08/09/2022
የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባት አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ አላቸው።
መጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ 12:6
በሰው ነፍስ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው
መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ 6:3
ሩፋኤል ማለት የስሙ ትርጓሜ
ሩፋ ማለት ጤና፣ፈውስ መድኃኒት ማለት ነው
ኤል ማለት አምላክ ማለት ነው
በጥምረት ,የእግዚአብሔር ሐኪም ማለት ነው ።
ሩፋኤል ከሦስቱ ሊቀነመላዕክት ሦስተኛው ሊቀ መላዕክት ነው,
ቅዱስ ሚካኤል
ቅዱስ ገብርኤል
ቅዲስ ሩፋኤል
ጳጉሜ ሦስት የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሲመቱ ነው
በዚህ ቀን ሐዋርያቱ ክርስቶስን ፣ጌታ ሆይ የከበረ መልአከ የቅዱስ ሩፋኤልን ክብር ታስረዳን ዘንድ እንለምንሐለን አሉት
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ያን ጊዜ ሦስቱን የመላአክት አለቆች ቅዱስ ሚካኤል ፣ቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ሩፋኤልን ከሦስተኛይቱ ሰማይ ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው
እነሱም ደስ እያላቸው መጡ
ጌታችንም ሩፋኤልንም የክብርህን ታላቅነት ያውቁ ዘንድ ስምህን ለሐዋርያት ነገራቸው አለው
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሩፋኤልም ለሐዋርያት እንዲህ አላቸው ፣እኔ ሩፋኤል እባላለሁ የዋህ ነኝ ከመላእክት አለቆች ሦስተኛው ነኝ ፣ ልቦናን ደስ የሚያሰኝ የዋህ ቸር ለኃጥአን የምራራ ነኝ ፣በማለት ለሐዋርያቱ ብዙ ነገር ነገራቸው
ድርሳነ ሚካኤል ዘ ጳጉሜ
የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ፣ በዓሳ ሐሞት ኩለህ የጦቢት አይን እንዳበራህ ሁሉ የእኛንም አይነ ልቦና አብራልን አሜን .። ከሐብተ ረድኤትህም ተሳታፊ አድርገን አሜን.።
አቤቱ የቅዱስ ሩፋኤል አምላክ ሆይ ከመከራ ነፍስ ከመከራ ስጋ ሰውረን ጠብቀን አሜን ።