11/07/2026
"የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና። ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤
የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል።"መዝ 83/84፥6
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
በዳርምሽታትና አካባቢው የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ የዳርምሽታት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለብዙ ዓመታት እንጠቀምበት ከነበረው ቤተ ክርስቲያን ወደአዲስ ቤተ ክርስቲያን መቀየሩ ይታወቃል ይህን ምክንያት በማድረግ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም /Juli 19 .2026/ ብፁዕ አባታችን አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በቦታው ተገኝተው ምዕመናኑንም ቤተክርስቲያኑንም ይባርካሉ የጽዮንም አምላክ በእኛም ለይ በቤተክርስቲያኑም ያድራል።
ይህንን ተረድታችኁ ሁላችሁም ከጧቱ 5 ሰዓት አንስቶ በቦታው በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊዎች ትሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።
📍 St. Giorg Kirche
Stockhausenweg 50,
64297 Darmstadt-Eberstadt
የዳርምሽታት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት