የዲን ወታደር Ye din wetader

የዲን ወታደር Ye din wetader our page serves to peoples who wants real information

SHARE  SHARE  SHARE ያድርጉLIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ #የፌስቡክ  #ገጻችንን  #የዲን  #ወታደር  #የሚለዉን  #ይህንን👇🏿...
28/02/2026

SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

"ደሴ ላይ መስጅዳችን ታሽጎብን ውጭ እየሰገድን ነው" የደሴ ነባር አህሉሱና ሙስሊሞች በአማራ ክልል ወሎ አካባቢ ያለው ግፍ ልኩን ያለፈ ይመስላል።ለዚህም ደግሞ የሱፍዩ አምርሮ ያለመታገል ውጤ...
23/02/2026

"ደሴ ላይ መስጅዳችን ታሽጎብን ውጭ እየሰገድን ነው" የደሴ ነባር አህሉሱና ሙስሊሞች

በአማራ ክልል ወሎ አካባቢ ያለው ግፍ ልኩን ያለፈ ይመስላል።ለዚህም ደግሞ የሱፍዩ አምርሮ ያለመታገል ውጤት ይሆን ወይንስ በአካባቢው ያለው መንግስታዊው የውሀብይ ሀይማኖት ደጋፊ ጫና የሚለውን ለይቶ አምርሮ መታገል ግድ የሚልበት ስአት ላይ እንገኛለን።ደሴ ከተማ ጅብሪል ጎራ መሥጅድ ቧንቧ ውሀ ክፍለከተማ ቀበሌ 012 ከመሥጅድ ተባረዉ ለ15 አመት ቂርአት ሢያቀሩ የኖሩበት መሥጅድ ሸይኹን ጨምሮ ከነ ደረሦቻቸው ተባረዉ በረመዷን መስጂዳቸው ታሽጎ ውጭ ላይ እየሠገዱ መሆኑ ምእመናን ገልፀዋል ።

አያይዘዉም በመጅሊሱ የሚደገፈዉ የውሓብያ አንጃ መሥጅዳችን ገብተው ደረሦቻችንን ከደበደቡ በሗላ ሦሥት ደረሳ አካል ጉዳተኛ አድርሠውብናል ብለዋል ።

በተጨማሪም ደረሳ ሰብስበዉ የሚያቀሩት ሸይኽ ደግሞ ደረሣወችህን ካልበተንክ በፓሊሥ እርምጃ እናሥወሥድብሀለን ብለው ደብዳቤ ፅፈዋል በማለት ገልፀዋል ።

በሀይማኖት ላይ የሚደርስብን በደል በተመለከተ ለሚመለከተው ሁሉ አድርሡልን ሲሉ ተማፅነዋል ።በተጨማሪም ወጣቱና የአካባቢው ነዋሪ ተደራጅቶ የፈለገውን የፈለገውን የማምለክ መብት እንዳለውና መጅሊስ ተብየው ውሀብያውን እንጅ የአንተ እምነት ለኔ አይሆነኝም ያለው ጋ መድረስ እንደሌለበት በፍ/ቤት በኩልም ቢሆን መብት የማስከበር ሂደቱ መቀጠል አለበት በማለት እያስታወቅን ሰሚ ያለው secular የአካባቢው አስተዳደር ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ እኛም ጥሪ እናቀርባለን።

በተመሣሣይ በዚሁ በአማራ ክልል የመስጂድ ኢማም የነበሩ የሀይማኖት አባት የረመዷን በተለያዩ ወቅቶች የሚደረጉ ዚክሮች ታደርጋለህ በማለት መታሠራቸዉ ተገልጿል ።

በተያያዘ ዜና ኮምቦልቻ አሊ መስጅድ በውሀብያ ካልሰገዳቹህ ተብለው የታሰሩ 15 ደረሶች በገንዘብ ተገዝተው በሚመጡ ፖሊሶችና ምኒሻወች እስካሁን እንዳልተፈቱ ተገልጿል።የዛ አካባቢ አስተዳደር ደግሞ መብት የሚባል ነገር የማይገባው የለየለት ውሀብያዊ መንግስት ሆኖት አርፏል።

በቃ-ውሀብያዊ መንግስት
በቃ-በሱፍያ መስጅዶች ያለው ግፍ

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

ልክ ያለፈው የውሀብይ ቡድን በኮምቦልቻ ከተማ አሊ መስጅድ ላይ ተራዊህ አስቆመ!!!በኮምቦልቻ ከተማ በተደራጀ መልኩ የሱፍይ መስጅዶችን በስመ-ሀፊዝ ህጻናት ካላሰገዱ በሚል ሰፊውን ሱፍይ ሙስሊ...
22/02/2026

ልክ ያለፈው የውሀብይ ቡድን በኮምቦልቻ ከተማ አሊ መስጅድ ላይ ተራዊህ አስቆመ!!!

በኮምቦልቻ ከተማ በተደራጀ መልኩ የሱፍይ መስጅዶችን በስመ-ሀፊዝ ህጻናት ካላሰገዱ በሚል ሰፊውን ሱፍይ ሙስሊም በመናቅ፣በህገ-ወጥ ሴራ ወንበር የያዘው የውሀብዩ መጅሊስ በረመዳንም ህዝቡን ከመበጥበጥ አልተቆጠቡም።

የህዝቡ ፍላጎትን ወደ ጎን በመተው ማ ሲባል የሚመጣ ሂድ ሲባል የሚሄድ በውሀብያው መጅሊስ የሚታዘዘውን ሚኒሻና ፖሊስን በመጠቀም አሁንም ከተማው ውስጥ አብሮ ያደገውን የተራዊህ ሶላትና ዚክር ለማስቆም የማያባራ ተንኮል ውስጥ ገብተዋል።

ግን ግን ከልጅነታችን ጀምሮ ያደግንበትን እምነትና መስጅድ ዛሬ ላይ ከመሬት ተነስተው ሊያፈናቅሉን እና የእነሱን ተላላኪ መስጅዳችን ውስጥ ካላመጣን የሚሉትን ወንበዴወች ለምን ይሆን ዝም ብለን የምናያቸው? በቃቹህ የሚል ህዝባዊ ትግልና ንቅናቄ በህቡእ ተደራጅቶ ሰላማዊ ግን ተጽእኖ ፈጣሪ እንቅስቃሴ በመጀመር ህዝባዊ ትግል ግድ የሚልበት ስአት ደርሷልና አሁንም እምቢ ማለት አለብን።

መስክዱን አሳልፎ የሚሰጥ፣ህዝብ ከመረጠው ኢማም ውጭ ከየትም የመጣ ህጻናትን ተራዊህ የሚያሰግዱበትን ሴራዊ-አካሄድ በቃ ሊባል ይገባል።ይህንን ህዝባዊ ፍላጎትም መንግስታዊው አስተዳደርም ሆነ ታጣቂ ቡድኑ ገንዘብ ለሸጎጠለት ሳይሆን ህዝብ የሚፈልገውን ነው ማድረግ የሚኖርበት።

መስጅድ ነጠቃ-በቃ
ኢማሞቻችን ማባረር -በቃ
ያደግንበትን መስጅድ መበረዝ -በቃ
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

ጉዳዩ : -  ይግረም የመስጂዳችን ኮሚቴ ሰብሳቢነቱ ላይ እንዲፀና ፍላጎታችን መሆኑን ስለማሳወቅ    በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ውስጥ የሚገኘው የአቃቂ ራህማ መስጂድ በአዲስ አበባ ...
18/02/2026

ጉዳዩ : - ይግረም የመስጂዳችን ኮሚቴ ሰብሳቢነቱ ላይ እንዲፀና ፍላጎታችን መሆኑን ስለማሳወቅ

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ውስጥ የሚገኘው የአቃቂ ራህማ መስጂድ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ቀደምት ታሪካዊ መስጂዶች አንዱ ሲሆን ከ95% በላይ የሚሆነው ሰፊውን ቁጥር የሚሸፍነው የአካባቢው ማህበረሰብ ሱፊይ ነው ። መስጂዱ ከምስረታው ጀምሮ በነባሩ እስልምና ሱፊያዊ አስተምህሮ ደምቆ በታሪኩ አንዳች ኮሽታ ሳይሰማበት እስካሁኑ ጊዜ ድረስ ፍፁም ሰላም የሰፈነበት ሆኖ ዘልቋል። ይሄን ከሙስሊሙ አልፎ ሙስሊም ያልሆኑ የአካባቢው ነዋሪያንም በአጠቃላይ በአንድ ድምፅ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው።

ከ2014 ጀምሮ ግን ያለ ምንም ህጋዊ መሰረት እና ህዝባዊ ቅቡልነት መስጂዱን ከአካባቢው ሱፍያ ማህበረሰብ ነጥቆ ለመቆጣጠር እና ከምስረታው ወቅት አንስቶ የነበረውን የሱፍያ አስተምህሮ በሂደት ሙሉ በሙሉ ለመቀየር በማለም የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገው በመስጂዱ ጀመዓ ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።

2015 ላይ የክፍለ ከተማው መጅሊስ የመስጂድ ኮሚቴዎችን በማሳሰር መስጂዱን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ አድርጎ ከብዙ ልፋት በኃላ በኮሚቴዎች እና ህብረተሰቡ ትግል ከነበሩት ኮሚቴዎች ገሚሶቹ ተቀንሰው መጅሊሱ የፈለጋቸው ውሃቢያዎችን በእነርሱ ፋንታ በመተካት እንዲሰባጠር ተደረገ። ይህ የሆነው የወረዳ ፖሊስ እንዲሁም የሰላም እና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊዎች ባሉበት መስጂዱ ላይ ከምስረታ ጀምሮ የቆየውን የሱፍያ አካሄድ ላይነኩ ፤ ከልማት በቀር የመስጂድ እና የመድረሳ ጉዳይ ላይ ላይገቡ ፤ የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ ያልፈለገውን አንዳች ነገር ላያደርጉ በፊርማቸው በማረጋገጥ ነው። ቃለጉባኤውም የወረዳው ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ይገኛል።

ለረጅም ዓመታት የመስጂዳችን ኮሚቴ በመሆን በልዩ ትጋት እና ቀናኢነት ያገለገለው አቶ ይግረም ገብረመድህን በ2017 ሀገር አቀፍ የመጅሊስ ምርጫ ላይ ከፍተኛ ድምፅ ሰጥተንው የወረዳችን መጅሊስ ፀሀፊ ሆኖ ተመርጦ ሁለቱም ቦታ ላይ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ሆኖም ግን 2 ኃላፊነት ላይ ማገልገል ስለማትችል አንዱን ምረጥ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ሁለቱም ቦታ ላይ እንዳልሰራ የሚከለክለኝ ህግ ከሌለ 2ቱም ቦታ ላይ እሰራለሁ ፤ ከልካይ ህግ ካለ ግን ከህግ በላይ አይደለሁምና የመስጂድ ኮሚቴ ሰብሳቢነቴ ላይ እንዳገለግል ነው እኔም ሆንኩ የአካባቢው ህዝበ ሙስሊም የሚፈልገው የሚል አጭር እና ግልፅ ምላሽ ሰጥቶ ነበር። የክፍለ ከተማው መጅሊስ ግን የእሱንም ሆነ የእኛን የአካባቢው ማህበረሰብ ፍላጎት ወደ ጎን በማለት የወረዳ መጅሊስ ፀሀፊነትህ ላይ ነው መስራት ያለብህ የሚል በየትኛውም መመዘኛ አግባብነት የሌለውን ሃሳብ አንስቷል ።

አቶ ይግረም ሁለቱም ቦታ ላይ በህዝብ ተመርጦ የመጣ መሆኑ እሙን ሲሆን የመስጂድ ኮሚቴ ሰብሳቢ መሆኔ ለመጅሊስ ምርጫ ከመወዳደር የሚያግደኝ ከሆነ በሚል መራጮች ባሉበት በምርጫው ወቅት ላይ ጥያቄ አቅርቦ ችግር የለውም ተብሎ ምላሽ እንደተሰጠው ሁላችንም የምናውቀው ነው። ከዚህም ባሻገር ሁለቱም ቦታ ላይ መስራት የማይቻል ከሆነ የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ እና አስተባባሪ ግብረሃይል ባሉበት ህዝብ ፊት በጥቆማ ቀርቦ ድምፅ ሊሰጥበት ሲል የመስጂድ ኮሚቴ መመረጥ አይችልም ተብሎ መከልከል ነበረበት። ይሄ ግን አልተደረገም።

የምርጫ ማስፈፀሚያ ደንቡ ውስጥም መመረጥ የማይችሉት እነማን ናቸው የሚለው ክፍል ላይ የመስጂድ ኮሚቴ የሚል ፈፅሞ አልተጠቀሰም። በግልፅ የሚከለክል ነገር ቢኖር እኛም ባልጠቆምንው እና ድምፃችንን ባልሰጠንው ነበር ። እውነታው እንዲህ ሆኖ ሳለ በእሱም ሆነ በመረጠው ህዝብ ባልሆነ ስህተት እራሱም ሆነ የአካባቢው ማህበረሰብ የሚፈልገው ቦታ ላይ እንዳያገለግል መከልከል ከህዝቡ በላይ ለህዝቡ እኔ አውቅለታለው የሚል ስላቅ ሲሆን መስጂዱን ከሱፍያው ነጥቆ የአስተሳሰብ ገፅታ ለውጥ ለማድረግ ያለመ እንቅስቃሴ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው።

በመጨረሻም የሚመለከተው የመንግስት ክፍል እኛ የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ በምንፈልገው አካል የመመራት መብታችንን እንዲያረጋግጥልን እና መስጂዱ ላይ ያጠለለውን አላስፈላጊ ሰላም አደፍራሽ እንቅስቃሴ እንዲያስቆምልን ፊርማችንን አባሪ በማድረግ ከታላቅ አክብሮት ጋር እንጠይቃለን ።

የአቃቂ ራህማ መስጂድ ወጣት ጀመዓ

SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

✍️ባለፈው ሳምንት ማለትም የካቲት 4 -2018 ወረኢሉ ወረዳ በሚገኘው የሸይኽ በድሩ ሐሪማ ደማቅ የመዉሊድና የዱዓ ፕሮግራም ተከናዉናል። በፕሮግራሙ ላይ በተለያዩ ሐሪማዎች የሚያስተምሩ ከ10...
18/02/2026

✍️
ባለፈው ሳምንት ማለትም የካቲት 4 -2018 ወረኢሉ ወረዳ በሚገኘው የሸይኽ በድሩ ሐሪማ ደማቅ የመዉሊድና የዱዓ ፕሮግራም ተከናዉናል። በፕሮግራሙ ላይ በተለያዩ ሐሪማዎች የሚያስተምሩ ከ1000 በላይ ዑለሞች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል።

በዕለቱ ለዲን እንዲሁም ለሐገር ሰላም ጥልቅ የሆነ ዱዓ ተደርጓል። ተነፋፍቀው የነበሩ ዑለሞች ለመገናኘትና የልባቸውን ለመጨዋወት ችለዋል። እንዲሁም የቀደምት የሐበሻ ዑለሞች አስተምህሮት ምን ነበር በሚለው ዘለግ ያለ ማብራሪያ በዑለሞች ተደርጓል።

የፕሮግራሙ ተሳታፊ የነበሩት የሐሪማ ባልተቤቶች እና ዑለሞች ሰፊ የሆነ ዉይይት ካደረጉም በኋላ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አዉጥተዋል።

ከአማራ ክልል ከተለያዩ ዞኖች በደቡብ ወሎ-ወረኢሉ ከተሰበሰቡ ዑለሞች እና የማህበረሰብ ተወካዮች የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በአህሉሱናህ ወልጀመዐ እና ራሱን ሰለፍያ ብሎ በሚጠራው የወሃብያ ቡድን መካከል መሰረታዊ የእምነት ልዩነት መኖሩን በግልፅ እናስዉቃለን።

❷ የተቋቋመው መጅሊስ ጥቂት ፐርሰንትን በማይሞሉ ራሳቸውን ሰለፍያ ብለው በሚጠሩ ቡድኖች በተደረገ ህገወጥ ምርጫ የአህሉሱናህ ወልጀመዐ-ሱፊያህ ያልተሳተፈበት በመሆኑ እኛን የማይወክል መሆኑን እናሳዉቃለን።

❸ ተመርጫለሁ በሚለው ቡድን እየደረሰብን ያለው ጫና ፤ በደል እንዲሁም የመብት ጥሰት አምባገነናዊ በመሆኑ በጥብቅ እናወግዛለን ።

❹ ይህ ቡድን ባልሰራው መስጂድና ተቋም በየቦታው የሚያደርገዉን መስጂድ ነጠቃና የኢማሞች ቅየራ እንዲሁም በራሱ አምሳል ለመቅረፅ የሚያደርገዉን የእምነት-ንቅለ ተከላ አጥብቀን እንቃወማለን።

❺ የተቀሙ መስጂድና ተቋማት እንዲሁም የተባረሩ ኢማሞችን ለማስመለስ በህጋዊ መንገድ በጋራ እንሰራለን።

❻ የሱፊያውን አቋም ለማስቀየር በሱፊያ ስም በየሐሪማው እየዞሩ በሱፊያው መካከል ልዩነት እንዲፈጠር የሚሰሩ ቡድኖችን አጥብቀን እንቃወማለን።

❼ አንዳንድ በመንግስት መዋቅር ዉስጥ ያሉ በሓይማኖት ዉስጥ ኢ ህገመንግስታዊ ጣልቃ እየገቡ በሱፊያው ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ እንዲሁም እስራት በማድረግ ሱፊያው ማህበረሰብ ከመንግስት ጋር ለማቃቃር እያደረጉ በመሆኑ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አጥብቀን እናሳስባለን።

❽ ነባሩ የአህሉሱናህ ወልጀመዐ-ሱፊይ ሙስሊም በኢትዮጲያ ዉስጥ 1400 በላይን ያስቆጠረና እውቅና ኖሮት ሲንቀሳቀስ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግልፀኝንነት እና ተአማኒነት በሌለው የተጭበረበረ ምርጫ መጤ አስተሳሰብ ባላቸው ቡድኖች የተያዘ መዋቅር እኛን ስለማይወክል ተቋማችንን በህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እንሰራለን።

❾ ሐይማኖት በፍላጎት እንጂ በሐይልና በጉልበት ስለማይቀየር በራሱ አስተሳሰብ ሙስሊሙን ለማጥመቅ ሌት ከቀን እየሰራ ያለውን መጅሊስ በጋራ እንከላከላለን።

❿ በሱፊያዉ እና እራሱን ሰለፊያ ብሎ በሚጠራው ቡድን መካከል መሠረታዊ የእምነት ልዩነት ስላለ አሁን ካለው መጅሊስ ለመነጠል አጥብቀን እንሰራለን።

የካቲት - 4 - 2018
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

ይህን ያክል በየ ሐገሩ ለሚደክሙት መሪያችን ሲባል የሐጅ ዋጋ ላይ አስተያየት መስጠት የተከለከለ ነው!ይቺ ብር የተለያዩ እስላማዊ አለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ሲካሄዱ "ክቡር መሪያችን ሃጂ ቱፋ"...
02/12/2025

ይህን ያክል በየ ሐገሩ ለሚደክሙት መሪያችን ሲባል የሐጅ ዋጋ ላይ አስተያየት መስጠት የተከለከለ ነው!

ይቺ ብር የተለያዩ እስላማዊ አለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ሲካሄዱ "ክቡር መሪያችን ሃጂ ቱፋ" ስብሰባዉን ለመካፈል ሲሄዱ የአየር በረራ ፣ የፔንሲዮን ፣የቀን አበል…ወጪ ሳይጨምር ለአንዲት ቀን ለምግብ ብቻ ከምንበጅትላቸዉ በጀት ሰባት እጥፍ ያነሰ ነዉ::

ታላቁ መሪያችን ክቡር ሃጂ ቱፋ ሀፊዘሁሏ የዘንድሮው ዓመት ከገባ ብቻ ሃያ ዘጠኝ አለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ ተሳትፈዋል/ከሌላ ሃገር የመጡት ተሳታፊዎች ለቁርስ ብቻ በርካታ ሚሊየን ሲመድቡ /ለምስኪኑ መሪያችን ሃጂ ቱፋ ግን ለአንድ ቀን ቁርስና ምሳ እራትን ጨምሮ ሶስት ሚሊየን ብር ብቻና ብቻ ነዉ ዉጪ ምናደርገዉ /

ወጪያችን ከገቢያችን ጋር እየተመጣጠነ አይደለም አህመዲን ጀበል ለሚያስተዳድረዉ ለኢምፓክት ሜከርስ ፋዉንዴሽን የክፍለ ከተማና የክልል አመራሮችን እንዲያሰለጥን በርካታ ቢሊየን ብሮችን እያፈሰስን ነዉ /

ገቢያችንን ለማሳደግ ስንል መድረሳ እያፈረስን ሚከራይ ሱቅ እየገነባን ነዉ /ገቢ የማሳደግ እቅዳችን አሊ መስጂድ እና ጎሮ አንቢያ መስጂድ ላይ ዉጤታማ ስለሆነ በተመረጡ ሌሎች ሱፊ መሳጂዶች ላይም ኢንሻ አላህ መድረሳ አፍርሶ ሱቅ የመገንባት ዕቅዱ ተግባራዊ ይሆናል /

ሌላዉ ገቢ የመፍጠር ዕቅዳችን ዉስጥ የተካተተዉ ቦሌ ኤድናሞል አከባቢ አዲሱ አደይ አበባ እስታዲየም ጎን ያለዉ ግዙፉ ጡሩ ሲና መስጂድን ለስፖርት ኮሚሽን ጠቀም ባለ ብር የመሸጥ ድርድር ዉስጥ ነን አቡነ ጴጥሮስ ሃዉልት ጋር የምትገኘዉ ቲኒሿ አወሊያም ግንባር ቦታ ናት ከሷ ሽያጭ ሚገኘዉ ብርም በጣም ብዙ ወጪ ይሸፍንልናል ::

ገቢና ወጪያችንን የሚያመጣጥን ጥናት በአንድ ታዋቂ ኡስታዝ ድርጅት ለማስጠናት 10 ቢሊየን ብር ተዋዉለናል /ለጥናቱ የተዋዋልነዉን በጀት ለድርጅቱ ለመክፈል የሃጁን ገቢ እየጠበቅን ነዉ /

[የፌደራል መጅሊስ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ተጠሪ አቶ ሰቦቃ ዉቃ]
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

የዘንድሮ ሀጅ ዋጋ 740,000 ሽ ብር ነው ተባለ!!!አሁን ነው ሙፍቲ ሰያሚ ሀጅ አይወጅብም ባዩን መጥራት@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@ህዝቡ በኑሮ ውድነት እየተሰቃየ፣የእለ...
01/12/2025

የዘንድሮ ሀጅ ዋጋ 740,000 ሽ ብር ነው ተባለ!!!አሁን ነው ሙፍቲ ሰያሚ ሀጅ አይወጅብም ባዩን መጥራት
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
ህዝቡ በኑሮ ውድነት እየተሰቃየ፣የእለት ኑሮውን የሚያቃልል መፍትሄ የሚያመጣ ሀሳብ ሲናፍቅ ሴረኞች ሆዳቸው እንዳይጎድል እና የደላላወቻቸው ኮሚሽን እንዳይቀንስ በህዝቡ ላይ የተጫኑት የመጅሊስ ሰወች ግን እያደሩ ምን ታመጣለህ በሚል እልህ ውስጥ 740 000 ሽ ብር ነው ብለው ብቅ ብለዋል።

100 ሽ ብር የሀጅ ዋጋ ተደረገ ብለው ራሳቸው የሙፍትሂነት ማእረግ የሚያጎናጽፉት የነ አቡበክር እና የነ አህመዲን ዳይናስቲ "እኛ ያቋቋምናቸው ሙፍቲወች ዘንድሮ ሀጅ አይወጅብም ብለዋል "የሚል ፕሮፓጋንዳቸውን ያስታወሰ ሰው የሆነ ሁሉ እነዚህ ሰወች ወሬያቸው እና ተግባራቸው፣ሌብነትና ሽቀላቸው አይን ያወጣ የዘራፊ ጥርቅሞች መሆናቸውን በግልጽ ይረዳል።

ኢማምና በማባረርና መድረሳ በመንጠቅ ላይ ያለው ይህ የውሀብይ ስብስብ በሙስሊሙ ላይ ተጭኖ እንደ መዥገር በያንዳንዱ አገልግሎት ላይ ሁሉ ካልመጠጥሁህ ያበዛ ይመስላል።
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

ኢማም ማባረሩ፣መድረሳ መንጠቁ በተደራጀ ሁኔታ ተባብሷል።ብቸኛ መፍትሄው በትግልህ  @@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ እና ሱፍያው ሙስሊም በቆረቆራ...
27/11/2025

ኢማም ማባረሩ፣መድረሳ መንጠቁ በተደራጀ ሁኔታ ተባብሷል።ብቸኛ መፍትሄው በትግልህ
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ እና ሱፍያው ሙስሊም በቆረቆራቸው መስጅዶች ያሉ እና የሱፍይ ኢማምን፣የሱፍያ መድረሳ ኮሚቴን የአዲስ አበባ መጅሊስ ነን ባዮች በየ ክ/ከተማው እየዞሩ በማባረር ላይ ተጠምደዋል።የራስህን ተቋም ሌላ አካል መጥቶ የሚያባርርበትና የሚረከብበት አካሄድ በእኛ ሀገር ብቻ የሚገኝ ግፍ ነው።ይህንን ከላይህ ላይ የተጫነን ሸክም ደግሞ በተደራጀ ትግል፣በሚጠይቀው መስዋእትነት ሁሉ ከፍሎ የሱፍያን መጅሊስ በመመስረት ነጻነትህን ማወጅ የግድ ይላል።

በዚህ ሳምንት ብቻ የአምቢያ መስጅድ ኢማምን በግፍ ያባረረው የውሀብይ ስብስብ፣ውሎ ሳያድር ደግሞ መድረሳ ሊነጥቅ እያኮበኮበ ይገኛል።ባለፈው ያፈረሰውን መድረሳ ለንግድ ያከራየው ይህ ጥቅም አሳዳጅ ቡድን ዝም ካልከው የሱፍይ መኖሪያ ቤትንም አስረክቡኝ ማለቱ የማይቀር ይመስላል።ታዲያ ምን እስኪሆን ነው የሚጠበቀው? ካልን ለዚህ መራራ ትግል ከፊት የሚሆኑ መሪወች እና ለመሪወቹ ፍጹም ታዛዥ የሆነ ተከታይ ሱፍይ በውጭም በሐገር ውስጥም በማደራጀት ይህንን ማንም ሊነጥቅህ የማይችለውን ሰብአዊ መብት ማስከበር ይገባል።
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

 አብሮ ሊያደርግህ ከማይችል ብዙ ምክንያቶችና፣በእምነትም ከማይመሳሰልህ፣በአንተ ስም የሚነግድ እና የአንተን መስጅድ የሚነጥቅ ቡድን ጋር ለምን አንድ ነህ ተብለህ ቁስልህን  ታባብሳለህ?ለምንስ...
09/11/2025



አብሮ ሊያደርግህ ከማይችል ብዙ ምክንያቶችና፣በእምነትም ከማይመሳሰልህ፣በአንተ ስም የሚነግድ እና የአንተን መስጅድ የሚነጥቅ ቡድን ጋር ለምን አንድ ነህ ተብለህ ቁስልህን ታባብሳለህ?ለምንስ ያለህን ታጣለህ

በቃ እኮ እነሱ መውሊድ የሚባል በአል የሌላቸው፣ተበሩክ የማያውቁ፣ሽርክና ዚያራ የተምታታባቸው፣ከራሳቸው ውጭ ሌላውን አማኝ የማይመስላቸው፣በፖለቲካዊ ሴራ እንጅ በፍትሀዊነት ለህዝብ መቆም የማይችሉ ሰወች ጋር በአንድ ተቋም ለመኖር የሚያስችል የህግም፣የሞራልም ግዴታ የለብንም።

እንኳን መጅሊስ መስራች የሆነ በሚሊዮን የሚቆጠር ሱፍይ ሙስሊም ቀርቶ አንድ ግለሰብ እንኳ የፈለገውን እምነት የማመን እና የመከተል መብት እያለው 6 አመት ሙሉ ቢሮ ሰብሮ የገባው እና በማጭበርበር ምርጫ ተጨፍልቀህ በእምነት በማይመስሉት ሰወች ተቋምህን አስረክበህ፣ያለህን እየተቀማህ ኑር የሚል አካል አይኖርም።ቢኖርም መብትን በትግል ማስከበር የእኛ የአማኒያን ግዴታ ይሆናል።ከዚህ በላይ እያስታመሙ፣እምነታችንን በማያምኑ፣እምነታችንን እና አቂዳችንን በይፋ በሚቃወሙ ስብስቦች መቸም ቢሆን እንደ መሪ ቆጥረን አብረን ልንቀጥል የሚያስችል ትሥስር አይኖረንም።በመሆኑም ይህንን ይፋ የወጣ ያገጠጠ ያፈጠጠ የእምነት ልዩነት ያለን ማህበረሰቦች እምነታችንን ከሚቃወም፣በአላችንን ከሚንቅ፣መስጅዳችንን ከሚነጥቅ ስብስብ የተዋቀረን ቡድን መንግስት እንዳቋቋመው ሁሉ ራሳቸውን አስችሎ ተቋም እና መሪወቻችንን በመረጥነው ሁኔታ፣ባለን ሀገራዊ ታሪክ እና ተቋም ምስረታ ዋጋ ልክ ተቋማችንን ለመስራቾች አስረክቦ ሐገርም ሰላም ትሆን ዘንድ እንደ ጀመረው ሁሉ መፍትሄ መስጠት ግዴታ ነው።
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

/Ustaz Hasen Taju https://t.me/hassentajuሸፍጥና ዉሸት በየትኛዉም ቦታና ሁኔታ የእኩይ ስብዕናዎች መገለጫ ቢሆንም በሀይማኖት መስክ ሲሆን የበለጠ ያሳቅቃል፡፡ የአፈንጋ...
05/11/2025

/Ustaz Hasen Taju https://t.me/hassentaju
ሸፍጥና ዉሸት በየትኛዉም ቦታና ሁኔታ የእኩይ ስብዕናዎች መገለጫ ቢሆንም በሀይማኖት መስክ ሲሆን የበለጠ ያሳቅቃል፡፡ የአፈንጋጭ አስተሳሰብ ባለቤቶች እምነታቸዉን ለማጽናት ከሚጠቀሙባቸዉ ስልቶች መካከል አንዱ በታላላቅ ስብእናዎች ስም መጽሀፍና አባባሎችን መፈብረክ ወይም የታዋቂ ሰዎችን መጽሀፍት መበረዝና መከለስ ነዉ፡፡ ከስነምግባርና ከታማኝነት መርሆዎች ዉጭ የሆነዉ ይህ መንገድ ከሀይማኖቶች ይልቅ ከግብረገብ ከተፋቱ የፖለቲካ አይዲዮሎጂዎች ጋር ያመሳስላቸዋል፡፡

የጥንቶቹ አፈንጋጮች በኢማም አህመድ እብን ሀንበል ስም መጽሀፍትና አባባሎች ፈብርከዉ ማሰራጨታቸዉ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸዉ፡፡ ‹‹አርረድ ዐለል ጀህምያ ወዝዘናዲቃ›› እና ‹‹ሪሳለቱል እስጦኽሪ›› የተሰኙ ኪታቦች በታላቁ ሰዉ ስም ተፈብርከዉ ተሠራጭተዋል፡፡ ኢማም ዘሀቢ ስለኢማም አህመድ አንድ ድርሳን ሲተነትኑ እግረ መንገድ የሁለቱን መጽሀፍት ቅጥፈትነት አስምረዋል፡-

لاَ كَرِسَالَةِ الإِصْطَخْرِيِّ ، وَلاَ كَالرَّدِّ عَلَى الجَهْمِيَّةِ المَوْضُوْعِ عَلَى أَبِي عَبْدِ الله

‹‹በአቡ ዐብደላህ ላይ እንደተቀጠፉባቸዉ ‹ሪሳለቱል እስጦኽሪይ›› እና ‹አርረድ ዐለል ጀህምያ› መጽሀፍት (ይህኛዉ የተቀጠፈ አይደለም)፡፡››[1]

የዑለሞችን ሥራዎች የመበረዝና የመከለስ፣በነርሱ ስም ኪታብ የማተምና የማጭበርበር ልምምድ ወደሀገራችን ተዛምቶ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የተዘጋጀዉ የቅዱስ ቁርአን ትርጉም ተመሳሳይ ወንጀል ተፈጽሞበታል፡፡ በተለይም ወንጀሉ ያተኮረዉ ‹ሲፋቱል ኸበርያ› በሚል ስያሜ በሚታወቁ በአሻሚ የቁርአን ገለጻዎች ላይ ሲሆን፣ በሀገራችን ለምዕተ ዓመታት ሲሰጥ የኖረዉን የአህሉሱና ዐቂዳ መሠረት በማድረግ የተተረጎሙ አንቀጾችን ይዘት በመቀየር ጣኦታዊ ቃና እንዲላበሱ ተደርጎ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የተጅሲም ጣኦታዊነት አቀንቃኝ ተደርገው ተስለዋል። የዚህ ቅጥፈትና ሸፍጥ ባለቤት ‹‹ዳሩ ሰላም አሳታሚና አከፋፋይ›› የተባለ በሳዉዲ ዐረብያ ሪያድ የሚገኝ ድርጅት ነዉ፡፡ የሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብንና የሸኽ ሰይድ ሷዲቅን ስም ተጠቅሞ ባሳተመዉ ‹‹የክቡር ቁርአን መልዕክተ-ትርጉም›› የተሰኘ መጽሀፍ[2] ዉስጥ የበርካታ አንቀጾችን ትርጉም በማዛባት በሸኽ ሙሀመድ ሳኒና በባልንጀሮቻቸዉ ላይ ቅጥፈት ፈጽሟል፡፡ ጥቂት ናሚናዎችን ለማሳየት ያህል፡-

1. ‹‹ዐለል ዐርሽ እስተዋ›› ለሚለዉ ሀረግ ሁለቱ ሊቃዉንት በሁሉም ቦታዎች የሰጡት ትርጉም ‹‹(ልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ›› የሚል መሆኑ ይታወቃል፡፡[3] ይህ ማለት ሁለቱ ሊቃዉንት ለአላህ የመኖሪያ አድራሻና አቅጣጫ ከመስጠት ታቅበዋል ማለት ነዉ፡፡ የትርጉማቸዉ መነሻ የሰለፉ የቁርአን ተንታኝና የተፍሲር ሊቃዉንት ሸኽ የሆኑት የኢማም እብኑ ጀሪር ጦበሪ (እስከ 310 ዓ፣ሂ) ተከታዩ አፈታት መሆኑ ግልጽ ነዉ፡-

علا عليها علوّ مُلْك وسُلْطان، لا علوّ انتقال وزَوال

‹‹በርሷ ላይ የመንቀሳቀስና ስፍራ የመልቀቅ ሳይሆን የንግስናና የስልጣን ከፍታን ከፍ አለ፤››[4]

ጦበሪ ለዚህ አፈታት መሠረት ያደረጉት "ዐላ ወርተፈዐ" የሚለውን የታቢእ ትውልድ ተፍሲር መሆኑ ከኪታባቸው ውስጥ ተመልክቷል። ዳሩ ሠላም ማተሚያ ግን -መነሻዉ ምንም ይሁን ምን- የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒን ትርጉም በየስፍራዉ እየተከታተለ በመለወጥ አጭበርብሯል፡፡ ይህ ተቋም ለዚህ ገለጻ በየቦታዉ ያሰፈረዉ መልእክት እንዲህ ይላል፡-

‹‹ከዐርሹ በላይ ሆነ፤(የርሱን ክብር በሚመጥን መልኩ)፤››[5]

በቀሪዎቹ ተመሳሳይ አንቀጾች ላይም ተመሳሳይ ሸፍጦች ፈጽሟል፡፡ ለአልአዕራፍ 54፣ ለአርረዕድ 2፣ለጦሀ 5፣ለአልፉርቃን 59፣ለአስሰጅዳህ 4 እና ለአልሀዲድ 4 የተሰጡ ትርጉሞችን ከገጽ 226፣352፣445፣521፣594 እና 785 ላይ ይመልከቱ፡፡ የዚህ ጽሁፍ አላማ ሸፍጥና ማጭበርበርን ማሳየት እንጅ ከሁለቱ አስተሳሰቦች የትኛዉ ትክክል ነዉ? ለሚለዉ ጥያቄ መልስ መስጠት አይደለም፡፡ እርሱን የተመለከተ ሰፊ ሥራ ‹‹አል-ዑሉዉ›› በሚል ርእስ የተዘጋጀ በመሆኑ ከዚያ ላይ በስፋት የምታገኙት ይሆናል፡፡

2. አልሙልክ 16ን እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ የፈሰሩት እንደሚከተለዉ ነዉ፡-

‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለን (ሠራዊት) በናንተ ምድርን ቢደራርብባችሁ ወዲያዉም እርሷ የምታረገርግ ብትሆን ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?)››

ዳሩ ሰላሞች ግን ‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለን (ሠራዊት)›› የምትለዋን ክፍል ቆርጠዉ በማዉጣት፡- ‹‹በሰማይ ዉስጥ ያለዉ (አላህ) በምትል ሀረግ ተክተዋታል፡፡[6]

በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ግንዛቤ መሠረት ለአላህ ቦታና አቅጣጫ መስጠት እርሱን ከፍጡራን ጋር ማመሳሰልና የቦታና የአቅጣጫ ከጃይ ማድረግ ስለሆነ አግባብ ባለመሆኑ ‹‹በሰማይ ዉስጥ›› የተባሉት ‹‹የአላህ ሠራዊት ወይም መላእክት›› እንጅ አላህ አይደለም፡፡ ይህን አፈታት የቀዱት ከተዉሂዱ ሊቅ ከኢማም ማቱሪዲ (እስከ 333 ዓ.ሂ)፣ እንዲሁም ከኢማም ቁርጡቢ፣ከኢማም ጀላሉዲን ሱዩጢ፣ ከኢማም መሀሊና መሰል የቁርአን ትንታኔዎች መሆኑ እሙን ነዉ፡፡[7]

በዳሩ ሰላሞች ዐቂዳ መሠረት ደግሞ አላህ ከሰማየ ሰማያት በላይ መሆኑ የእምነታቸዉ መሠረት ነዉ፡፡ እንደፈለጉ ማመን መብታቸዉ ሆኖ እምነታቸዉን በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ስም ማሰራጨት ግን በዕዉቀት ላይ የተፈጸመ ሸፍጥ ነዉ፡፡

3. ‹‹ዐይን›› የሚለዉ ቃል ከአላህ ጋር ተያይዞ በተገለጸባቸዉ ቦታዎች ሁሉ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹ጥበቃ/እንክብካቤ›› በማለት ከአካል ክፍልነት ዉጭ የተረጎሙት ሲሆን የዕምነታቸዉ መሠረት ለአላህ የአካል ክፍሎችና ቅርጽ ማላበስ ጣኦታዊነት በመሆኑ የሚጸየፈዉ የሰለፎች አስተሳሰብ ነዉ፡፡ ኢማም አቡሀኒፋ (እስከ 150 ዓ.ሂ) የሚከተለዉን ዐቂዳ አስተምረዋል፡-

الثَّابِت بِلَا جسم

‹‹(አላህ) ያለ ‹ጅስም… ህልዉናዉ የጸና አምላክ ነዉ፡፡››[8]

ጅስም ማለት ከተለያየዩ የአካል ክፍሎች የተዋቀረ ነገር ማለት ነዉ፡፡[9]

ኢማም ጦሀዊ (እስከ 321 ዓ.ሂ) በርሳቸዉ ዘመንና ከርሳቸዉ በፊት የነበረዉን የሰለፍ አህሉሱና ዐቂዳ ሲያብራሩ ፡-

وَتَعَالَى عَنِ الْحُدُودِ وَالْغَايَاتِ وَالْأَرْكَانِ وَالْأَعْضَاءِ وَالْأَدَوَاتِ

‹‹/አላህ/ ከገደብና ወሰን፣ከአካል ክፍሎችም (ዉቅርነት) የጸዳ ነዉ፤››[10]

በነዚህ ሁለት የሰለፍ ሊቃዉንት የዐቂዳ ትምህርት መሠረት የትኛዉም የቁርአን አንቀጽ በዚህ አግባብ ለአላህ አካላዊ ቅርጽነና ይዘት ከማላበስ በጸዳ መልኩ መፈሰር አለበት ማለት ነዉ፡፡ እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ከዚህ የሰለፎች ዐቂዳ በመነሳት ይህንና መሰል አንቀጾችን ከአካላዊ ቅርጽና ገጽታ ዉጭ በሆነ መልኩ የፈቱበት መንገድ ከእብን ዐባስ[11] ቀታዳ[12] ቁርጡቢ[13] ነሰፊም[14] በይዷዊ[15] በገዊ[16] እብን ዐጥያ[17] እና ሌሎች የተፍሲር ሊቃዉንት ገለጻዎች የተቀዳ ነዉ፡፡

ዳሩሰላም የተሰኘዉ ተቋም ግን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን ከአካል ክፍልነት የጸዳ ፍች ቀይሮ ‹‹አይን›› በማለት አካላዊ ትርጉም አላ በነዚህ ዑለሞች ስም አሰራጭቶታል፡፡[18]

4. እነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹የዱ ላህ›› እና መሰል ገለጻዎችን የአካል ክፍል በመምሰል ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣዉንና ከዑለሞቻቸዉ የተማሩትን ዐቂዳ የሚጻረር መስሎ በተሰማቸዉ ቦታ ሁሉ ላይ ‹‹የአላህ ሀይል›› ወይም ‹‹እጅ›› ብለዉ በቅንፍ ዉስጥ ‹‹ሀይል›› በማለት ከአካል ክፍል በራቀ መልኩ የተረጎሙት ሲሆን[19] የዳሩሠላም እትም ግን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒን ዐቂዳ ለማጽናት እጅግ ጠቃሚ የሆኑትን በቅንፍ ዉስጥ የተቀመጡ ቃላት በማስወገድ ይዘቱ አካላዊ ገጽታ እንዲላበሱ አድርጓል፡፡[20]

5. ‹‹የሚን›› የሚለዉ ቃል ከአላህ ጋር ተገናኝቶ ሲመጣ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ‹‹ሀይል›› ተብሎ የተተረጎመ ሲሆን በዳሩ ሰላም ተቋም ግን ‹‹ቀኝ እጁ›› በሚል ተተክቶ የአካል ክፍል ምስል እንዲይዝ ተደርጓል፡፡[21]

አላህን ከተለያዩ የአካል ክፍሎች የተዋቀረ የሚያስመስሉት የቁርአንና የሀዲስ መልእክቶች በምን አግባብ መቃኘት እንዳለባቸዉ የሚያሳይና ከዚህ ዉጭ በሆነ አፈንጋጭ አቅጣጫ የተደረገዉ የአስተሳሰብ ጉዞ በእስልምና ላይ የለጠፈዉን ነዉር የሚተነትን ‹አል ወሰንያ-በእስልምና ስም የተስፋፋ ጣኦታዊነት›› በሚል ርእስ መጽሀፍ የተዘጋጀ በመሆኑ በቅርቡ ከአንባብያን እጅ የሚገባ ይሆናል፡፡ በመስኩ የተስተዋሉ ብዥታዎችን ያጠራል ተብሎ ይታመናል፡፡

ዳሩ ሰላም በተሰኘዉ ድርጅት አማካይነት በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ የቁርአን ትርጉም ላይ የተፈጸሙ ማጭበርበሮች በርካታ ቢሆኑም ለአብነት ያህል ከላይ የተዘረዘሩት በቂ ናቸዉ፡፡ የማጭበርበሩ ዓላማ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን የቁርአን ትርጉም እነርሱ ከሚያምኑበትና ከኖሩለት የዐቂዳ አስተሳሰብ ዉጭ የሆነ ገጽታ በማላበስ ማህበረሰብን ማደናገርና ስሁት አስተሳሰቦችንና ዐቂዳዎችን በታላላቅ ስብእናዎቻችን ስም ማሰራጨት ነዉ፡፡

ከዉስጥ ከተደረጉ በርካታ ለዉጦችና ማጭበርበሮች በተጨማሪ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ያልሆነ 45 ገጽ ያህል የመግቢያ ሀተታ፣እንዲሁም በየገጹ የነርሱን ዕምነት የሚጻረሩ[22] የግርጌ ማስታወሻዎች ተጨምረዉበታል፡፡[23] ሀተታዉ የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን እምነት (ዐቂዳ) የሚጻረር የተዉሂድ ግንዛቤን፣የሸሀዳን ትርጉም፣የኩፍር፣የሽርክና የኒፋቅ ትንታኔዎችን፣እንዲሁም የእየሱስን ማንነትና ተመልሶ መምጣት፣ነብዩ ሙሀመድ በመጽሀፍ ቅዱስና የስቅለት ጉዳይን የተመለከቱ ጭብጦች ተካተዉበታል፡፡ ሀተታዉም ሆነ የግርጌ ማስታወሻዎች ዕዉነትን ከግድፈት የቀላቀሉ ሲሆን፣ መጀመሪያዉኑ በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ሥራ ዉስጥ መካተት አልነበረባቸዉም፡፡ መካተታቸዉ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም የአሳታሚ ድርጅቱ ወይም የሌሎች ግለሰቦች ሀሳቦች መሆናቸዉ በማያሻማ ሁኔታ መገለጽ ነበረበት፡፡ ይህ ሳይደረግ መቅረቱ አንባብያን ሀተታዉንና የግርጌ ማብራሪያዎችን የነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ዕምነትና ሀሳብ አድርገዉ እንዲቆጥሩ እድል ከፍቷል፡፡ ይህ ደግሞ በነኝህ ሊቃዉንት ስም የነርሱ ያልሆነን ሀሳብ በማሰራጨት ማጭበርበር ይሆናል፡፡

በጥቅሉ መጽሀፉም ሆነ ድርጅቱ፣ እንዲሁም መሰል ድርጅቶች ዕምነት የማይጣልባቸዉ ሸፍጠኞች በመሆናቸዉ አስፈላጊዉ ሁሉ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ በዚህ አጋጣሚ ማሳሰብ እወዳለሁ፡፡ የዚህን የቁርአን ትርጉምና የተፈጸሙበትን ሸፍጦች በሙሉ ነቅሶ በማዉጣት በታላላቅ ዑለሞቻችን ስም ነዉሮችና አፈንጋጭ አስተሳሰቦች እንዳይሰራጩ መከላከልና ማህበረሰቡን ማስጠንቀቅ ተገቢ ነዉ፡፡

በሌሎች መጽሀፍት ላይ በተለያዩ ድርጅቶች፣በተለይም መክተበቱ ሻሚላ በተሰኘዉ አፕሊኬሸን አማካይነት የተፈጸሙ ሸፍጦችን ወደፊት የምናይ ይሆናል፡፡ ለማንኛዉም ‹ዳሩ ሰላም› ያለዉ ምርጫ ሁለት ነዉ፡፡ አንደኛዉ ያለአግባብ የለወጣቸዉን አንቀጾች ወደነበሩበት መልሶ መጽሀፉን በነሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብ ስም ማሳተም ወይም የነርሱን ስመ ሰርዞ የራሱን አዲስ የትርጉም መጽሀፍ ማሳተም፡፡ አሁን ያለዉ ይዘቱና ድርጊቱ ግን በሰዎች ስም የማያምኑበትን ዐቂዳና አስተሳሰብ የማሰራጨት ወንጀልና በህግ የሚያስጠይቅ አጭበርባሪነት መሆኑ ጥርጥር የለዉም፡፡ አስተሳሰብን በጠንካራ መረጃዎች እንጅ በሸፍጥና ጭበርበር ለማሰራጨት ከመሞከር የበለጠ የሀሳብ ምክነት የለም፡፡

[1] ሸምሱዲን ዘሀቢ፣ሲየር አዕላመ ኑበላእ፣ሙአሰሰቱ ሪሳላ፣ሁለተኛ ዕትም 1985፣ካይሮ፣ 11/286-287

[2] የመጀመሪያ እትም በፈረንጆች 2010

[3] ለአልአዕራፍ 54፣ዩኑስ 3፣አርረዕድ 2፣ጦሀ 5፣አልፉርቃን 59፣አስሰጅዳ 4 እና አልሀዲድ 4 የተሰጡ ትርጉሞችን ይመልከቱ፤

[4] ያለፈዉ ምንጭ

[5] ለዩኑስ 3 የተሰጠ ትርጉም ገጽ 295

[6] ገጽ 821 ለአንቀጹ የተሰጠዉን ትርጉም ይመልከቱ፤

[7] ተፍሲር ማቱሪዲ 10/117፣ተፍሲር ቁርጡቢ 18/215፣ተፍሲር ጀላለይን ገጽ 756

[8] ፊቅሁል አክበር ገጽ 4

[9] አልእቅቲሳድ ፊልእዕቲቃድ ሊልገዛሊ ገጽ 33

[10] ዐቂደቱ ጦሀዉያ ገጽ 5

[11] ተፍሲር እብን ከሲር 4/349

[12] ተፍሲር ቁርጡቢ 11/197

[13] ያለፈዉ ምንጭ 11/196

[14] ተፍሲር ነሰፊ 2/364

[15] ተፍሲር በይዳዊ 4/27

[16] ተፍሲር በገዊ 5/272

[17] ተፍሲር እብን ዐጥያ 4/44

[18] ለጦሀ 39፣ሁድ 37 እና አጥጡር 48 የተሰጡ ትርጉሞችን ገጽ 447፣319፣762 በቅደም ተከተል ይመልከቱ፤

[19] አልፈትህ 10፣ሷድ 75፣ያሲን 71 ለአብነት ይመልከቱ፡፡

[20] ለአልፈትህ 10፣ሷድ 75፣ያሲን 71 የተሰጡ ትርጉሞችን ገጽ 740፣659፣638 ይመልከቱ

[21] ለአዝዙመር 67 የተሰጠዉን ትርጉም ገጽ 671 ይመልከቱ፤

[22] ለምሳሌ ገጽ 804 ህዳግ ቁጥር 1 ይመልከቱ፤

[23] የላቲን ቁጥር ገጽ22-67

 ታሪካችንን ለማያውቅ፣እምነታችን እምነቱ ላልሆነ ስብስብ ለፖለቲካ ፍጆታ ተብሎ በግድ መኖር ጭቅጭቅና ጸብ እንጅ ሰላምን አያመጣም።በመሆኑም ኦርቶዶክስና ፕሮቲስታንት በስመ-ክርስትና አብረው እ...
31/10/2025



ታሪካችንን ለማያውቅ፣እምነታችን እምነቱ ላልሆነ ስብስብ ለፖለቲካ ፍጆታ ተብሎ በግድ መኖር ጭቅጭቅና ጸብ እንጅ ሰላምን አያመጣም።በመሆኑም ኦርቶዶክስና ፕሮቲስታንት በስመ-ክርስትና አብረው እንዳልሆኑ ሁሉ እኛና ውሀብይ በአንድ ተቋም ስር መሆን የሚያስችል ቁመና ስለሌለን ሁለት መጅሊስ አይነተኛ መፍትሄ ነው።

መፍትሄ ማንም ስለ ማንም ሀይማኖት የማይመለከተው፣በምርጫ ስም ማጭበርበር የሌለበት፣በህገ-መንግስቱም እንኳን ይህን ያክል ጉምቱ ታሪክ፣ተቋም መስርቶ የማስተዳደር አቅም ላለው ሙስሊም ቀርቶ በአጭር ጊዜ ከውጭ ሀይማኖታቸውን አምጥተው እውቅና ተሰጥቶ በሰላም እየኖሩ ላሉትም ትልቅ የሰላም ስኬት ተመዝግቦበታል።

በእኛ እና በስመ-አንድነት የተጠለለው የውሀብይ ቡድን መቸም የማይታረቁ የአቂዳ ልዩነቶች ያሉን፣የእምነት አተገባበርና ረጅም ጊዜ የቆየ የመሪነት ሚና፣ያለ ኮሽታ ሀገር እስከ ሀገር የምንታወቅበት ሀይማኖታዊ በአል ያለን፣ውሀብይ ከመጣ ጀምሮ የሙስሊሙ እስከማይመስል በውስጥ ባለ ጠላት ፕሮፓጋንዳ መውሊድ ከበአልነት ይሰረዝ የሚሉ ጽንፈኞች፣የእስልምና መሰረታዊ እምነት መርሆ የሆኑትን ሽርክ ብለው ራሳቸውን አማኝ፣ሌላውን ኢ-አማኝ የሚያደርጉ ስብስቦች ጋር አብሮ የሚያስቀጥል አንዳችም ምክንያት ስለሌለን መብታዊ፣ሰላማዊ ፣ሐይማኖታዊ ህገ-መንግስያዊ መብታችንን ማስከበር እና ሁለት_መጅሊስ መፍትሄ አሁኑኑ ይተግበር።
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA

Address

Sydney, NSW

Telephone

+966593278284

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዲን ወታደር Ye din wetader posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የዲን ወታደር Ye din wetader:

Share