04/06/2018
አስደናቂ የጸሎት ጥቅሞች
ሳታቋርጡ ጸልዩ፤
(1ኛ ተሰሎንቄ 5:17)
የጸሎትን ጥቅምና ከፍ ያሉ ዓላማዎቹን ስትረዱ፣ ሁልጊዜም ለመጸለይ በተለይም በልሳን ለመጸለይ ፈቃደኛና ደስተኛ ትሆናላችሁ። እንደ እግዚአብሔር ልጆች መንፈስ ቅዱስ በህይወታችን ካደረገልን ነገሮች መካከል አንዱ፣ በልሳን የመናገር ችሎታ ነው። በልሳን ስንናገር የምናወጣቸውና የምንናገራቸው ቃላት በሰው የተፈጠሩ ሳይሆኑ ከጌታ ናቸው።
በተጨማሪም የምንናገረው ለሰው ሳይሆን ለእግዚአብሔር ነው፡- “በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤” (1ኛ ቆሮ 14:2)፡፡ በልሳን ስትጸልዩ ከአብ ጋር ህብረት እያደረጋችሁ ነው። በሰማያዊ ቋንቋ ከእግዚአብሄር ጋር በመንፈስ ጋር እየተነጋገራችሁ ነው፣ ይሄ እንዴት ድንቅ በረከት ነው!
ከዚህም በተጨማሪ በልሳን መጸለይ በመንፈሳችሁ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን ሀይል ለማንቀሳቀስ ይረዳል። ምንም እንኳን ያ ሀይል መንፈስ ቅዱስን ወደ ህይወታችሁ በተቀበላችሁ ጊዜ ወደ እናንተ የመጣ ቢሆንም (ሐዋርያት ሥራ 1፡8) ሁልጊዜም ልታነቃቁትና ለእግዚአብሔር ክብር ልትጠቀሙበት ይገባል።
በልሳን መጸለይ ሁልጊዜም የበለጠ መንፈሳዊ ብቃት እንዲኖራችሁ ያደርጋል፣ ለመንፈስ ቅዱስ ምሪት፣ የተቃኛችሁና ምላሽ የምትሰጡ ያደርጋችኋል። በመንፈስ ቅዱስ በመጸለይ ከጌታ ጋር ህብረት ለማድረግ የበለጠ ጊዜ ባሳለፋችሁ ቁጥር፣ የእርሱ ባህሪይና ስብእና በይበልጥ በእናንተ ውስጥና በእናንተ በኩል ይገለጣል።
አንዳንድ ሰዎች ለመጸለይ የሚገደዱት በህይወት አስቸጋሪ ሁኔታ ሲገጥማቸው ብቻ ነው፣ ይሄ ደግሞ ትክክል አይደለም። በሰማይ ካለው አባታችን ጋር ህብረት እንድናደርግ ተጠርተናል፣ የጸሎትና የመጸለይ ዋነኛው ዓላማ ህብረት ለማድረግ ነው።
በግልና በጋራ ለሚኖራችሁ የጸሎት ጊዜ ትኩረት ስጡ። በጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ልታደርጉ የምትችሉባቸውን አጋጣሚዎች ፍጠሩ፤ ህይወታችሁም ከክብር ወደ ክብር እያደገ ይመጣል።