Tewahedo World

Tewahedo World Ethiopian Orthodox Church Network

በስመ አብ ወ ወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጆች በዚህ ገጽ ተሰብሰቡ:: መዝሙሮችን እና ስብከቶችን እንዲሁም በየከተማው የሚደረጉ መርሃግብሮችን በዚህ ገጽ እናካፍላችኋለን:: ሼር እና ላይክ በማድረግ ይህን ገጽ ያስተዋውቁልን::

08/26/2026

ዋዜማ ራድዮ እንደዘገበው፣ የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት፣ የተለየ ፍላጎት አላቸው ያላቸው አካላት ሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ የመድሃኒአለም ቤተክርስቲያን ያስገነባውን መቃኞ ማፍረሳቸውን ኮነነ። የድርጊቱ ፈጻሚዎች "የሐይማኖት ጸብ" ለማስነሳትና የክልሉን መልካም ገጽታ ለማጠልሸት ሞከረዋል በማለት የወነጀለው የክልሉ መንግሥት፣ ፖሊስ የድርጊቱን ፈጻሚ አካላት በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ መጀመሩን ገልጧል። መቃኞው የተገነባበት ቦታ፣ በግለሰብ ስም የተመዘገበ ይዞታ መኾኑን ማረጋገጡንም የክልሉ መንግሥት ጠቅሷል።

"እመብርሃን ከጎኔ ናት!... Thank you, God, for guiding me, protecting me, and reminding me that my story is still unfolding beau...
08/24/2026

"እመብርሃን ከጎኔ ናት!... Thank you, God, for guiding me, protecting me, and reminding me that my story is still unfolding beautifully." ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ሩት ይርጋለም

ተዋሕዶ ወርልድ |  በኢትዮጵያ ረጅም ታሪክ ውስጥ፣ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት ተቋም ብቻ ሳትሆን፣ የሀገር ምሰሶ፣ የታሪክ ማህደር እና የማንነት መገለጫ ሆና ኖራለች። ነገ...
08/24/2026

ተዋሕዶ ወርልድ | በኢትዮጵያ ረጅም ታሪክ ውስጥ፣ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት ተቋም ብቻ ሳትሆን፣ የሀገር ምሰሶ፣ የታሪክ ማህደር እና የማንነት መገለጫ ሆና ኖራለች። ነገር ግን፣ ይህች ጥንታዊት እና ክብርት ቤተክርስቲያን፣ ዛሬም እንደ ትላንቱ፣ በተለያዩ አቅጣጫዎች የሚሰነዘሩባት ከባድ ፈተናዎች እና መከራዎች አላባሩም።

በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በተደራጁ ሰዎች ጥቃት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን የሶማሌ ሀገረ ስብከት አስታወቀ።

ሀገረ ስብከቱ ይህን አሳዛኝ ድርጊት የሚያሳይ እና የሕንጻ መቅደሱ ሙሉ በሙሉ ሲወድም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል በይፋዊ ገጹ ላይ አጋርቷል። ጥቃቱ በማንነታቸው ባልታወቁ ነገር ግን 'የተደራጁ' ባላቸው አካላት መፈጸሙንም አረጋግጧል።

ይህንን አሳሳቢ እና ህገ-ወጥ ድርጊት ተከትሎ፣ የክልሉ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት በአስቸኳይ ጣልቃ በመግባት ህግና ስርዓት እንዲያስከብሩ እንዲሁም አጥፊዎችን ለፍርድ እንዲያቀርቡ ሀገረ ስብከቱ ጥብቅ ጥሪ አቅርቧል።

በቅርቡ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ህንፃ መቅደስ በተደራጁ አካላት ሙሉ በሙሉ ፈርሷል በሚል በሶማሌ ሀገረ ስብከት በኩል የተገለጸው ዜና፣ የዚህ ተከታታይ መከራ አንድ ማሳያ ነው። ይህ ድርጊት፣ የአንድን ህንፃ መፍረስ ብቻ ሳይሆን፣ የአንድን ጥንታዊ እምነት ተከታዮች ልብ የሰበረ እና የሃይማኖት ነጻነት መብትን በጽኑ የፈተነ ክስተት ነው።

የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ውስጥ እያለፈችበት ያለው መንገድ እጅግ ፈታኝ ነው። በአንድ በኩል፣ የዘመናት ቅርሶቿ፣ አድባራት እና ገዳማቷ ሆን ተብሎ በሚሰነዘርባቸው ጥቃቶች ሲወድሙ እና ሲቃጠሉ ይታያል። በሌላ በኩል ደግሞ፣ ምእመናኖቿ እና አገልጋዮቿ በእምነታቸው ምክንያት ብቻ ለእንግልት፣ ለመፈናቀል እና ለሞት ሲዳረጉ ማየት የዘወትር ዜና እየሆነ መጥቷል።

ይህ ሁሉ መከራ ሲፈራረቅባት ቤተክርስቲያኒቱ ግን እንደቆመችበት ጽኑ መሰረት፣ ዛሬም በፍቅር፣ በትዕግስት እና በይቅርታ ጥላ ስር ቆማለች። መከራው እሳቷን ሊያጠፋው ቢሞክርም፣ እሷ ግን እንደ ወርቅ በእሳት እየተፈተነች፣ ይበልጥ ደምቃ እና ጸንታ ትወጣለች እንጂ አትጠፋም።

የቤተክርስቲያኒቱ እና የምእመናኗ ጥያቄ አንድ እና ግልጽ ነው፡- በገዛ ሀገራቸው በነጻነት እና በሰላም አምልኮታቸውን መፈጸም፣ እንዲሁም ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ተቋሞቻቸው በመንግስት እና በህግ የተሟላ ከለላ እንዲያገኙ ነው። የጅግጅጋው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መፍረስ፣ ህግ እና ስርዓት እንዲከበር፣ እንዲሁም ለዘመናት አብሮ የኖረው የኢትዮጵያውያን የመከባበር እሴት እንዳይሸረሸር ጮክ ብሎ የሚጠይቅ የደወል ድምጽ ነው።

ፈተናው ቢበዛም የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በጸሎት፣ በጽናት እና በእምነት ጉዞዋን አታቋርጥም። እያንዳንዱ የሚፈርስ ጡብ፣ የጽናት መሰረቷን ይበልጥ ያጠነክረዋል እንጂ አያዳክመውም። መንግስትም ሆነ ህብረተሰቡ፣ ይህንን ታሪካዊ ተቋም የመጠበቅ እና የሁሉንም ዜጎች የሃይማኖት ነጻነት የማረጋገጥ ታሪካዊ እና ህገ-መንግስታዊ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል።

08/22/2026

እንኳን አደረሳችሁ!...

እንጦጦ ኪዳነምህረት የናፈቀቻችሁ ይህችን የአንድ ደቂቃ ቪድዮ ተመልከቱ
08/20/2026

እንጦጦ ኪዳነምህረት የናፈቀቻችሁ ይህችን የአንድ ደቂቃ ቪድዮ ተመልከቱ

በመንገዳችን ላይ... እንጦጦ ሐመረኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም - አዲስ አበባ ...

🔥 የቡሄ በዓል ልዩ ድምቀት! ይህ የደመቀ ብርሃን የሰላም እና የፍቅር ብርሃን ይሁንልን
08/19/2026

🔥 የቡሄ በዓል ልዩ ድምቀት! ይህ የደመቀ ብርሃን የሰላም እና የፍቅር ብርሃን ይሁንልን

When the Buhe Chibo (torch) lights up... our hearts fill with nosta...

የቡሄ ብርሃን ሲፈነጥቅ… ልባችን በናፍቆትና በደስታ ይሞላል!
08/19/2026

የቡሄ ብርሃን ሲፈነጥቅ… ልባችን በናፍቆትና በደስታ ይሞላል!

When the Chibo is lit... 🔥 The true magic and warmth of Buhe! May t...

በገዳማትና በአምልኮ ሥፍራዎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በጽኑ ያወገዙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ አጥፊዎች በአስቸኳይ ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ
07/25/2026

በገዳማትና በአምልኮ ሥፍራዎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በጽኑ ያወገዙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ አጥፊዎች በአስቸኳይ ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሴኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች ውስጥ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ ከተከናወነው ጥቃት ጋር ተያይዞ ከ53 በላይ ሰዎች መገደላ...
07/24/2026

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሴኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች ውስጥ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ ከተከናወነው ጥቃት ጋር ተያይዞ ከ53 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና ሰፊ ውድመት መድረሱን የሚገልጹ ዘገባዎች ወጥተዋል። ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ ወር ድረስ በዘለቀው በዚህ የታጠቀ ቡድን ጥቃት ሳቢያ በርካታ ሰላማዊ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ መኖሪያ ቤቶች እና የእምነት ተቋማትም የቃጠሎና የጉዳት ሰለባ ሆነዋል።
በአሴኮ ወረዳ በቴሌታ ጨፋ፣ ባቲ እና ካራፈኒሳ ቀበሌዎች በተካሄደው በዚህ ጥቃት ከ200 በላይ መኖሪያ ቤቶች በእሳት የወደሙ ሲሆን፣ ከ150 በላይ ከብቶችም ተዘርፈዋል። በተጨማሪም የ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የቴሌታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት እንዲቃጠል ተደርጓል። በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ከ280 በላይ ቤተሰቦች (ወደ 1,500 የሚጠጉ ሰዎች) በሱልጤ ቅድስት ማርያም እና በእሬቻ ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ ሌሎች በርካታ ተፈናቃዮች ደግሞ ወደ አርባጉጉ ደን በመሸሽ በከፍተኛ ስጋትና እንግልት ውስጥ ይገኛሉ።

የብፁዕ አቡነ ኤልያስን መግለጫ እና የማኅበረ ቅዱሳን ዘገባን ዋቢ በማድረግ እንደተገለጸው፣ ጥቃቱ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች የሆኑ ቤተሰቦችን በተለየ መልኩ ኢላማ ያደረገ ነው። በብዙዎች ዘንድ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይነትን ከአማራ ብሔር ጋር ብቻ አያይዞ የመመልከት የተሳሳተ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በዕውነታው ግን የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ከኦሮሞ፣ ከትግራይ፣ ከጉራጌ እና ከሌሎችም በርካታ ብሔረሰቦች የተወጣጡ ናቸው። አሁን እየታየ ያለው ጥቃት የሃይማኖትና የብሔር ማንነትን መሠረት ያደረገ በመሆኑ፣ በሕዝቦች መካከል ያለውን አብሮ የመኖር ባህል እንደሚያደፈርስና የከፋ የሃይማኖት ግጭት ሊቀሰቅስ እንደሚችል የሃይማኖት መሪዎች አስጠነቅቀዋል።

በአካባቢው ከዚህ ቀደምም መሰል ጥቃቶች በተደጋጋሚ የተፈጸሙ ሲሆን፣ የቴሌታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከሰባት ጊዜ በላይ ጥቃት እንደተሰነዘረበትና በ2017 ዓ.ም 25 ሰዎች፣ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በሽርካ ወረዳ 21 ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸው ይታወሳል። ነዋሪዎችና የአካባቢው አመራሮች የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በወቅቱ ደርሰው ጥቃቱን እንዲያስቆሙ አቤቱታ ቢያቀርቡም፣ የፌዴራልም ሆነ የክልሉ የጸጥታ አካላት በቂና ፈጣን ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል በሚል ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

እስካሁን ድረስ ከፌዴራልም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በይፋ የተሰጠ መግለጫ አለመኖሩ በሕዝቡ ዘንድ ጥርጣሬንና አለመመካመንን ያባበሰው ሲሆን፣ ታማኝና ገለልተኛ ምርመራ እንዲካሄድ ጥሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ። የአካባቢውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ፣ ሰላማዊ ዜጎችን ከአደጋ ለመጠበቅ፣ ለተፈናቃዮች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እና ጥቃቱን የፈጸሙትን አካላት ለሕግ ለማቅረብ መንግሥት በአስቸኳይ ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ተላልፏል።

የገዳሙ ሰቆቃ፡ በጸሎት እና በሥራ መሃል የወረደው ድንገተኛ መቅሰፍትበአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ ውስጥ በአባይ ወንዝ ዳርቻ የሚገኘው የአባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊ እ...
07/23/2026

የገዳሙ ሰቆቃ፡ በጸሎት እና በሥራ መሃል የወረደው ድንገተኛ መቅሰፍት

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ ውስጥ በአባይ ወንዝ ዳርቻ የሚገኘው የአባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊ እና የቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም፤ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደተለመደው በጸሎት፣ በዝማሬ እና በመንፈሳዊ እርጋታ ተጀምሮ ነበር። ክረምቱን በሰላም ለመሻገር በማሰብ የገዳሙ እናቶች (መነኮሳይት) ከገዳሙ ዛፍ ሥር ተሰባስበው የክረምት እህል በማዘጋጀት እና በመልቀም ላይ ነበሩ። የጠዋቱ ፀሐይ ሞቅ እያለች ስትመጣ፣ ሰላማዊው የገዳሙ ድባብ በቅጽበት ወደ አስፈሪ የሞት ቀጠናነት ይቀየራል ብሎ ያሰበ ማንም አልነበረም።

እማሆይ ወለተ ማርያም ሌላ ሥራ ለመሥራት ከእናቶቹ ተለይተው ጥቂት እርምጃዎችን እንደተራመዱ ነበር ያ ጆሮ የሚያደነቁር እና መለየት ያቃታቸው አስፈሪ የፍንዳታ ድምፅ የተሰማው። ልባቸው በድንጋጤ እየመታ "ወዮ!" እያሉ ወደ ኋላ ሲመለሱ ያዩት ትዕይንት ለዘለዓለም ከህሊናቸው የሚፋቅ አልነበረም። አብረዋቸው ሲስቁና እህል ሲለቅሙ የነበሩት እናቶች በየቦታው ተዘርረው ራሳቸውን ስተዋል፤ ደም የለበሱት የገዳሙ ልጆችም በከፍተኛ ድንጋጤ እያለቀሱ ይሯሯጡ ነበር። እማሆይ ወለተ ማርያም በጭንቀት ውስጥ ሆነው የቆሰሉትን እናቶች ወደ ጥግ እየጎተቱ፣ ሕይወታቸውን ለማትረፍ ደማቸውን ለማስቆም ያደረጉት ጥረት የዕለቱን አሰቃቂነት በግልጽ ያሳያል።

የድሮን ጥቃቱ በቀጥታ ያረፈው በሴቶች መነኮሳይት መኖሪያ እና የሥራ ስፍራ አካባቢ ላይ ነበር። የገዳሙ አስተዳዳሪ አባ ኤልያስ ተሻገር በሐዘን በተሰበረ አንደበት እንደሚያስረዱት፣ በዚሁ አደጋ በአጠቃላይ በ14 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ከእነዚህም መካከል የስድስቱ እናቶች አካል በፍንዳታው ክፉኛ ተቆራርጦ ነበር።

የሁለቱ እናቶች ሕልፈት ግን የገዳሙን ማኅበረሰብ ልብ ክፉኛ ያደማ ነበር። አንደኛዋ እናት ጥቃቱ እንደተፈጸመ እዚያው እህል ሲለቅሙበት በነበረው ዛፍ ሥር ወዲያውኑ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ስትለይ፣ ሁለተኛዋን እናት ግን ነፍስ ይደርስላቸው እንደሆነ በሚል ተስፋ ወደ መካነ ሰላም ሆስፒታል ይዘዋቸው ገሰገሱ። ሆኖም መቅደላን አልፈው 'ሰኞ ገበያ' ከምትባለው መንደር ላይ ሲደርሱ እሳቸውም በደረሰባቸው ከባድ ጉዳት ሕይወታቸው አለፈች።

አባ ወልደ ሚካኤል የዚያን ቀን ጠዋት ከሰማይ ሲሰማ የነበረውን አስፈሪ የሞት ድምፅ ያስታውሳሉ። ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ በአካባቢው ላይ ስትሽከረከር የነበረችው ድሮን፣ አራት ሰዓት ሲሆን ድምጿን አጥፍታ ድንገት መዓቷን አወረደች። በአካባቢው ላይ ከገዳሙ ውጪ የራሳቸው ኬላ ያላቸው የፋኖ ታጣቂዎች ቢኖሩም እና ጥቃቱም ምናልባት እነሱን ያለመ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ አደጋው ያረፈው ግን ከታጣቂዎቹ ርቆ ምንም በማያውቁት እና በዕለተ-ተግባር ላይ በነበሩት ምስኪን መነኮሳይት ላይ ነበር።

አደጋው የሰዎችን ሕይወት ከመቅጠፍ እና ከማቁሰል ባለፈ በገዳሙ መሠረተ-ልማት ላይም ከባድ ውድመት አስከትሏል። የገዳሙን ቤተ እግዚአብሔር ጨምሮ በርካታ ቤቶች ፈርሰዋል። በተለይም "ተግባር ቤት" በመባል የሚታወቀው እና ለገዳማውያኑ የዓመት ፍጆታ የሚሆን እህል የተከማቸበት ክፍል ሙሉ በሙሉ ወድሞ ከጥቅም ውጪ ሆኗል። የእናቶቹ ጉልበት የነበረው የከርሰ ምድር ውኃ መሳቢያ የብረት ቱቦ እና የውኃ ማጠራቀሚያ ታንከሩ ሳይቀር በፍንዳታው ብትንትኑ ወጥቷል።

ከዚህ ሁሉ ሰቆቃ በኋላ የወረዳው አስተዳደር ባደረገው የተሽከርካሪ ትብብር አማካኝነት፣ የቦረና ወረዳ ቤተ ክህነት ኃላፊ ሊቀ ካህናት ቀሲስ እንዳለ ሰማኝ እና ሌሎችም አባቶች ተረባርበው ቁስለኞቹን ወደ ሕክምና ማዕከል አድርሰዋል። በተለይ እጅግ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን አንዷን እናት በአስቸኳይ ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል መላክ ቢቻልም፣ የገዳሙ ሐዘን እና ከዓለማዊው ኑሮ ተገልለው በጸሎት በተወሰኑ ንጹሐን እናቶች ላይ የደረሰው ይህ ሰቆቃ ግን፣ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ልብ ለዘለዓለም የሚያደማ ሆኖ አልፏል።

Address

Washington D.C., DC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tewahedo World posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share