04/26/2026
ክፍል 5 (ማጠቃለያ)- የመፍትሄ ሀሳቦች
------------------------------------
"ቢቻላችሁስ በሰላም ኑሩ::" ሮሜ 12:18
"ከሁሉ ጋር ወደ ሰላም ሩጡ ቅድስናችሁንም አትተው::" ዕብ. 12:14
ቅዱስ መፅሀፋችንና ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ የምታስተምረን ለሰላም ዝግጁ እንድንሆንና ፀብና ክርክርን ከመካከላችን እንድናርቅ ነው::ለአለፋት ጥቂት እመታት በቤተክርቲያናችን ውስጥ ለተነሱ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ያላመጡ የውሸትና የለበጣ የመሰሉ የእርቅ ሂደቶች ቢደረጉም ውጤቱ ዛሬ የደረስንበት ደረጃ ላይ ልንደርስ ችለናል::ለዚህም አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ እንዲሉ ጥልቅ ውይይት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችና ችግሮች ቂምን ክፋትንና ጥላቻን እንዲወልዱ ሆኗል::
ዛሬ በሀገራችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች በእምነታቸው ብዙ በደልና ግፍ ሲደርስባቸው አቤቱታ የሚያቀርቡበት ሰሚ ባጡበት ዘመንና ከሩቅ ሆነን እያየንና እየተቆጨን ባለበት ሰአት እኛ እዚህ ሀገር ህግና ስርአት ከመናገር ነፃነት ጋር ባለበት ቦታ ሆነን ምእመናን ለማፈን እየተኬደ ያለው እንቅስቃሴ ሊወገዝ የሚገባው የአምባገነኖች አካሄድ ነው::
ቢሆንም ግን ማንኛውም የሀገርም ሆነ የቤተክርስቲያን ችግሮች በውይይት ቢፈቱ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ያመጣሉ ብለን ምእመናን እናምናለን::በእርግጥ ከውይይትና ከሰላም ንግግሮች አናተርፍም ብለው ጠብና ብጥብጥን ሁልጊዜም የሚመርጡ እንዳሉ ሳንገነዘብ ቀርተን አይደለም: ነገር ግን መፅሀፍ "እነዚህ የገዛ መንገዳቸውን መረጡ ነፍሳቸውም በርኩሰታቸው ደስ ይላታል" ኢሳ 26:3 እንዲል ፍርዱን ለእግዚአብሔር በመተው ነው::
በዚህ በደብረ ይባቤ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ውስጥ ዘላቂ መፍትሄ እንዲመጣ ከተፈለገ ከዚህ በታች የተጠቀሱት ነጥቦችን እንደ መፍትሄ ለማቅረብ እንወዳለን::ይህንን ስንል ግን እስከ ዛሬ ብዙ ጥያቄዎች ሲነሱ ሰበካ ጉባኤውና አጠቃላይ መስተዳደሩ ለህዝብና ለቤተክርስቲያኑ የቆየ ታሪክ ሲያሳዩ የሰነበቱትን ንቀትና ማን አለብኝነት ከመቀመጫቸው አስፈንጥሮ ለሰላምና ለውውይይት ይመጣሉ ብለን በቀቢፀ ተስፋ ተነሳስተን ሳይሆን ሁልጌዜም ምእመናን ሰላምና ውይይት የመጀመሪያ ምርጫችን እንደሆነ በእግዚአብሔርም በሰውም ፊት ለመመስከር ነው:: በዚህም መሠረት እነዚህን የአጭርና የረጅም ጊዜ የመፍትሄ ሀሳቦችን እንደሚከተለው እናቀርባለን::
1. አዲስ ቤተክርስትያን በመግዛት ስም አሁን ያለንበትንም በመሸጥ ምእመኑን ለመበተን እየተደረገ ያለው ማንኛውም እንቅስቃሴ በአስቸኳይ እንዲቆም::
2. በተደጋጋሚ እንደተገለፀው የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ የችግሮች በዚህ ደረጃ መድረስና በህዝበ ክርስቲያኑም ውስጥ መከፉፈል እንዲኖር ያላቸውን ሚና ከዚህ ቀደም ገልፀናል:: ስለዚህም ግለሰቡ ከማንኛውም የአስተዳደር ሀላፊነት ገለል እንዲሉና ዘላቂ መፍትሄ እስኪገኝ ከሁለቱ ሌሎች ካህናት ጋር በቀጣይ ምን መደረግ እንዳለበት በተለይም ሀይማኖታዊ ሀላፊነቶች እንዴት ማስቀጠል እንደሚቻል ምክክር ቢደረግ::
3. ምንም እንኳ ሰበካ ጉባኤው የስራ ዘመኑን እየጨረሰ ቢሆንም በምርጫ ሰበብ ሌላ ግርግርና ሁከት ከማስነሳት ይልቅ ህዝበ ክርስቲያኑ ገለልተኛ ናቸው ብሎ የሚያምንባቸውን ስዎች ወደፊት እምጥቶ አስተዳደሩን ለተወሰነ ጊዜ እንዲረከቡ ማድረግ::
4. ከአንድ አመት ተኩል በላይ ረፍዶ የቀረበው የሂሳብም ሆነ የቁጥጥር ክፍል ሪፖርቶች ብዙ ግድፈቶችና ግልፅነት የጎደላቸው እንደነበሩ ለሁላችንም ግልፅ ነው::ስለዚህም የውጭ ኦዲተርም በመቅጠርም ይሁን በሌሎች ባለሙያዎች የቤተክርስቲያኑ የሂሳብ አያያዝ በአግባቡ እንዲመረመር::
5. ቤተክርስቲያኑ ውስጥ የግለሰቦችን ፈቃድ ወይም በህግ አገላለፅ consent ሳይጠይቁ የሚደረጉ ማንኛውም የምስልም ሆነ የድምፅ ቀረፃ በአስቸኳይ እንዲቆም::
6. በደህንነት ስም ለአንድ ግለሰብ የተሰጠን የካሜራ እይታ ፈቃድ በአስቸኳይ እንዲነሳ::ግለሰቡ ከዚህ ቀድም የነበረው ፈቃድ ለምን እንደተነጠቀ የሚያመለክት መረጃ ማቅረብ እንደሚቻል ማሳወቅ እንፈልጋለን::
በመጨረሻም ምእመናንና ቤተክርስትያንን በመናቅ እየተደረጉ ያሉት ህገወጥ ድርጊቶች ብዙ ዋጋ ሊያስከፍላችሁ እንደሚችል አምናችሁ ጉዳዮ የሚመለከታችሁ ሁሉ ወደልቦናችሁ እንድትመለሱ እንመክራለን::
ወስብሀት ለእግዚአብሔር!!