሱ ጋር የዘላለም ኅብረት እንዲያገኙ ለማድረግ ሞተ። ከሞት በመነሳትም፣ ሞት ከዚህ በኋላ ሀይል እንደሌለው፣ እንዲሁም በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንደሚሰጥ አረጋግጧል። ስለዚህ ማንም በክርስቶስ አምኖ የሞተ የትንሣኤና የዘላለም ክብርን ተስፋ ይጋራል።

ፋሲካ የአንድ ወቅት ክስተት ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር የድነት ዕቅድ ሙላትና ይህንን አሸናፊ ተስፋ የያዘ ነው፡፡ መስቀል ወደ ትንሣኤ ትንሣኤም ከአዳኙ ጋር ወደሚሆን የዘላለም ኅብረት ይመራናል።

በመጨረሻም ስቅለት ኢየሱስ ስለሞተና ድል አድርጎ ስለተነሳ አማኞች አንድ ቀን ከእርሱ ጋር በደስታ፣ በሰላምና በማያልቅ ክብር ለዘላለም እንደሚኖሩ የተረጋገጠላቸውን የተስፋ ኪዳን የያዘ የክርስትና መሰረት ነው።
ቀን 12




Address

Adama

Telephone

+251928205050

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Astuecsf Official posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Astuecsf Official:

Share