Ethiopian Catholic Community in Germany /Äthiopische katholische Gemeinde/

Ethiopian Catholic Community in Germany /Äthiopische katholische Gemeinde/ Die äthiopische katholische Gemeinde in Deutschland ist die erste bekannte äthiopische katholische Bewegung in Deutschland.

Als von Gott berufenen Volk versammeln wir uns, um Gott zu preisen.

2019 አዲስ ዓመት ዝግጅታችን በፍራንክፈርት በድምቀት ተከበረ! በ13.09.2026 የተካሄደው የአዲስ ዓመት ዝግጅታችን፣ ከቅርብም ከሩቅም፣ በተለይም ከባቫሪያ የመጡ በርካታ አባላት በተገኙበ...
15/09/2026

2019 አዲስ ዓመት ዝግጅታችን በፍራንክፈርት በድምቀት ተከበረ!
በ13.09.2026 የተካሄደው የአዲስ ዓመት ዝግጅታችን፣ ከቅርብም ከሩቅም፣ በተለይም ከባቫሪያ የመጡ በርካታ አባላት በተገኙበት በታላቅ ደስታና ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
ክቡር አባ ግርማቸው ከእህታችን ሊዲያ የተበረከተውን የመዘምራን ልብስ በመባረክ አስጀምረው፣ የአዲስ ዓመት ቡራኬ ፀበል ከረጩን በኋላ መሰዋዕተ ቅዳሴውን መርተዋል።
በአዳራሽ ውስጥ እህቶቻችን “አበባየሁ ሆይ ለምለም” በማዜም የቆየውን ውድ ባህላችንን እንድናስታውስና እንድንወያይበት አድርገውናል። በማዜም ያገኙትን ገንዘብ ለማህበራች ህፃን አባላት አገልግሎት እንዲውል ለግሠውታል።
ከዚያም የምሳና የቡና ጊዜ ከተለያዩ አዝናኝ ጨዋታዎች ጋር በደስታ አሳልፈናል። በመጨረሻም አባ ግርማቸው በመዝጊያ ፀሎት የዕለቱን መርሃ ግብር አሳርገዋል።
ይህ የአብሮነት፣ የፍቅርና የደስታ ቀን በሁላችንም ልብ ውስጥ የማይረሳ ትዝታን ጥሎ አልፋል።
አዲሱ ዓመት የፍቅር፣ የሰላም፣ የጤናና የበረከት ዓመት ይሁንልን!

ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክትበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።"ጌታን አመስግኑ ቸር ነውና" (...
10/09/2026

ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
"ጌታን አመስግኑ ቸር ነውና" (መዝ 136፤1)
በክርስቶስ የተወደዳችሁ ብፁዓን ጳጳሳት
ክቡራን ካህናት
ገዳማውያንና ገዳማውያት
መላው ምዕመናንና ምዕመናት
እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ከአገራችሁ ውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውናና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ በጎ ፍቃድ ያላችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች በሙሉ
እንኳን ለ2019 ዓመተ ምህረት የዘመን መለወጫ በዓል አደረሳችሁ!
እንኳን ከዘመነ ቅዱስ ማርቆስ ወደ ዘመነ ቅዱስ ሉቃስ በሰላም አሸጋገራችሁ::
የዘመናት ባለቤት እግዚአብሔር እነሆ ከዘመን ወደ ዘመን አሸጋገረን፤ አዲስ ዓመት መጣልን፤ ክብርና ምስጋና ለእርሱ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ይሁን! ዳዊት በመዝሙሩ እንደሚለን የሰማይን አምላክ ልናመሰግን ያስፈልጋል (136፤26 )።
ያለፈውን ስናስብ የምናመሰግንባቸው ወቅቶች እነሆ ብዙ ናቸው። በመሆኑም በግልም ሆነ በጋራ በቤተሰብም ውስጥ ሆነ በማኅበረሰብ ለተከናወኑ ቁም ነገሮች ምስጋናን እናቅርብ።
ማመስገን አመስጋኙን ያሳድገዋል። ማመስገን ትሕትናን ገልጾ በረከትን ያመጣል። ቅዱስ ጳውሎስ "ሁሉንም ከአምላክ ተቀብለህ ለምን ምንም እንዳልተቀበልክ ትሆናለህ?" (1ኛ ቆሮ 4፤7) የሚል ቃል ያቀርባል። በእርግጥም ምስጋናና ውዳሴን መርሳት በ2018 ዓ/ም ውስጥ የተቀበልነውንና የተደረገልንን ችላ ማለት ነው። ራሳችንን ስንመረምር ንሰሐ የምንገባባቸውም ጊዜያት አያሌ ናቸው። ከአምላካችንም ጋር ሆነ ከወንድም እህቶቻችን ጋር ግንኙነታችን እንዴት ነበረ? ባልንጀራችንንም እንደ ራሳችን ያልወደድንበት ወቅቶች ብዙ አልነበሩምን? እግዚአብሔርን በፍፁም ልባችን፤ በፍፁም ኃይላችን፤ በፍፁም ነፍሳችን ያልወደድንባቸው ወቅቶችስ አልነበሩምን? ይህንንስ ትዕዛዝ ሁልጊዜ ፈጽሜያለሁ በማለት ደፍሮ መናገር የሚችልስ ማነው?
ይህንን ለማለት እንደማንችል ማስተዋል ከፈለግን የቅዱሳንና የጻድቃንን ንግግር መስማት ይበቃናል። ቅዱሳንና ጻድቃን ትላልቅ ኃጢአተኞች እንደሆኑ በድፍረት ይናገራሉ። ምክንያቱም ምናልባት ለብዙዎቻችን የማይታየው ይታያቸዋልና ነው። በጣም ንፁህ በሆነ ቤት ውስጥ ብጣሽ ወረቀት ወይንም ትንሽ ቆሻሻ እንደሚታየው ማለት ነው። ቅዱሳን እና ጻድቃን አዘውትረው "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ካሉ እኛም የበለጠ "ጌታ ሆይ ማረኝ ! ጌታ ሆይ ማረን!" ልንል ይገባናል።
በብሉይ ኪዳን ነቢያት ዘወትር የእግዚአብሔርን ምህረት ለሕዝባቸው ይለምናሉ። እኛም ላለፈው ኃጢያቶቻችን ምህረትን ልንለምን ይገባናል። በፍፁም አልተሳሳትኩም የሚባል ስህተት የለምና። ኃጢአትን መካድ በራሱ ኃጢአት ነውና። በሉቃስ ወንጌል ምዕ.18፣9-14 ላይ እንደምናነበው ጽድቅን አግኝቶ የተመለሰውን ቀራጭ ማስታወስ እጅጉን ይጠቅማል። ምክንያቱም በትህትናውና ምህረትን በመለመኑ ጽድቅን አግኝቶ ሲመለስ በአንጻሩ እራሱን እንደመልካም ሰው ብቻ እየቆጠረ የተመጻደቀው ፈሪሳዊ ከበረከት ሸሸ።
አዲሱን ዓመት ስንቀበል ለወደፊት እንዲሻሻሉ ወይንም እንዲለወጡ የእግዚአብሔርን ፀጋ የምንጠይቅበት ወቅት ነው። የሰላምና የዕርቅ ዘመን እንዲሆንልን፤ የእግዚአብሔር ምሕረትና ፍቅር እንዲገዛንና የአምላክን ፀጋ በመምረጥ ሕይወታችን ትርጉም የሚያገኝበት ሁኔታ እንዲመጣልን ተስፋ በማድረግ አዲሱን ዓመት እንጀምረው።
ዘመናችን የማኅበራዊ ግንኙነት ዘመን ነው። ብዙ ድምፆችን እንሰማለን። ነገር ግን የሚሻለውንና የሚያስፈልገውን የምንለይበትን ፀጋ ከእግዚአብሔር መቀበልን አንዘንጋ። መልካሙን ለማስተናገድ ፈቃደኛ እንሁን። ነገር ግን ጎጂውንና አፍራሹን ለመሸሽ አናመንታ። እግዚአብሔር የሚወደውን የሰው ልጅን ክብር የሚያስጠብቀውን ለመቀበል አንፍራ። በአንጸሩ ፈጣሪ የሚወደውን፣ ከፈሪሃ እግዚአብሔር የራቀውን ጥበብ የሌለበትን ከመሸሽ ወደ ኋላ አንበል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ብፁዕ ወቅዱስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በቅርብ ጊዜ ለዓለም ሁሉ ስለ ሰው ልጅ ክብር በተጻፈው የቤተክርስቲያን ሐዋሪያዊ መልዕክታቸው የሚከተለውን አስተላልፈዋል። "በታላቅነቱ ሁሉ በእግዚአብሔር የተፈጠረው የሰው ልጅ ዛሬ ወሳኝ በሆነ ምርጫ ላይ ይገኛል፤ አዲስ የባቢሎን ግንብ መገንባት ወይም እግዚአብሔርና የሰው ልጅ አብረው የሚኖሩባትን ከተማ መገንባት"።
የመልዕክቱ ፍሬ ሐሳብ የሰው ልጅ የደረሰበትን ቴክኖሎጂና አስተውሎት መሰል መሳሪያ ለሰው ልጅ ክብርና ለፍትህ እንዲጠቀምበት ይጋብዛል። በሌላ አነጋገር የሰው ልጅ እራሱ በሰራው መሣሪያ ሰውን ዝቅ ካደረገ ፈጣሪንም ከደፈረ የባቢሎን ግንብ ታሪክ ተደገመ ማለት ነው። የዚያን ዘመን ሰዎች በትምክህታቸው ረጣሪን ለመቆጣጠር ፈለጉ። እርሱ ድረስ የሚደርስ ግንብ የሠሩ መስላቸው።
ነገር ግን በኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 11 እንደምናስተውለው ሰዎች እንኳን እግዚአብሔር ላይ ሊደርሱ፣ ይልቁንም እግዚአብሔር እነርሱን ለማግኘት እንደወረደ እናነባለን። በእነርሱ አመለካከት ወደ ከፍተኛ ስፍራ ደርሰዋል ነገር ግን ቅዠት ነበር።
ታዲያ የሰው ልጅ የሚከብረው በእግዚአብሔር የተሰጠውን መልክ በፍቅር ሲጠብቅ መሆኑን ከረሳና ይህንን መልክ ወደ ባርነት የሚወስድ መንገድ ከተከተለ ዕጣ ፈንታው የባቢሎን ግንብ ሰዎችን ዓይነት ሲሆን ነው ማለት ነው። እዚህ ላይ ግልጽ እንዲሆን እንፈልጋለን። ቤተክርስቲያን ቴክኖሎጂን አትቃወምም። ሆኖም ቤተክርስቲያን አደራ የምትለው ግን ሰው በዚች ምድር ላይ ልዩ ጥሪ፤ ልዩ ሃላፊነት፤ ልዩ ክብር አለውና ይህንን የሚረሳ ወይንም የሚያጠፋ መሣሪያ መሥራት ስህተት ነው የሚል ነው።
እያንዳንዱ ትውልድ የራሱን ዘመን የመቅረፅ እንዲሁም ታሪክ የእያንዳንዱ ሰው ክብር የሚጠበቅበት፤ ፍትህ የሚሰፍንበትና የሚስፋፋበት፤ ወንድማማችነትና እህትማማችነት በግልጽ የሚታይበት ስፍራ እንዲሆን የመምራት ሃላፊነት መውረስ አለበት። ሆኖም እያንዳንዱ ዘመን ሰብዓዊነት የጎደለውና የበለጠ ፍትህ የሌለው ዓለም የመፍጠር አደጋ ተደቅኖበታል። የሰው ልጅ እውነተኛ ማንነቱን የማበላሸት አደጋ በሚረጋገጥበት ጊዜ ሁሉ እና ክርስቲያኖች የሰው ልጅ ሚስጥር እውነት ሆኖ የሚገለፀው በእግዚአብሔር ቃል አማካይነት መሆኑን በማወቅ ኣይኖቻችንን ወደ እርሱ እናንሣለን። እውነትና ሕይወት በሆነው በክርስቶስ እያንዳንዳችን ወደ ሙላት እናድጋለን።
በመጨረሻም ሁላችንም በዚህ አዲስ ዓመት እውነተኛ ሰላምን እግዚአብሔር እንዲሰጠን እንፈልጋለን። ከእርስ በርስ ጦርነት ወጥተን፣ ሁሉም ጠግቦ የሚኖርበት የእውቀት ጮራ ለሁሉም የሚደርስበት፣ ስደትና መፈናቀል የሚያበቃበት፤ የተጣሉ እንዲታረቁ፤ ያልተማሩ እንዲማሩ፤ በበጎ ፈቃድ ተባብሮ በመጣር በአገራችን የተስተካከለና ፍፁም የሆነ ሰላም እንዲሰጠን በሙሉ ልባችን እንፀልይ እንመኝ።
ይህን የዘመን መለወጫ በዓል ስናከብር በችግረኞች መካከል በመገኘትና ችግራቸውን በማቃለል የችግራቸው ተሳታፊዎች በመሆን ክርስቲያናዊ ተግባራችንን እንፈጽም።
አዲሱ ዓመት ለታመሙት ምህረትን፤ ላዘኑት መጽናናትን፤ ለታሰሩት መፈታትን፤ በጭንቀት በችግርና በመከራ ውስጥ የሚገኙትን ወገኖችንንን እግዚአብሔር ሰላሙንና ፍቅሩን ፀጋውን የሚሰጣቸው የምህረት ዓመት ያድርግልን።
ልዑል እግዚአብሔር አዲሱን ዓመት ይባርክልን፣ ይቀድስልን፣ ሰላሙን ያውርድልን። በመንፈስ ቅዱስ ብርሃን በጥበብ እንድንመራ ያድርገን።
በድጋሚ ሁላችሁንም እንኳን ለ2019 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ።
እግዚአብሔር አዲሱን ዘመናችንን ይባርክልን።

ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የቀድሞ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳሳትና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊ ጳጳሳት ጉባዔ ፕሬዜዳንት መንፈሣዊ አገልጋይ የ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት።
ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

🎊መልካም የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት🎊 🎊 Frohes äthiopisches neues Jahr!🎊
10/09/2026

🎊መልካም የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት🎊
🎊 Frohes äthiopisches neues Jahr!🎊

የ2019 ዓ/ም ዓዲስ አመት መሰዋዕተ ቅዳሴእሑድ ሴፕቴምበር 13 ቀን 2026 ዓ/ምከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮቦታ: Sancta Famila-Ginnheim       Am Hochwehr 11   ...
06/09/2026

የ2019 ዓ/ም ዓዲስ አመት መሰዋዕተ ቅዳሴ
እሑድ ሴፕቴምበር 13 ቀን 2026 ዓ/ም
ከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮ
ቦታ: Sancta Famila-Ginnheim
Am Hochwehr 11
60431 Frankfurt am Main

06/09/2026
መሰዋዕተ ቅዳሴእሑድ ሴፕተምበር 06 ቀን 2026 ዓ/ምከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮ ቦታ: St. Stephan Kirche         Baumkirchner Str.39         81673 Mü...
02/09/2026

መሰዋዕተ ቅዳሴ
እሑድ ሴፕተምበር 06 ቀን 2026 ዓ/ም
ከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮ
ቦታ: St. Stephan Kirche
Baumkirchner Str.39
81673 München

መሰዋዕተ ቀዳሴእሑድ ኦገስት 23 ቀን 2026 ዓ/ምከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮቦታ:  St. Stephan Kirche        Baumkirchner Str. 39        81673 Münch...
20/08/2026

መሰዋዕተ ቀዳሴ
እሑድ ኦገስት 23 ቀን 2026 ዓ/ም
ከጠዋቱ 10:30 ሰአት ጀምሮ
ቦታ: St. Stephan Kirche
Baumkirchner Str. 39
81673 München

🌹የፍልሠታ ማርያም በዓል - አልትኦቲንግ 2026🌹በየአመቱ በአልትኦቲንግ በታላቅ ክብር የሚከበረው የጥቁራ ማርያም የፍልሠታ በዓል፣ ዘንድሮም በ14 እና 15 ኦገስት 2026 ዓ/ም በታላቅ ድም...
17/08/2026

🌹የፍልሠታ ማርያም በዓል - አልትኦቲንግ 2026🌹

በየአመቱ በአልትኦቲንግ በታላቅ ክብር የሚከበረው የጥቁራ ማርያም የፍልሠታ በዓል፣ ዘንድሮም በ14 እና 15 ኦገስት 2026 ዓ/ም በታላቅ ድምቀትና ልብ በሚነካ መንፈሳዊ ድባብ ተከብሮአል።
በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ፕሮግራም ላይ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ በርካታ አማኞችና ነጋዲያን በፀሎት፣ በቅዳሴ፣ በዑደትና በሌሎችም መንፈሳዊ ሥነ ስርአቶች በመሳተፍ የተባረከና የልብ ሰላም የሚሰጥ ጊዜ አሳልፈዋል።
የኛም አባላቶች በቦታው ለይ በብዛት በመገኘት የቡራኬው ተካፋይ ሆነዋል። በተጨማሪም መዝሙር በመዘመርና በማሸብሸብ የብዙዎችን ስሜት ማርከው ነበረ።
በዚህ ታላቅ የእምነት፣ የፀሎትና የአንድነት በዓል ላይ እንድንሳተፍ ላደረገን ሁሉን ቻይ አምላካችን ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን።

06/08/2026

ሰላም ካቶሊክ ቲቪ Pax ...

መሠዋዕተ ቅዳሴ እና የመቁጠሪያ ፀሎትእሑድ ኦገስት 09 ቀን 2026 ዓ/ምከጠዋቱ 10:30 ሰዓት ጀምሮቦታ: Sancta Famila-Ginnheim       Am Hochwehr 11       60...
05/08/2026

መሠዋዕተ ቅዳሴ እና የመቁጠሪያ ፀሎት
እሑድ ኦገስት 09 ቀን 2026 ዓ/ም
ከጠዋቱ 10:30 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ: Sancta Famila-Ginnheim
Am Hochwehr 11
60431 Frankfurt am Main

Adresse

Am Hochwehr 11
Frankfurt

Telefon

+4917622679250

Webseite

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Ethiopian Catholic Community in Germany /Äthiopische katholische Gemeinde/ erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Die Kultstätte Kontaktieren

Nachricht an Ethiopian Catholic Community in Germany /Äthiopische katholische Gemeinde/ senden:

Verknüpfungen

Teilen