14/09/2026
🔔 የመስከረም (ብዙኀን) ማርያም ክብረ_በዓል ጥሪ
በጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ለምትገኙ ምእመናን እና ምእመናት ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ በመጀመሪያ እንኳን ለአዲሱ ዘመን 2019 ዓ.ም እና ለበዓለ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ እያልን የመስከረም ማርያምን በዓለ ንግሥ በደብራችን ፍራንክፈርት ጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀትና ሥነ ሥርዓት ለማክበር የአጥቢያው ሰበካ ጉባኤ ኑ አብረን እናክብር በማለት መንፈሳዊ ጥሪውን ያቀርባል።
በበዓሉ ላይም ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ፣ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንት ፣ ካህናት፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ በዛ ያሉ ምዕመናንና ምዕመናት ይገኛሉ።
🗓
ዓርብ እና ቀዳሚት መስከረም ፳፪ እና ፳፫ ቀን 2019
Freitag & Samstag, October 2 & 3 2026
በደመቀ ሁኔታ ይከበራል፡፡
⏰
መርሐ ግብር
• በዋዜማው ዓርብ ከ16:00 ሠዓት ጀምሮ ዋዜማ ይቆማል
• ዓርብ ከምሽቱ 23:00 - 05:30 ሠዓት ሥርዓተ ማኅሌት
• ቅዳሜ ከጠዋቱ 05:30 - 09:00 በጸሎተ ኪዳን እና በሥርዓተ ቅዳሴ አገልግሎቱ ከተከናወነ በኋላ
በስብከተ ወንጌል ፣ በመዝሙር እና የተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከብሮ፤
ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ዑደት ይደረግና
በብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ ሊቀ ጳጳስ
ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ የበዓሉ ፍጻሜ ይሆናል።
🚩
በዓሉ የሚከበርበት አድራሻ ፤
Matthäuskirche
Friedrich-Ebert-Anlage 33,
60327 Frankfurt am Main
ወደ ቦታው ለመምጣት ከውናው ባቡር ጣቢያ Hauptbahnhof straßebahn 16 &17 በመያዝ ወደ Festhalle/Messe እቅጣጫ 2 Station ወይም ከ Hauptbahnhof በእግር ከ3-5 ደቂቃ ሄደው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኙታል